September 27, 2023
2 mins read

ትግስት አሰፋ የሮጠችበት ዐይነት አዲዳስ በ500 ዶላር መሸጥ ጀመረ

Tigist Assefa 1 1የአዲዳስ አዲሱ ጫማ የሆነውና፣ ባለፈው እሁድ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትግስት አሰፋ በበርሊን የማራቶን ሬከርድ የሠበረችበት ዐይነት ጫማ፣ ትናንት ማክሰኞ በ500 ዶላር ዋጋ ገበያ ላይ መዋል ጀምሯል።

የሩጫ ጫማ ገበያውን ለመቆጣጠር ከናይኪ ጋር ከፍተኛ ትንቅንቅ ላይ ያለው አዲዳስ፣ አዲስ ያቀረበው ‘አዲዚሮ ፕሮ ኢቮ 1’፣ ናይኪ ካቀረበው ‘አልፋ ፍላይ 2’ ዋጋው በ 225 ዶላር ይበልጣል። አማተር ሯጮች ጫማውን ለመግዛት ተጨማሪውን ዋጋ ለመክፈል ፍላጎት ያሳዩ እንደሁ ይታያል ሲል ሮይተርስ በዘገባው አመልክቷል።

አትሌቶች በተሻለ እንዲሮጡ ለማስቻል፣ ሶሉ ወፈር ያለ እና ለስላሳ እናዲሁም ከካርበን ፋይበር የተሰራ ንጣፍ ያለው ጫማ መመረት ከጀመረ አንስቶ፣ ሁለቱ የጫማ አምራቾች ከፍተኛ የንግድ ፉክክር ውስጥ ቆይተዋል።

አዲሱ የአዲዳስ ጫማ በጣም ቀላልና ክብደቱ 138 ግራም እንደሆነ እንዲሁም የሚያገለግለው ለአንድ ማራቶን ሩጫ ብቻ እንደሆነ ተገልጿል። ሯጮች ለእያንዳንዱ ማራቶን አዲስ መግዛት እንዳለባቸው ኩባንያው አስታውቋል።

ጫማው ለፍጥነት እንጂ ለረጅም ግዜ ለማገልገል እንዳልተሰራ የገለጸው አዲዳስ፣ ትናንት ማክሰኞ 521 ጫማዎችን ለገበያ አቅርቧል። ተጨማሪ ጫማዎች በሕዳር ወር ለገበያ እንደሚቀርቡም አስታውቋል።

አዲዳስ ጫማው ሬከርድ ሰባሪ እንደሆነ በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል። ከትግስት አሰፋ ጋር አዲሱን ጫማ ይዘው የተነሱትን ፎቶ በኢንስታግራም ያጋሩት የኩባንያው ዋና ሥራ ስፈጻሚ ቢዮርን ጎልደን፣ “ትግስት አሰፋ እንኮራብሻለን!” የሚል ጽሁፍም አክለውበታል።

VOA

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop