በ አምሳል ወረታ
- ለአማራ የህልውና ተጋድሎ የሚያስፈልጉ ስልታዊ መፍትሄዎች
ሀ. የፖለቲካ እና ወታደራዊ ድርጅት
አንድነት ያለው አመራር መመስረት፦የአማራን የፖለቲካ እና ወታደራዊ የተጋድሎ እንቅስቃሴዎች ማስተባበር የሚችል የተማከለ አስተዳደራዊ መዋቅር መፍጠር አስፈላጊ ነው። አስፈላጊ ሀብቶችን በማሰባሰብ እና በማቅረብ ህብረተሰቡ በያለበት አካባቢ ራሱን መከላከል እንዲችል መከላከል ሰፋፊ አደረጃጀቶችን መፍጠር እና ማስታጠቅ ያስፈልጋል።
ለ. ጠንካ ኢኮኖሚያና ሚዲያ መፍጠር
ማዕቀቦች እና ኢኮኖሚያዊ ተቃውሞ – አማሮች ፀረ-አማራ ኃይሎች ከሚቆጣጠሯቸው ንግዶች እና የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋረጡ ማድረግ። የአማራ ሚዲያና የግንኙነት አውታሮችን ማጠናከር፦ በአማራ ትግል ውስጥ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመመከትና በአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን በበቂ ሁኔታ ለማጋለጥ የአማራ ሚዲያዎች አስፈላጊውን የገንዘብ ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ።
ሐ. የመረጃና ደህንነት ተግባራት እና የፀረ–ሰርጎ ገብ እርምጃዎች ተባባሪዎችን ማጋለጥ እና ማግለል፦ በአማራ ትግል ውስጥ ከአማራ-ጠል ኃይሎች ጋር የሚሰሩ ግለሰቦችን ከኃላፊነት ማንሳት።
የአማራ የስለላ መረብ መገንባት፦ የጠላት እንቅስቃሴዎችን ለመከታተል እና ጥቃቶችን ለመከላከል የሚያስችሉ ሚስጥራዊ የስለላ መረቦችን መፈጠር አስፈላጊ ነው።መ. የዓለም–አቀፍ ድጋፍ እና ዘለቄታዊ ጥምረት አስፈላጊነት የውጭ መንግስታትን እና ተቋማትን ማሳመን፦የአማራ ዳያስፖራ በአማራ ህዝብ ላይ ላይ የሚፈፀመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ዓለም አቀፋዊ እውቅና እንዲያገኝ ጫና መፍጠር መቻል አለበት።
ከሌሎች የተጨቆኑ ቡድኖች ጋር ጥምረት መፍጠር፦በስራ ላይ ያለውን የጎሳ ፌደራሊዝም ከሚቃወሙ ቡድኖች ጋር ስልታዊ ጥምረት በመፍጠር የአማራን ትግል ማጠናከር።
ማጠቃለያ እና አፋጣኝ የትግበራ ጥሪ የአማራ ህዝብ ወሳኝ በሆነ መስቀለኛ መንገድ ላይ ይገኛል። አንድነትን ማምጣት የማይቻል ከሆነ በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለው መዋቅራዊ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሊቆም አይችልም። በመሆኑም በደንብ የተደራጀ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ስትራቴጂን በአስቸኳይ መተግበር እጅግ አስፈላጊ ነው።
ነገሮችን በዝምታ የምንመለከትበት ጊዜ አብቅቷል። አማራ በተደቀነበት የህልውና አደጋ ልክ መንቀሳቀስ እና በተባበረ ክንድ ህልውናውን እንዲቀጥል ማድረግ አለበት። የአማራ ህዝብ በጋራ ጥረት፣ የአመራር ጥበብ እና ዘለቄታዊ ግብ ባለው የትግል መንገድ በህልውናው ላይ የተከፈተበትን ጦርነት መቋቋምና መመከት ይችላል። ይህ ትግል ዛሬን ብቻ ሳይሆን የወደፊቱን ትውልድ ህልውናም ታሳቢ ያደረገ ነው።
የአማራ ህዝብ በህልውናው ላይ የተከፈተበትን ጦርነት ሊመክት የሚችለው በጋራ ጥረት፣ በአመራር ጥበብ እና ስልታዊ ትግል በማድረግ ብቻ ነው!
