ያግኙን

Please visit us every time, we hope you enjoy it and we welcome any feedback. Send any comments and questions concerning zehabesha.com to us at
aatebeje@gmail.com
admin@zehabesha.com
971- 426 6404

 የzehabesha.com መስራች እና ዋና አሳታሚ እና ስራ አስፈፃሚ ሲሆን ከዚህ ቀደም በቅንጅት ሰሜን አሜሪካ ፣ቅንጅት ፣አንድነት ፓርቲ እና ፍኖተ ነፃነት ድረ-ገጾች ይመራ ነበር።  # እባኮዎትን ለ ዘሀበሻ ፌስቡክ ፣ ዘሀበሻ ኦፊሻል ዩቲዩብ ፣ ዘሀበሻ ሬስቶራንት ፣ለሌላ ማንኛውም የሀበሻ  የሚዲያ አውታር ስልክ አትደውሉ:: ስልክ ቁጥሩ ለ amharic.zehabesha.com ግንኙነት ብቻ ነው የሚያገለግለው

 አልዩ ተበጀ

Zehabesha.com
2005 – Present


Please Give Your Own Honest Opinion About US

Your opinion matters to us! If you love our work then your reviews helps us to improve our work and enhance the value we stand for. With your help, we can gain greater visibility  Click here to Review 

56 COMMENTS

  1. I believe you are not balanced and fare since all you focus on is negative news and information. The same is true on the other side as it is only the positive news that gets any air.

    Now iit is all polarized, who is going to break this cycle? How are we meant to be civilized? What is wrong in being fair and reasonable?

    • To tell you the truth i am only visiting two wesbsites those are This one and Awramba times are those only two who are showing both side of the story.

      The rest are one sided extrimist. I know this website is a bit sided with G7 and Awramba with Woyanne but they both put every news and leave the reader to decide.

      I think the zehabesha is a web sight with most updated news. Whenever there is an important breaking news, this is where I read it first. I think you provide a balanced and fair reporting. In addition to the political news, you provide you readers with important health information, sport and entertainment. Most importantly you post the daily ESAT news which is awesome. The only thing I would love to read on your Web sight is more inspirational stories of Ethiopians who accomplished in different field. This can be from within Ethiopia or around the world. In addition, one thing I read a lot on people comment, it seems like there lots of people who know little about the history of their country. They rant negatively about ethnic groups. If the zehabesha posts our history of togetherness, our ancestors love to their country and people, our week ability to tolerate one another..etc, this may help most of us to be aware of our true history rather than afe tarik. Keep doing the wonderful job you are doing and I give you a big tumbs up for even asking our opinion.

      you are doing a good job!!!!you are on the right track!!!!keep on!!!! @kal are you looking for report on hidase gidib, growth and transformation etc!!!Media must not fear anybody and must be fare to nobody!!!Their main objective should be…telling the truth!!!!

      you are doing a good job!!!you are on the right track!!!!keep on!!!!@Kal are you looking for a report on hidase gidib,growth and transformation,etc!!!! Media must not fear anybody and must be fair to nobody!!!! ..their main objective should be….telling the truth!!!!!

      Just carry on as usual. You are providing a good service to our people are helping to promote democracy through the open forumms that are provided for everybody to have their say. What I suggest is that you sometimes need to look at a particular point of view and judge it on the value that it brings to the discussion at hand. If it does not it should be censored.

      Outright insults, uncivilised talk and such like should be banned.

      As a diaspora news outlet it is difficult to be fair and balanced. You need to distance your self from other foreign backed websites.

      Thank you zehabasha you are the number one balanced website.There is no discrimination in your website.Long live to Zehabasha.

      So far I see little biasedness other wise well and fine web site. When I said little biase you lean toward one group and one religion just like king Haile time. I don’t blame you for this for you are the offspring of that group. I am sure next generation will be free of this/

      You doning a great job with free press, a few may oppose for a few articles, but still we have to learn the other side story, deal with it, and come up with a solution. Hiding is not a solution. We all know what we can do and what we can not do.
      Getahun

      Zehabesha web site is one of the best so far. you guys always give us breaking news way ahead of the others.The other thing is you have your websites both in English and Amharic which makes it easy for every Ethiopian to get latest news. Keep up the good work!!!

      Zehabesha,

      Truly an Ethiopian web site since it entertains the diverse views of the country and the people. I always belived that hypocricy does not serve a coomon good unless we practice what we say. A number of web sites call themselves the “Ethiopian Democratic” web site when we know how biased their coverage is. One notable web site is only interested on the issue of Assab and nothing else about the TPLF government bothers the editorial body. While the issue of Assab is important, reducing the human rights violation of the Tigrean government against non-Tigreans must be of the prime importance if we have to live together.
      I can say that your web site is the first I check for any news. I have given up on others and I am pretty sure that many people have done the same.

      Zehabeshawoch enay betamnew yemtekemwe yenanten metatefe bemulu eketatelalehu,betam gen letenenetay astemarewochay nachuna amesegenachuwalhu.andanday tenshe legha ethiopiaweyan yemaysefelgu negrochin makrebuin betetyafu yebelet ewdachuwalhu.amesegenalhu.

      Hi Habesha,

      You are doing a great job. Keep it up!!!! Having said that I have two comments. (1) Please do not interefere in church affiars. A few months ago you posted an article about Medhanealem Church (Minneapolis) including the photos of the priests. Although I agree with some of the points raised in the article, let spiritual issues be discussed at the church face to face, with politeness and with the fear fo God, not here behind the computer screen. (2) A few weeks ago, you posted an article mentinoning that Dawit (from Awaramba times) was seen at the Ethiopian Embassy, in DC, on a certain day, probably arranging his return to Ethiopia. However, I read an article by Dawit in which he claimed that he was somewhereelse on that day. As an evidence for this, Dawit sent you the copy of his air ticket. I want you to comment on that.

      Thanks again for being a great source of news from the MOTHERLAND. I check your website every hour.

      The bad thing about it all is that I was a Late Comer to the Site.Since then I have enjoyed it every bit of it including Tena Adam. . The latest of which was the interview with Lidetu Ayalew. It was an information in clear thinking. It was a political thought ABC.. Besides I always wondered why people just “voted” to misunderstand/hate Lidetu.I also enjoyed the piece by Temegen.
      Please Keep up the Good Work
      A Luta Conua!!