- መግቢያ
የአማራ ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ነው፤ እየደረሱበት ያሉት ዘርፈ-ብዙ ጥቃቶችም ጊዜያዊ ሳይሆኑ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና መልከዓምድራዊ ከባቢ ስልታዊ በሆነ መልኩ ለማዳከም፣ ለማግለል እና ለማጥፋት የታለሙ የረጅም ጊዜ እቅድ አካል ናቸው። በአማራነት ላይ የተከፈተው ጦርነት እና እልቂት በአማራ ክልል የሚኖረውን አማራ ብቻ ሳይሆን በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በሌሎች የሀገሪቱክፍሎች ባሉ አማራዎች ላይም ጭምር የማያባሩ ጥቃቶችን ለመፈፀም ዒላማ ያደረጉ ናቸው። የጋራ ተግባር፣ የተስተካከለ አመራር እና ስልታዊ የትግል እንቅስቃሴዎች በሌሉበት ሁኔታ፣ የአማራ ህዝብ የገጠሙት ፈተናዎች በመጪዎቹ ጊዚያት በከፋ ሁኔታ ሊቀጥል ይችላል፣ መጪው ትውልድም ለነዚህ ተግዳሮቶች ተጋላጭ የመሆን ዕድሉ የሰፋ ነው።
አማራ እያደረገ ያለው የህልውና ትግል ዛሬ ላይ በህይወት ስለመኖር ብቻ ሳይሆን፤ መጪው የአማራ ትውልድም ደህንነቱ የተጠበቀ፣ የተጠናከረ እና የራሱን እጣ ፈንታ በራሱ መወሰን እንዲችል ማረጋገጥንም ታሳቢ ያደረገ ነው። ይህንን ውጥን እውን ለማድረግ፣ አማራ ግልፅ በሆነ የአመራር መዋቅር ስር ወጥ የሆነ የፖለቲካ ማህበረሰብ መፍጠር፣ ውጤታማ ስትራቴጂን መዘርጋት፣ እንዲሁም ዘለቄታዊ የሆኑ ተቋማትን መመስረት እና አማራ በኢትዮጵያ የፖለቲካ አውድ ውስጥ የሚገባውን ቦታ እንደሚይዝ ማረጋገጥ ያስፈልጋል።
- ለአማራ ህዝብ “የጋራ ጥረት” ማለት ምን ማለት ነው?
የጋራ ጥረት ማለት ሁሉም በኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረው አማራ ጭቆናን ለመቋቋም፣ የአማራን የፖለቲካ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማጠናከር እና መመጪውን ጊዜ ራስ-መር ለማድረቅ የሚደረግ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ነው። ይህ ማለት ሁሉም የአማራ ማህበረሰብ ክፍሎች፣ ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ የንግድ መሪዎች፣ የሃይማኖት ሰዎች፣ ወታደሮች፣ እና ዳያስፖራው የተነጣጠለ አካሄድን ትቶ በአንድነት የመስራት ባህልን ማዳበር ማለት ነው።
የጋራ ጥረቶችን ዕውን ለማድረግ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ስልቶች፦
- ህዝቡን መሠረት ያደረገ ራስን የመከላከል ጥምረት
✔ በእያንዳንዱ የአማራ ከተማ እና የገጠር መንደር በአማራ ላይ የሚቃጡ ጥቃቶችን ለመከላከል የሚያስችሉ አደረጃጀቶችን መገንባት።
✔ በክልልና እና ሀገር አቀፍ ደረጃ የደህንነት መዋቅሮችን በመዘርጋት በየአካባቢው ከተደራጁ ራስን የመከላከል እንቅስቃሴዎች ጋር እንዲጣመሩ ማድረግ ያስፈልጋል። 2. የዳያስፖራ ንቅናቄ እና ድጋፍ
✔ የአማራ ዳያስፖራ ትግሉን ለመደገፍ ያለመ የሀብት ማሰባሰብ እና የመደገፍ ስራን አሁን ካለበት ሁኔታ በበለጠ ንቁ ሚናን እንዲጫወት ይጠበቅበታል።
✔ በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በዓለም አቀፍ መንግስታትን እና ተቋማትን እውቅና እንዲያገኙ ለማድረግ እና ጫናዎችን ለመፍጠር የሎቢ ቡድኖችን ማደራጀት ይጠበቅበታል።
- የኢኮኖሚ ትብብር እና የፋይናንስ ነፃነት
✔ የአማራ ንብረት የሆኑ ንግዶችን እና የፋይናንስ የግንኙነት መረቦችን በመደገፍ የአማራን የኢኮኖሚ ስነ- ምህዳር መገንባት አለበት።
✔ ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ማህበረሰቦች ድጋፍ ለመስጠት እና የመሠረተ ልማቶችን መልሶ የመገንባት ጥረቶችን ለማገዝ የሚያስችል ፈንድ መመስረት ያስፈልጋል።
- የአማራ የፖለቲካ እና የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት
✔ ፀረ-አማራ ፕሮፓጋንዳዎችን ለመመከት ጠንካራ አማራ-ተኮር የመገናኛ ብዙሃን መረብ መመስረት አለበት።
✔ የአማራ ህዝብ በኢትዮጵያ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ የራሳቸውን ነጻ የፖለቲካ ተቋማት መፍጠር እና ማጠናከር አለባቸው።
ለ. የአመራር ጥበብን ማጎልበት እና ተዋረዱን የጠበቀ የዕዝ ሠንሰለትን መፍጠር
በአማራ ትግል ውስጥ ከሚታዩ ስር የሰደዱ ድክመቶች መካከል የተማከለ እና ስነ-ስርዓት ያለው የአመራር መዋቅር አለመኖር አንዱ ነው። ለብዙ አሥርተ ዓመታት በከፍተኛ ሁኔታ የተደራጀ የዕዝ ሰንሰለት ካለው ህወሓት አንፃር ሲታይ፣ የአማራ ተጋድሎ የተበታተነ እና ቅንጅት የጎደለው በመሆኑ ምክንያት አማራ ሲያደርግ የኖረው ትግል ተጎድቷል።3 የሚያስፈልገው የአመራር አይነት
- የአማራን ተጋድሎ በዘላቂነት ሊያሳልጥ የሚችል ሁሉን አቀፍ ምክር ቤት
✔ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የተጋድሎ እንቅስቃሴዎችን ማስተባበር የሚችል አንድ ጠንካራ የአማራ ምክር ቤት ማቋቋም አስፈላጊ ነው።
✔ ምክር ቤቱ ሁሉን አቀፍ የትግል ስትራቴጂን ማረጋገጥ እንዲችል ወታደራዊ መሪዎችን (የፋኖ ተወካዮችን)፣ ምሁራንን፣ የሃይማኖት መሪዎችን እና የኢኮኖሚ ባለሙያዎችን ማካተት አለበት።
- ያልተማከለ ግን የተቀናጀ አመራር
✔ ራስን ለመከላከል በየአካባቢው የሚደራጁ ቡድኖች (የፋኖ ክፍሎች) ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸውን ጠብቀው ነገር ግን ስርዓትን እና ውጤታማነትን በሚያረጋግጥ መልኩ በአንድ የዕዝ ሠንሰለት ውስጥ እንዲሰሩ ማድረግ ያስፈልጋል።
✔ ወታደራዊ አዛዦች፣ የፖለቲካ መሪዎች እና የኢኮኖሚ እቅድ አውጪዎች የውስጥ ግጭቶችን እና ክፍፍሎችን ለመከላከል በጋራ ራዕይ መስራት አለባቸው።
- ስነ–ምግባራዊ እና ግብረገብነት
✔ መሪዎች ተጠያቂ መሆን አለባቸው፤ ሙሰኛ፣ ውጤታማ መሆን ያልቻሉትን እና ከፋፋዮችን እየለዩ ከሃላፊነት ማንሳት ያስፈልጋል።
✔ መሠል እንቅስቃሴ አላስፈላጊ የሆነ ጣልቃገብነትን ማስወገድ አለበት። ነገር ግን በአማራ ጥቅሞች ላይ የሚያሴሩ ሰርጎ ገቦችን መለየት እና ገለል ማድረግ አለበት።
- መንግስት ሰርጎ እንዳይገባ መከላከል
✔ የኢትዮጵያ መንግስት እና አማራ-ጠል ኃይሎች አማራ ያቋቋማቸው ድርጅቶችን በተደጋጋሚ ሰርገው ገብተው ሲከፋፍሉ ተመልክተናል።
✔ በአማራ የትግል እንቅስቃሴዎች ውስጥ የተሰማሩ ሰላዮችን እና ለመንግስት መረጃ አቀባይ የሆኑ አካላትን በጥንቃቄ ለመለየት ልዩ የፀረ-ስለላ እና የመረጃና ደህንነት ክፍል መቋቋም ያስፈልጋል።ስልታዊ ጦርነት፡ የአማራ ህዝብ የህልውና ጦርነቱን እንዴት መዋጋት እና ማሸነፍ
አለበት?