      Though I`m late comer and rarely post any comments here, your website is much better than many others. Firsts, I was suspicious about your name brand–TheHabesh name– which excludes many Ethiopian nationalities except Amharas and Tigrians groups. I thought an inclusive name would have conveyed the message better to majority of Ethiopian, but it is too late at this juncture. Second, If your website refrains from the negatives of religious hyperbole as some polarizing other sites are doing, especially about Ethiopian Muslims, your site reputation will only increase over time thereby attracting many decent readers. Thanks you guys and good luck for your hard works

      If yoy really need opinion of your readers. it should be confidential and not in public .if it’s help !!! Any way I like your hard work keep it up bro

      Ze Habeshoech,
      I comment rearly and when I do it is in your website, because you provide good source of information and fair selection of comments.Keep up the good work do not always listen to the flock, there are moments the flock could be misgiuded and can end up misguiding you, free thinking is a choice and there are flocks who are scared of this and judge you thier ennemy. what is not apealing to you can be of benefit to others.Give a fair chance to free thinking comments as well.
      Thank you I like your work.
      Lej.Mesfinachew Anteneh AKassa.

      Zehabesha website is the number one choice news media for me for the last three years, compare with other ethiopian related media website, because of well balanced and accommodate all kind of views. Also the most abated and brought true professionalism way of informing to our people! I hope your good work will continue and there are many backwards media are exist for ex ecdaform with full of old school thinkers. All the best zehabesh we love you.

      Ze-Habesha is the most reliable news source for Ethiopians. I am very pleased with your job. The only problem is with Ze-Habesha magazine. Be on time. It is very informative magazine. I do not think it is a big deal of posting the magazine on time. Previously, I mentioned to the chief editor but no improvement is shown.

      Keep up the good job !!!

      Ze-Habesha,
      Please read my above comment as “Ze-Habesha Newspaper” instead of “Ze-Habesha magazine”. Sorry!
      Talking about magazine, what happened to Madina magazine used to be issued by Ze-Habesha fellows? It was the best Ethiopian magazine in the U.S. Please continue.
      Thanks.

      Honestly speaking, at the beginning I have never expected fair information from name Zehabesha as this name was used by first class Ethiopianist who want Ethiopia to serve them but doesn’t want to see the people on that earth. I found Zehabesha fair online media as it tries to entertain divers views and opinions. I understand there is massive pressure from self claimed first class ethiopianst who are a curse for that land and rebuffed by majority. At this rate, Zehabesha editor will be a unique person next to Walelign from Abyssinians camp who is naturally gifted to think as human being. Good job. I wish you all the best.

      የዘ-ሃበሻ ተከታታይ ነኝ ጥሩ የዜና ምንጭ ነው። ከዚህ ውጪ ተጨማሪ አስተያየት አለኝ
      – ማድረግም ሆነ ጽሁፎች መምረጥ አይቻልም እና አስተካክሉት
      – እንደ ጋዜጠኛ ከሃገር ቤት ዜና ስትሰማ የሚመለከታቸውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ሞክር ቢቻል እየቀዳሃቸው መልሳቸውን አሰማን። አድራሻቸውን እና ስማቸውን መጥቀስ ሳትረሳ
      – ከፖለቲካ ውጪ ከማህበራዊ ሚዲያዎች ኢትዮጲያውያን የሚያካፍሏቸውን አሪፍ ቪዲዮዎች እያካተትክ መዝናኛነቱን ጨመር አርገው
      – ከታዋቂ ሰዎች ጋር ቃለመጠይቅ ለማድረግ ሞክሩ

      የዘ-ሃበሻ ተከታታይ ነኝ ጥሩ የዜና ምንጭ ነው። ከዚህ ውጪ ተጨማሪ አስተያየት አለኝ
      – Right click ማድረግም ሆነ ጽሁፎች መምረጥ (Select) አይቻልም እና አስተካክሉት
      – እንደ ጋዜጠኛ ከሃገር ቤት ዜና ስትሰማ የሚመለከታቸውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ሞክር ቢቻል እየቀዳሃቸው መልሳቸውን አሰማን። አድራሻቸውን እና ስማቸውን መጥቀስ ሳትረሳ
      – ከፖለቲካ ውጪ ከማህበራዊ ሚዲያዎች ኢትዮጲያውያን የሚያካፍሏቸውን አሪፍ ቪዲዮዎች እያካተትክ መዝናኛነቱን ጨመር አርገው
      – ከታዋቂ ሰዎች ጋር ቃለመጠይቅ ለማድረግ ሞክሩ

      To be honest, you come close to what I call a genuinely ETHIOPIAN media. You put out news as they come. I do not see too much bias in the origin or perspectives.

      I have always hoped, rather dreamed, that a day will come when we come out of the chronic segregation disease where Amharas, Oromos, Tigres, Somalis etc, just talk in their own domain, without any exchange of view points with others. Ideally, we have as few as possible websites so that we all get exposed to divergent viewpoints, regardless of the inconveniences this might cause. It is only that way that we progressively get more and more united as a nation.

      What is happening now is rather scary, groups talking their own members – preaching the convert. The way we exchange ideas and generate “political thoughts” is equivalent to in-breeding in “biology”. It is weird, it has to change. In that respect, you are doing much better than others.

      Having said this, I do not see other well known Ethiopian websites and blogs in your “Ethio Newslinks”. For instance, where are Opride.com, Ayyaantuu.com, Gullelee Post.com, etc?. You must have had some criteria to exclude these and other pages, but then again you are inconsistent because I see OLF in the listing of opposition groups. Just get over it and aspire to become fully Ethiopian.

      Best wishes

      I am Eritrean. I read your website almost daily. I appreciate your website for presenting balanced news. I can say it is web site of all “THE HABESHs”,be Ethiopians or Eritreans. Please continue the same.

      From- GETACHEW REDA (Editor Ethiopian Semay):

      You made me laugh when you asked readers an opinion about your website. Are you serious you respect readers and writers’ opinion?
      I sent you two articles for post this year. One commentary was about Tamang Beyene, Islam and its history in Ethiopia. You decline to post it because you claimed you will not post comment in regard to Tamang. I asked you why. You reason was “it will weakened the struggle”. He is God or a king not allowed by opposition media for any critique

      The other commentary sent to you to be posted was ድምፃችን ዛሬም ነገም የጎሹ ወልዴ ነው!” This was also focusing Ethi-WEritrea issue that Col. Goshu addressed Ethiopian legal argument opposing Western plots against Ethiopia. You decline to post it (My guess is it deals also with Ginbot 7 and Eritrea and decline to post it- because your Ginbot 7 was mentioned ), that too was declined to be post.

      I asked you three times to provide me reason for your refusal. As an editor, you should have given me reason for it- be it- reasonable or not. But, you felt shy to give your reason- because -your reason seemd to be poor for response and declined from answering it. I am asking you still to come up with reason for your decision not to post it.

      The sad thing is you give Shaabia agents like Amanuel Beademariam and Sofia (our enemies) many times repeatedly to insult our Ethiopia while you refuse to serve Ethiopian issue that opposed Shaabia and its clicks. I asked you why you decline to response. Are you shy to response because your answer might not be adequate for argument? Why are you asking readers here our comment about your webite when you know you are repressing Ethiopian voices? Your OLF, ONLF, EPLF readers will love to hear your action against Ethiopian voices- because, that is what they are looking for. A subversive media! You still need to answer it why? Check your email for evidence. Boy! you are only fooling yourself, not me. If you are Ethiopian, serve Ethiopians not anti Ethiopian groups. Do nor be a subversive agent for them.
      Thanks Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay) getachre@aol.com

      Getachew Reda,

      You are blaming Ze-Habesha for declining your articles. On the other hand, you have your own website/blog and you never treated any other openions other than yours (EPRPS). Ask yourself before blaming other. Do you really post an article if I write you about Our hero Tamagne? Have you ever mentioned about Ethiopian Muslims movement. All you are doing is posting negative aticles, back biting and proofless videos in your closed door website. Be out of your box first, Semay man. You are still on “Semay”. You think you are the only one who loves Ethiopia and struggles for Ethiopian. Loving Ethiopian is not just liking Ethiopian Semay only but loving Ethiopian people first. Boy! Land on Ethiopian earth and face the reality and start to like people. The problem with you and your fellow is that no say or write about Ethiopian struggle but your.group. Do you really beleive in FREEDOM OF SPEACH? ask youself.

29 Comments

  1. Zehabesha publishers,
    I am glad you are becoming a source of info esp for Ethiopians. But there is a lot more to do. If I were you I would take time to study reasons for readers deserting Abugida, Ethiomedia, and Ethiopia Register.

    If you think you could go on promoting your biases in the guise of providing fair and factual perspectives, think again. Sooner or later you will meet the fate of Abugida.

  2. ሐበሻ ዜና በኢትዮጵያ ውስጥ በጣም አንባቢ ያለው ድህረገፅ ጋዜጣ ነው ፡፡ እንደኔ ምልከታ. ሐበሻ ዜና አርታኢ ገጽ እና አንዳንድ የዜና ሽፋኑ ተራማጅ እይታ እና የአለምን የእድገት እይታ ያዘሉ ናቸው። ነገር ግን ሐበሻ የሪፖርት ሥነምግባር ደረጃዎችን እና የጋዜጠኝነትን መደበኛ ይዘቶችም በሁሉም መስክ ያመጣጠነ ነው:: በንግድ ፣ በፖለቲካ እና በባህል ሽፋን መሪ እንዲሆን ጥርጣሬ የለኝም።

  3. ወደ አስመራ የሚመለሱ የተቸገሩ ኤርትራዊ መንገደኞች የግድ ገንዘብ መዘረፍ አለባቸዉ?

    የአስመራዉ መንግስት ኮሮናን መከላከል የምንችለዉ በራችን ጠርቅመን ነዉ በማለት ወጥቶ የነበረዉ ሰዉ እንዳይመለስ ሆኖ በኢትዮጵያና ሌሎች አገሮች ለወጪዎችና ሌላም ችግሮች ተዳርጎ ቆይቷል።
    ታድያ ከዉጭና ከዉስጥ ጭሆት ሲበዛ የኤርትራዉ መንግስት፡ የኤርትራ ቀዋሚ ነዋሪ መሆናቸዉ ማረጋግጥ የሚችሉ መመለስ ይችላሉ ብሎ በመወሰኑ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጥቅምት መጨረሻ አከቢ ወደ አስመራ እንደሚበር በድረ-ገጹ የበረራ ፕሮግራሙን ማስታወቅ ጀምሯል።
    አስገራሚዉ ነገር ግን አየር መንገዱ በምን ምክንያት እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም ከአዲስ አበባ አስመራ የአንድ ጊዜ መሄጃ ቲኬት ዋጋ በአጭር ጊዜ ከ7000 ወደ ከ27000 የኢትዮጵያ ብር በላይ ከፍ አድርጎታል። ከዚህ በላይ አስደንጋጭ ዘረፋ ምን ሊኖር ይችላል?
    በዚሁ ኮሮና አስጨናቂ ወቅት ተዘግቶባቸዉ ለወራቶች ሲሰቃዩ የነበሩ ኤርትራዉያን አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሊዘረፉ ነዉ።
    ይህ እጅግ ያሳዝናል።
    የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰዉን ችግር ለጥቅሙ ባያዉለዉ መልካም ነዉ።

  4. TMH በ10/04/20
    በሚል ርእስ አወያዩ አቶ ስታሊን “ዶ/ር ሮንዳስ እሸቴ” ብሎ ከጠራው ሰው ጋር ባደረገው ውይይት ወቅት ሮንዳስ የተባለው “ዶ/ር” የ 10 ስኮንድ እንሰሳዊ ንግግሩን ህዝብ እንዲያውቀው በቪድዮው ላይ ይህንኑ ያለበትን ደቂቃና ሰኮንድ ጠቅሼና
    [ከ29:52 ደቂቃ እስክ 30፡02 ደቂቃ]
    የኔኑ እጅግ በጣም የተመጠነ አስትያየቴን ጨምሬ አስፍሬያለሁ፡፡ ይህኑ አስትያየቴን ከታች ለአንባቢዎች እንደገና አስፍሬዋለሁ፡፡ ከሮንዳስ እንሰሳዊ እሳቤ በተለየ መልኩ ሆኖ እኔም አብይ አገሪቱን በትክክለኛው መንገድ እየመራት እንዳልሆነ እገነዘባለሁ፡፡ በዝነኛው ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የተነገረውን ምክር (ነፍስ ይማር እያልኩ) በአንድ እጁ ህግ በሌላኛው እጁ ሰይፉን መያዝ ባለማወላወል መጓዝ ግድ ይለዋል፡፡ ካላዳላና (የሚያዳላ ይመስለኛል) ካልሰረቀ (ሌባ ፈጽሞ አይመስለኝም) ፡ አሁንም ጊዜው አልመሸበትም፡፡ክወያኔ ሌቦችና ከተረኛ ነን ባዮቹ በስተቀር ህዝቡ አሁንም ከጫፍ እስከጫፍ ከእርሱ ጋር ይቆማል፡፡ እነዚህ ሁለቱ ስብስቦች ፈጽሞ የህዝብም የእውነትነትም መሰረት የላቸውምና በቀላሉ ይናዳሉ፡፡ ካስፈለገም ይመታሉ፡፡ ይህንን ማድረግ ደግሞ እጅግ አስፈላጊና አማራጭ የሌለው ቀጭን ግን ብቸኛ የመፍትሄ መንገድ ነው፡፤ አለበለዚያ አብይም “ህልሙ” ይከሽፋል፡ አገሪቱም በአብይ አመራር ስህተት ምክንያትነት ብቻ ችግር ውስጥ ትወድቃለች፡፡