በአማራ ላይ የታወጀው ጦርነት ወታደራዊ ዘመቻ ብቻ አይደለም። የህልውና፣ የስነ-ልቦና፣ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ጦርነት ጭምር ነው። አማራ ለትግሉ ምቹ እና ስልታዊ መንገድን መፍጠር የሚችለው ህልውናውን ከማረጋገጥ ባሻገር ለቀጣይ ድል የሚያበቃው የረጅም ጊዜ ራዕይ ሊኖረው ይገባል።
- ወታደራዊ ስትራቴጂ፡ መከላከል እና የመልሶ ማጥቃት
ሀ. በየግዛቱ ራስን የመከላከል ስልት፡
✔ ሌሎችየመከላከያ ብሔሮች (ትግራዮች፣ ኦሮሞዎች) በገነቡት ሠራዊት መሬታቸውን እንዳስጠበቁ ሁሉ እያንዳንዱ አማራ በሚኖርበት የገጠር መንደርም ሆነ ከተማ ራሱን መጠበቅ የሚችልበትን ስልት መቀየስ እንዲሁም ሠራዊት ማዋቀር አለበት።
✔ የጠላት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ዋና ዋና መንገዶችን፣ የውሃ ምንጮችን እና ስትራቴጂዊ ጠቀሜታ ያላቸው ከተሞችን ጨምሮ ሁሉንም ቁልፍ ቦታዎችን መቆጣጠር አስፈላጊ ነው።
ሐ.የሽምቅ ውጊያ እና የስለላ ተግባራት፡
✔ የጠላት ቅንጅትን ለማስተጓጎል እና እልቂትን ለመከላከል የሚያስችሉ በከተማ እና በገጠር ላይ የተመሰረቱ የትግል ህዋሶች መገንባት አስፈላጊ ነው።
✔ የጠላት እንቅስቃሴዎችን እና የመንግስት እቅዶችን ለመከታተል የሚያስችሉ የስለላ መረቦችን ማዘጋጀት።
መ.የጦር መሳሪያ እና የሃብት ማግኛ መንገዶች፡
✔ በአካባቢው ምርት፣ ከውጭ ሃይሎች ድጋፍ እና ከጠላት ሃይል የሚገኙ ወታደራዊ ግብዓቶችን መልሶ በማከፋፈል የጦር መሳሪያ እና አቅርቦቶችን ማግኘት ይቻላል።
- 2. የስነ–ልቦና ጦርነት፡ የትርክት ጦርነትን ማሸነፍሀ.ሚዲያውን መቆጣጠር
✔ በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፀሙ ጭፍጨፋዎችን ለመመዝገብ፣ የጠላት ፕሮፓጋንዳን ለመመከት እና እውነተኛ መረጃዎችን ለማሰራጨት ነፃና አማራ ተኮር የዜና እና መረጃ ማሳራጫ የሚዲያ መረቦችን ማቋቋም ያስፈልጋል።
✔ በአማራ ላይ የሚፈፀመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለዓለም ለማጋለጥ በእንግሊዝኛ እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች የተቀናጀ የሚዲያ ዘመቻዎችን ማካሄድ።
ለ.የአማራ ብሔራዊ ማንነትን መልሶ መገንባት
✔ በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የትምህርት ስርዓት ውስጥ ያሉ ትርክቶች የብዙ ወጣት አማሮችን አመለካከት መቅረፅ ችለዋል።
✔ የአማራን ታሪክ፣ ተጋድሎ እና አማራ ለኢትዮጵያ ያበረከተውን አስተዋፅኦ በትምህርት ቤቶች እና የባህል ተቋማት ተመልሰው እንዲተረኩና እንዲነገሩ ማድረግ።
- የፖለቲካ እና የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ
ሀ.ከዓለም አቀፍ አካላት ጋር ግንኙነት መፍጠር
✔ የአማራ ዳያስፖራ ማህበራት በአማራ ላይ ለሚፈፀመው የዘር ማጥፋት ወንጀል እውቅና እንዲሰጡ የምዕራባውያን እና የአፍሪካ መንግስታትን ማሳመን አለባቸው።
✔ የኢትዮጵያ መንግስት የፈፀማቸውን የጦር ወንጀሎችን ለተባበሩት መንግስታት፣ ለአፍሪካ ህብረት እና ለዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች በዝርዝር ሰንዶ በማቅረብ ክስ መመስረት ያስፈልጋል።