    My TMH comment on the issue was the following
    ሮንዳስ እሽቴ ፦ በዚህ ቪድዮ ላይ በትክክል ደቂቃውን ለመጥቀስም ያህል ከ29 ደቂቃ 52 ሰኮንድ ጀምሮ እስከ 30ኛው ደቂቃ 02 ስኮንድ ድረስ ለ10 ሰኮንዶች የተናገርከው ይህንን ነው፡፡ ” አብይን አርዶ ስጋውን ተከፋፍሎ ጠብሶ መብላት ” ብለሃል፡፡ የሰውየውን ሰቅጣጭ አባባል እውነት( ሰው ነውን???) ለህጋዊ እርምጃም ሆነ ለመታዘብ እባካችሁ በቪድዮው የተጠቀሰውን 29ኛ ደቂቃ ላይ ሂዱና አረመኔው ሮንዳስ ያለውን ስሙት፡፡ ዶክተር ነው ተባየው ሮንዳስ ፦ ዱሮስ እናንተ……. ሰው አርዶ ስጋውን ተከፋፍሎ ጠብሶ መብላት……..

    • ከላይ ለሰፈረው ጽሁፌ የOct. 4,2020 የTMH (Tigray Media House) የውይይቱ ርእስ የነበረው
      የሚል ነበረ; ከይቅርታ ጋር !

  5. “አብዮቱ እንቁላሌን ከመበላት ያስጥልልኛልን?..”
    ጌድዮን በቀለ
    Gedionbe56@yahoo.com
    ኖቬምበር 8፣ 2020 አርሊንግተን ፤ቨርጅንያ
    ጊዜው ሚያዝያ 1991 አ,ም ነበር፤ በኢትዮጵያ ወገን ከ70ሽህ በላይ ወጣቶችን ቅርጥፍ አርጎ የበላው የባድሜ ጦርነት መፈንዳቱ ይፋ የሆነበት፤ የወያኔና ሻቢያ የጫጉላ ሽርሽር ያበቃበት እለት፡፡ ቦታው ባህርዳር የአማራ ክልል መናገሻ ከተማ፤
    እንደተለመደው ከጓደኞቼ ጋር ሆኘ ዘወትር እራት ከምበላበት ኤርትራዊው አቦይ ኪዳኔ ግሮሰሪ ጓዳ ባለገመዱ ሶፋ ላይ ተቀምጨ ያቦይ ኪዳኔ ልጅ ማርታ ከጎረቤታቸው ካለው ምግብ ቤት ያዘዝኩትን ራት አምጥታልኝ አጎንብሼ እየጎራረስኩ በቢራየ አወራርዳለሁ፡፡ ከስራ አምሽቼም ብወጣ እንኳ ቋሚ ደንበኛና ቤተኛ ስለሆንኩ የግሮሰሪው ባለቤት ልጅ ማርታ ምግብ ቤቱን አስከፍታ በልዩ ትእዛዝ አሰርታ ስለምታስመጣልኝ እራት አጥቸ አላውቅም፡፡
    እንደኔ ሌላው የመሸታ ቤቱ ደንበኛ በስካር አንደኛነቱ የተጨበጨበለት የክልሉ የደህንነት ቢሮ ሃላፊ የትም ውስኪውን ሲጋት አምሽቶ ያቦይን ግሮሰሪ ሳይረግጥ አያድርም፡፡ በዚህ የተነሳ ከእኔ ጋር አዘውትረን እንገናኛለን፤ ዛሬም እንደወትሮው ሁሉ ገና በሁለት ሰአት ከምሽቱ ጥንቢራው ዞሮ እየተንገዳገደ ገባና ከእኔ በስተቀኝ በኩል ካለው አግዳሚ ወንበር ላይ ወርዶ ዘጭ አለ፡፡ “ እህም… ነጋዴው አለህ እንዴ? “ አለና ተደላድሎ ሳይቀመጥ የነገር ጉሸማውን ለመጀመር አኮበኮበ፤
    “ አለሁ የት እሄዳለሁ?” አልኩት ደረቅ ፈገግታ አሳይቼ፤ “ የለም! የለም! አገር ሲወረር የት ነበርክ? ማለቴ ነው” አለኝ እየተለፋደደ፤ ትውውቃችን ከጎንደር ጨዋ ሰፈር ጀምሮ በ1960ዎቹ መጨረሻ ኢህአሠን ተቀላቅለን ጫካ እስከገበንበት ይዘልቃል፡፡ ዛሬ እሱ የባለጊዜዎቹ “ድል አድራጊ” ገዥዎች ዋና የደህንነት ሹም እኔ ደግሞ በአንደበቱና እውቀቱ አዳሪ የኮምፒዩተር ባለሙያ መምህር ሆኜ ብንገናኝም በመነቋቆር የተሞላው ጨዋታችን ግን ከነበረን የቆየ የትውውቅ ስንቅ የሚቆነጠር ነበር፡፡
    በዚህ የተነሳ ሞቅ ካላለው በፈገግታ የታጀበ ሳቅና ጨዋታ፤ ሞቅ ካለው ደግሞ በስላቅ ሳቅና ሽሙጥ እየተሸንቋቆጥንና እየተነቋቆርን እንተላለፋለን፡፡ ሁልጊዜ ስላቁ የሰላ ቢሆንም፤ በዚህ የተነሳ እኔን ለክፉ ያሰጠኛል ብዬ አስቤም ፈርቼም አላውቅም፡፡ በዚህ ምሽት ግን ደህንነቱ ወዳጄ ጥንቢራው የዞረው በመጠጡ ብቻ ሳይሆን “ ያመኑት ፈረስ.. “ እንዲሉ የፈጣሪያቸው ሻዕቢያ ክዳት እንደተጨመረበት ለማሳየት ጊዜ አላባከነም፡፡” እንግዲህ ጦርነቱ ተጀምሯል! አሁን ደግሞ ከየትኛው ጎራ ተሰልፈህ ይሆን? አለኝ ከወትሮው በተለየ የሽሙጥ ስላቁን አጠንክሮና እርግጠኛ በሆነ ስሜት፤
    “የትኛው ጦርነት? “ አልኩት የጠቀለልኩትን እየጎረስኩ ባልገባውና ባልሰማ ሰው የተረጋጋ መንፈስ፤
    “ጭራሽ! ጦርነቱን አልሰማሁም እያልከኝ ባልሆነ! “ አለኝ ከበፊቱ ተቆጥቶና ተኮሳትሮ ጉሽርጥ የመሰለውን አይኑን እያጉረጠረጠ፤
    “እውነቴን ነው ፤ ከጭምጭምታ ያለፈ አልሰማሁም፤ ጦርነት ተጀመረ እንዴ? “ አልኩት በተረጋጋና የእሱን ቁጣ ያላስተዋለ ነፈዝ በመምሰል፤
    “ ከአብዮታዊነት ጭልጥ ወዳለ ሶልዲ (ፍራንክ) አሳዳጅነት መሻገር የሚገርም መንሸራተት ነው” አለኝ፤ ሽርደዳ መሆኑ ነው ፤ ቀጠለ” ዛሬ ቁርጥ ያለ አቋምህን ማወቅ እፈልጋለሁ፤ ያለው ሁለት አማራጭ ብቻ ነው! “ የተወረረብንን ግዛት አስመልሰን ሏላዊነታችንን እናስከብራለን ፤የሚልና የለም ቀይባህር ውስጥ እንጨምራቸዋለን፤ አሰብን እንቀማቸዋለን የሚል የትምክህት ጎራ አማራጭ፤ አንተ የየትኛው ጎራ ነህ? መቸም በዚህ አያያዝህ ከትምክህተኞት ጎራ የምጸለፍ ይመስለኛል፤ አለ የምጸት ሳቅ እየሳቀ፡፡
    ”ከሁለቱም ያልሆነ ሶስተኛም ፤አራተኛም ምርጫ አለ እኮ፤ አንተ አልታየህ ይሆናል እንጅ” አልኩት እኔም በምጸት የለት እንጀራዬን እየበላሁ፡፡
    በፍጹም! ሊኖር አይችልም! ማንም ቢሆን ከነዚህ ሁለት አማራጮች አይወጣም! አለኝ፤”
    “ ሶስተኛው ወገን ቢያንስ ይጠይቃል፤ ውጊያው ለምን አስፈለገ? ከውጊያው ምን አተርፋለሁ? ይልና የሚያስገኝለትን ትርፍና ኪሳራ መዝኖ ከውጊያ በመለስ ያለ አማራጭ ላይ ሊያማትር ይችላል፤ ይሄ ቢያንስ ሶስተኛ አማራጭ ሊሆን አይችልም?” አልኩት በለበጣ የጎሪጥ እያየሁት፡፡ እስክጨርስ አልጠበቀኝም፤ ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳና እየተንቀጠቀጠ አምባረቀብኝ፤ “ ይሄን ያክል ትዘቅጣለህ ብየ አልጠበኩም ነበር፤ የነዋይ ፍቅርህ ከህዝባዊ ትግልና ከሃገር ፍቅር ስሜትህ ልቆ ይቦጠቡጥሃል ብዬ አልገመትኩም ነበር” አለኝ የኔ “ አገር ወዳድ ባለጊዜ”፡፡