ለ.ከሌሎች የተጨቆኑ ቡድኖች ጋር ጥምረት መፍጠር
✔ አማራ የጎሳ ፌደራሊዝምን ከሚቃወሙ እና ኢትዮጵያዊ ማንነትን ከሚያቀነቅኑ ሌሎች ብሔሮች ጋር ጥምረት መፍጠር አለበት።
✔ ትኩረታችን የጎሳ-ፌደራሊዝም ስርዓትን በማፍረስ የሁሉምን ዜጎች ደህንነት የሚያረጋገጥ እና ፍትህ የሚያሰፍን መንግስታዊ ስራዓትን በማምጣት ላይ ያተኮረ መሆን አለበት።ሐ.. ትግሉ ለዛሬ ብቻ አይደለም፣ ለመጪው ትውልድ ጭምርም ነው እየተካሄደ ያለው የአማራ ተጋድሎ አሁን ያለውን ቀውስ ተቋቁሞ መሻገርን ብቻ ያለመ አይደለም፤ መጪው የአማራ ትውልድ ጭምር ነፃ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ጠንካራ እንዲሆን ማረጋገጥንም ዓላማ ያደረገ ነው። ያህንን ለማረጋገጥ፤ ተጋድሎው ከጊዜያዊ የትጥቅ ትግል ባለፈ ተቋማዊ ቅርፅ የያዘ መሆን አለበት።
- የአማራን የወደፊት ህልዎና እንዴት ማረጋገጥ ይቻላል?
- ዘላቂ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተቋማትን ማቋቋም
✔ የአማራን ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከበር ሃይል በመንግስት መዋቅር ውስጥ እንዲፈጠር ማድረግ ያስፈልጋል።
✔ የኢኮኖሚ ነጻነትን ለማስቀጠል በአማራ ቁጥጥር ስር ያሉ የፋይናንስ ተቋማት መገንባት አለባቸው።
- ትምህርት እና የወጣቶች ንቅናቄ
✔ በመጪው ትውልድ ውስጥ መሪዎችን እና ታጋዮችን ማዘጋጀት እና ማብቃት እንዲቻል በትምህርት ቤቶች የአማራን ታሪክ፣ የተጋድሎ እንቅስቃሴዎችን እና የአማራን ብሔራዊ ኩራት ማስተማር እጅግ አስፈላጊ ነው።
✔ የትግሉን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የአማራ ወጣቶች ራስን በመከላከል፣ የስለላ እና የፖለቲካ ስልቶች ላይ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ ያስፈልጋል።
- ትውልድ ተሻጋሪ ራዕይ ለአማራ ጥንካሬ
✔ የአማራ ህዝብ ከሚቀጥሉት 5 ወይም 10 ዓመታት የተሻገረ ዕቅድ ማበጀት አለበት። ከ50 እስከ 100 ዓመታት የሚደርስ ራዕይ በማንገብ አማራ በኢትዮጵያ የሚገባውን ቦታ እንዲይዝ ማድረግ ይቻላል።
✔ ይህም ማለት የመጪውን የአማራ ትውልድ የፖለቲካ፣ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የበላይነትን ማምጣት የሚችሉ ፍኖተ ካርታዎችን ማዘጋጀት ማለት ነው።ማጠቃለያ፡ አፍጣኝ እና ቀጣይነት ያለው የትግበራ ጥሪ አማራ ጦርነት የታወጀበት ህዝብ ነው፣ ጉዳዩም የህልውና ጉዳይ ነው። ለመጪው የአማራ ትውልድ ስቃይ እና ጭቆና ላለማውረስ አፋጣኝ እርምጃን መውሰድ ያስፈልጋል። ወደ ድል የሚያደርሰው ብቸኛው መንገድ በጋራ መታገል፣ ስርዓቱን በጠበቀ አመራር እና ስልታዊ ትግል ማድረግ ብቻ ነው። አማራ አንድ መሆን፣ በብልሃት መታገል እና የወደፊት ህልውናውን በፅኑ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተቋማትን መገንባት አለበት።
በአማራ ትግል ውስጥ የቀጠሉ አለመግባባቶች፣ ምክንያቶች፣ የሚያስከትሏቸው አሉታዊ ውጤቶች እና ለሕልውና ትግሉ የሚያስፈልጉ መፍትሔዎች – ክፍል አንድ