    ጩኸቱና ቁጣው ያስደነገጣቸው ጓደኞቼ የሰውየውን ባለጊዜነትና የስልጣን ጉልበት ስለሚያውቁ የሚገቡበት ጠፋቸው፤ ያችን ቀን ከኔ ጋር በመታየታቸው ነገ ከነገ ወዲያ በስራቸውና በህይወታቸው ላይ ሊደርስ የሚችለው መአት እያሰቡ ተሽቆጠቆጡ፡፡ ለኔ ግን ከቀድሞው የኢህአፓ ባልንጀሬ ፊት ላይ ያነበብኩት ድንፋታ ከተበለጥኩ የባዶነትና ፤ ከተከዳን ቁጭት የመነጨ የተሽናፊነት ብስጭት እንደሆነ ለመረዳት ጊዜ አልወሰደብኝም፡፡ ከዚያ በፊት በነበሩ ጊዜያቶች “የማን ወገን እንደሆንኩ” ለማወቅ ያደረገው ጥረት ሳይሳካለት መቅረቱ ተደማምሮ አቃጥሎታል፡፡ የስለላ ጥረቱ እኔን ሰውየውን ሳይሆን እኔ የማላውቀውን ማንነት ከጀርባየ ለመቆፈር መሞከሩ ያስከተለበት ኪሳራ መሆኑን እንኳ አልተገነዘበም፡፡
    “አምርረሃል እንዴ? ይሄን ያክል አገርህንና አገሬን ከእኔ አስበልጠህ እንደምታፈቅራት እየነገርከኝ ከሆነ ከመሸታ ወጭ ተገናኝተን አገሪቱ በማንኛችን ሰበብ የተነሳ እዚህ ፈተና ውስጥ እንደገባች ተነጋግረን ሂሳብ ልናወራርድ እንችላለን፤ ያኔ እጅግ ቢያንስ የመከላከል አቅሙ ቢያጥጥብኝ ያለአበሳዬ ሌሎች ባቀጣጠሉት ነበልባል ሳልጠይቅና ሳላስተውል ገብቼ የምማገድ የእሳት እራት አለመሆኔን ትረዳልኝ ይሆናል! ከማለቴ በቆመበት ሳይቀመጥ ተፈናጥሮ ወጥቶ ሄደ፡፡
    ይሁንና ጦርነቱን እኔ ብደግፍም ባልደግፍም፤ ማስቆም ግን አልተቻለኝም ነበርና በጦርነቱ የተቃጠሉና የረገፉ ወገኖቼን ልቅሶ አብሬ ከማልቀስ ግን አላመለጥኩም፡፡ እንበለ ትርፍ ደማቸው ከፈሰሰው፤ አጥንታቸው ከተከሰከሰው ከሰባ ሽህ ሙታን ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ቤተሰቦች ጋር ልቤ እንደተሰበረ እስከዘንድሮ አለሁ፡፡
    “አገርህ ተወረረች “ ሲባል እየፎከረ የፈንጅ ማምከኛ ሆኖ የተማገደው ኢትዮጵያዊ በማይተካ ህይወቱ ያተረፋት አገር ከድል ማግስት ቋንቋው፤ እምነቱና ማንነቱ እየተመነዘረ ያለርህራሄ በጭካኔ የሚገድልባት፤ በቆንጮራ የተቀላው አንገቱ፤ በሳንጃ የተዘከዘከው አንጀቱ የሚቀበረበት አፈር እንዲነፈገው ሆነ፡፡ የሞተላት ኢትዮጵያ የመቆሚያ መቀበሪያውን ነፈገችው፡፡ እሳቱን የለኮሱት ነፍሰበላዎች ግን በአጥንቱና በመቃብሩ ላይ ህንጻ በህንጻ ላይ ሲገነቡ እሱ ከእነማቲዎቹ ይልሰው ይቀምሰው አጥቶ የመኖር ህልውና ተነፍጎት እንደተሳደደ ቀጥሏል፡፡
    ስለሆነም ዛሬ አብረው ገዝተውን፤ ተባብረው አዳምተውን፤ ያቋሰሉን አጋዳዮቻችን በሁለት ጎራ ተከፍለው “የማን አባት ገደል ገባ” ሲሉን አስቀድመን እንዲህ ብለን እንጠይቃለን፤
    `የጆርጅ ኦርዌሏ ዶሮ እንደጠየቀችው፤ “ ከዚህ ጦርነት ምን እናተርፋለን?” ብለን በመጠየቅ እንጀምራለን፡፡
    “ በእርግጥ አብዮቱ እንቁላሎቼን ከመበላት ያድንልኛልን? የሚታለበው ወተቴ ለጥጃየ እንደማይነፈገው ያረጋግጥልኛልን? …” እያልን እንቀጥላለን ፡፡ ከዚህ ጦርነት በኋላ በዘራቸው ፤ በቋንቋቸው፤ በእምነታቸውና በሆኑት አንዳች ምክኛት የሚታረዱ አማሮች፤ጉራጌዎች፤ ጋሞዎች፤ አገዎች፤ አፋሮች፤ ሶማሌዎች ፤ ጌዲዎዎችን ፍልሰት ይገታልን ? ብለን እንሞግታለን፡፡
    ይህ ጦርነት የሰቆቃችን ሁሉ ምንጭ የተቀዳበት መርዘኛ ብልቃጥ ላንዴና ለዘላለም ይታሸጋል? አሁን የገባንበት አበሳ ጠንሳሽ የሆነው ትህነግ በዚህ ጦርነት የሚወገድ ከሆነ እሱ የተሰራበት የሞት ሰነድ በዚህ ጦርነት ተቀዳዶ በምትኩ የህይወት ሰነድ ይተካል? ወይስ ሞታችን የገዳያችንን ሰነድ ዘላለማዊነት የማጽናት ነው?
    እንጠይቃለን! ይህ ጦርነት “ አማራ የሚባል ጭራቅ መጣብህ!” በሚል ሃሳዊ ትርክት የተዘራውን የጥላቻና ባንድ ወገን ላይ ያነጣጠረን መሰሪ የፈጠራ ዘመቻ ያስቀራልን? እያልን እየጠየቅን ፤ ለጥያቄአችንም ዋስትና የተግባር ምላሽ ማግኘት የዚህ ጦርነት ቁልፍ ተልእኮ ሊሆን ይገባል፡፡
    ከጦርነቱ መልስ በጭራሮ የዘጋነው ጎጆአችን ውስጥ የቀቀልነው ንፍሮ ተከፍቶ አለመበላቱን፤ በሰታቴ የተጣደው አጥንታችን ተግጦ መግላሊቱ ተሰብሮ በዝንብ አለመወረሩን፤ የጭራሮዋ ቤታችን ፈራርሳ መጠለያ አለማጣታችንን ካላስረገጥን ፤ እጣ ፋንታችን፤ በሞታችን አገራችንን ከማዳን ይልቅ ጨርሶ ማጣትን እንደማይስከትል ልብ እንድንል የትናንትናዎቹ ውድቀቶቻችን ትምህርት ሆነው ካላነቁን ያው ከሙታን በምን ያክል እንሻላለን??? ጥያቄ፡፡

  6. የምትገርም አገር
    ጃዋር እና እስክንድር እየተናበቡ ነው፡፡ (OMN) እና Ethio 360ም እየተናበቡ ነው፡፡ አሉን ሳያፍሩ !!
    ዛሬም በጦርነት ወቅት፡ ዛሬም የአገሪቱ የጉዞ አቅጣጫ ባልለየለት ጊዜ፡ ዛሬም እንደ አገር ለመቀጠል/ላለመቀጠል በገደል አፋፍ ላይ ቆመን ባለንበት ጊዜ ፡ ዛሬም ሚሊዮኖች በረሀብ አለንጋ ሊረግፉ ባሉበት ወቅት፡ ዛሬም ከውጭም ከውስጥም ጠላትም ወዳጅም እየተወራረድብን ባለበት ክፉ ቀን ላይ ሆነን አሁንም ለግል ስልጣን፡ አሁንም ለግል ምቾትና ዝና፡ ለግል የረዥም አመታት የመግዛት ከንቱ የማይሳካ ቅዠትና ምኞት ህዝቡንና አገሪቱን መረማመጃ ማድረግ እጅግ የከፋ፡ እጅግ የከረፋ እጅግ የወረደ ቆሻሻ ድርጊት ነው፡፡
    እስኪ እግዜር ያሳያችሁ፡፤ ተከበብኩ ብሎና፡ መንጋ ሰብስቦ ሰውን በዘር እየለየ በመምረጥ እንድታረዱ ያስደረገው ጃዋር ነው፡፡ ሻሸመኔ ላይ ሰው ዘቅዝቆ ያሰቀለው ጃዋር ነው፡፤ ከዚህ በተቃራኒው አዲስ አበባ የኗሪዎችዋ ነጻ ምርጫና ውሳኔ ተከብሮ እንደ በዚህ ቀደሙ ቁመናዋ ራስዋን በራስዋ እንዳታስተዳድር በአብይ አህመድ እየተሰራባት ያለውን ሽፍጥ በድፍረትና በግንባር ቀደም መሪነት ሲታገል የነበረው የህሊና እስረኛው እስክንድር ነጋ ነው፡፡ ታዲያ ታላቁ እስክንድርን ከአረመኔው ጃዋር ጋር እየተናበቡ ነው ወንጀል የሰሩት ብሎ ማለት ምን ማለት ነው? በሰማይና በምድር፡ በፍልስፍና፡በእምነት፡ በአስተሳሰብና በህሊና ምዘና የማይገናኙትን እነዚህን ሁለት ሰዎች ወንጀል የፈጸሙት እየተናበቡ ነው ብለው ክስ እንዲመሰረት ያደረጉት የአሁኗ የአዲስ አበባ ከንቲባ የበፊቷ አቃቤ ህግ መሆናቸው ይታወሳል፡፡
    ይታያችሁ፦ እስክንድር በአንድነት በማመን በአስተሳሰቡ “ለሁላችን” በሚል ጎራ ሲመደብ ጃዋር በተቃራኒው “ሁሉ የእኔ” የሚሉ የኬኛ መንጋዎችን ይዞ በተረኝነት በዘረፋና ግዲያ ላይ ተሰማርቶ የነበረ ሰው ነው፡፤ በኦሮሙማ እምነታቸው አብይ አህመድም ጃዋር መሀመድም ዳውድ ኢብሳም ዶ/ር መራራም ታዬ ደንደአም ፡አዲሱ ቂጤሳ፡ ሽመልስ አብዲሳም ሆነ ሁለቱም ሌንጮዎች ወዘተ ያው አንድ ናቸው፡፤ የኦሮሞ የበለይነት፡፡ ሁሉ የእኛ፡፡ በድምሩ ዘመናዊ ድንቁርና፡፤ የማይሳካ ቅዠት፡፡ በዜግነት ኢትዮጵያዊ ለመሆኑ ጉዳዩ ተድበስብሶ መማረጋገጫ ሳያገኝ የቀረው የኦፌኮው አባል (መሪ እንበለው) ጃዋር አሁን በእስር ላይ የሚገኘው በአንድ ምክንያት ብቻ ነው፡፤ ይህም በአብይ አህመድ ወንበር ላይ ስላፈጠጠ ብቻ ነው፡፡ ይህ ነው እውነቱ፡፡ይህ ባይሆን ኖሮ ጃዋር ያሻውን ወንጀል ሁሉ እንደፈለገ ቢፈጽም ጠ/ሚ/ር አብይ አያስሩትም ነበረ፡፤ ሚስጢሩም አብይ ጃዋርን በስልጣኑ ላይ ለመቆየት “ለሌሎች” የማስፈራሪያ መሳሪያው አድርጎ ይመለከቱት ስለነበረ ነው፡፤ ትክክለኛ አሰራርን የሚከተል ትክክለኛ መንግስት ቢኖር ኖሮ ጃዋር ከኢትዮጵያ የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመመሳጠርና “ሁለተኛ መንግስት እኔ ነኝ” ብሎ በኦሮሙማ ሰንሰለት ያንን ሁሉ ሲያዘርፍና ጭፍጨፋ ሲያስፈጽም ዝም ባልተባለም ነበረ፡፤ ትክክለኛ አሰራርን የሚከተል ትክክለኛ መንግስት ቢኖር ኖሮ ከወያኔ እስር ቤት የወጣውን እስክንድር ነጋን አሁን መልሶ የውሸት ሴራ ፈጥሮ እንደገና በለውጥ ሀይል ተብየው እንድታሰር ባልተደረገ ነበረ፡፡
    አሁን ደግሞ በደህንነቱ መ/ቤት በሁለተኛ ደረጃ ካለው ሰው አፍ ሌላ ጉድ እየሰማን ነው፡፡ ይህም የጃዋር OMN እና Ethio 360 ሁለቱም የወያኔ ቅጥረኞች ሲሆኑ የሚሰሩትም እየተናበቡ ነው የሚል ነው፡፡ ይህ ቆርጦ ቀጥል ውሸት፡ ይህ የተሾረበ የኦሮሙማ ሴራ ፤ይህ የሚገማና የሚገለማ የፖለቲካ ድሪቶ ነው፡፡ Ethio 360 አያሌ ኢትዮጵያዊ ጉዳዮች የሚመከሩበት ነጻ የሆነ የሚሊዮኖች ኢትዮጵያዊያን መድረክ ነው፡፤ እኛ ኢትዮጵያዊያን ከምንኮራባቸውና አለኝታዎቻችን ከሆኑት ነጻ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያን ከሚሸትቱ መድረኮች አንዱ ነው፡፡ የማያወላውል አቋሙም ጸረ ወያኔና ጸረ ኦነግነት ነው፡፤ የጃዋር OMN ግን በአጭሩ ጸረ ኢትዮጵያ የሆነ በኦሮሙማ መርዝ የተመረዘ ዘረኝነትን የሚሰብክ መድረክ ነው፡፤ OMN ከወያኔ ጋር የተቧደነ ጸረ ኢትዮጵያ መድረክ ነው፡፡ ለዚህም ብዙ ማስረጃዎች አሉ፡፡ በሬድዮ ስርጭቱ ከባድ እልቂትን በማስከተሉ በሩዋንዳ በአዋጅ እንደታገደው እንደ RTLM ሬድዮ ጣቢያ ሁሉ OMN ኦሮሞ በአማራና ሌሎች ዘሮች ላይ ተነስቶ ፍጅትና ጭፍጨፋ እንዲፈጽም የሚቀሰቅስ መድረክ ነው፡፤ይህንኑም አብይ አህመድን ጨምሮ ብዙዎች ያውቁታል፡፡ ታዲያ እንዴት ነው ሁለቱ የሚናበቡት? ሲገርም?? ጃዋርና እስክንድር እንደዚሁም (OMN) እና Ethio 360 እየተናበቡ ነው የሚሰሩት ባዮቹ ከንቲባዋም ሆኑ የደህነነት ምክትል ሹሙ በፖለቲካ ቁማሩ እንዲሰማሩ የተመለመሉ ተራ የቁማሩ ተዋናዮች እንጅ ይህንንና ሌሎች አያሌ የፖለቲካ ቁማሮችን የመጫዋቻ ህግ፡ ቦታ፡ጊዜና ሁኔታ ወስነው ጨዋታውን በበላይነት እየተቆጣጠሩ የሚመሩት ዶ/ር አብይ አህመድ ለመሆናቸው አያሌ ማሳያዎችን ማቅረብ ይቻላል፡፡
    ህዝብን ይህንን አታድርግ፡ ይህንን አትስማ፡ ይህንን አትከተል ብለህ ልታቆመው የምትችልበት የሞኞች ጊዜ አልፏል፡፡ ስለዚህ ሞኞቹ መሪዎቻችን ሆይ ፦ወደ ህሊናችሁ ተመለሱና የአገሪቱንና የህዝቦቹዋን ታላቅነት ሚዛን ላይ አስቀምጣችሁና መሬት ላይ ያለውን ነባራዊ እውነታ መሰረት አድርጋችሁ አሁን ለአገራችን የሚያዛልቀውን ለማድረግ በሀቅ ለሀቅ ቁሙ፡፡ በዘር ላይ ይተመሰረተውን የደደቢት ህገ መንግስትንና ራሱን የዘረኝነት አሰራርን በህግ ማገድ ቀዳሚ እርምጃዎች ሊሆኑ ይገባል፡፡ አሁን ላይ እንደ አገር ከመፍረስ የሚያድነን አንድ ብቸኛ ፈውስም አለ፡፡ ይህም ሟቹ ወያኔ በኦነግ ውስጥ የዘራው መርዝ ወደ ነቀርሳነት ከመቀየሩ በፊት ከስሩ መንቀል ነው፡፤ ይህ ሳይሆን ቀርቶ አገሪቱ ከፈረሰች ተጠያቂዎቹ እናንተው ናችሁ፡፤ በውጤቱም የምትመኙት የኦሮሙማ የበላይነት ቅዠት ሳይሳካ እንደፈረሰው የወያኔ የበላይነት ቅዠት መጨረሻው ከንቱ ሆኖ ይቀራል፡፡ በዚህም ማንም አይጠቀምም፡፡ ለሚመጣውም ከወያኔ የባሰ የከፋ አወዳደቅ እናንተው ተጠያቂ ስለምትሆኑ በወቅት አስቡበት፡፡ ቶሎም ተስተካከሉ፤፡ እግዜርም በጎውን ያሳያችሁ፡፡

    ዶ/ር አብይ ሆይ፦ ፖለቲከኛ ነዎት፡፡ የታሪክ አጋጣሚም በሚገርም ግጥጥሞሽ ተመቻችቶልወት ነበረ፡፡እርሰዎ የሚሰሩት ስራ ያለዘረኝነት ለሁሉም በእኩልነትና በሀቅ ቢሆን ኖሮ እንደ አርሰዎ የታደለ አይኖርም ነበረ፡፡ግን ምን ያደርጋል የአህያ ስጋ አልጋ ሲሉት መሬት እንዲሉ ሆኖ ቀረ እንጅ፡፡

  7. – – – የመቀሌዉ ድምጽ ተሰማ
    የአዲሳባዉ አቢይ አህመድ “ቀይመስመሩ ስለታለፈ በኮማንድ ፖስት እየተመራ ——” ብለው በትግራይ ለ 3- ሳምንታት ያህል የዘለቀዉን ጦርነት መጀመር ይፋ ሲያደርጉ፡ ለእንደኔ አይነቱ “የፈሩት ይደርሳል – – ” የሚለዉ ብሂል እዉን የሆነበት ጊዜ ነበር።
    ጦርነቱ በይፋ ከመታወጁ ሰአታት ቀደም ብሎ ጥዋት ላይ ከዚሁ ከአመሪካ መቀሌ ነዋሪ ለሆኑት እህቴና ባለቤቴ ደዉየ ሳናግራቸዉ፡ እህቴን “የጦርነት ድባብ አለ? ምናልባት ጦርነት ሊከሰት ይችላል – – ” ብያት ነበር። እስዋም ስትመልስልኝ “ምን – – አሁንም መግለጫ ነዉ። ያዉ ሁሌም እንደተለመደዉ – – – ። መግለጫዉን እንደሆነ ለምደነዋል። ማለቂያ የለዉም – – ” ነበር ያለችኝ።
    ባለቤቴን ደግሞ “መቀሌ ላይ የጦርነት ሁኔታ ያለ ይመስላል?” ስላት “ምን እነዚህ በራሳቸዉ ጊዜ የለመዱትን ጦርነት አሁን ለኛ እያመጡብን ነዉ። ገና ሂወትን እየጀመርናት ላለነዉ እኮ ነዉ እያበላሹብን ያሉት። ህጻኑ ልጃችን ለምን ጦርነት ያያል? ጊዜዉ የኛ እንጂ የነሱ እኮ አይደለም” ብላኛለች።
    በመጨረሻም “ለማንኛዉ ከቤት እንዳትወጡ። ጦርነት ሊኖር ይችላል!” ነበር ያልኳት።
    ለሶስት ሳምንት የሚቀጥል ጦርነት፡ ከአንድ ወር በላይ ትግራይን በመዝጋት ድምጽ አልባ የሚያደርግ ሁኔታ ይፈጠራል ብሎ ማሰብ ግን እንዴት ይቻላል? ማታ ላይ በድንገት የሆነዉ ነገር እሱ ነበር።
    የመቀሌ ቤቴሶቦቼና ወዳጆቼ የማገኝበት የኢሞ አፕሊኬሽን ላይ በእንግሊዝ ቋንቋ የሚንነበበዉ ጽሁፍ “ለመጨረሻ ጊዜ መስመር ላይ የነበሩት ኖቨምበር 3 2020 ላይ ነዉ – – ” እንዳለ ከአንድ ወር በላይ ቆሟል። ልክ የመቃብር ድንጋይ ላይ ያለ ጽሁፍ ይመስላል። በዚሁ ቀን ነበር ጥዋት ላይ ከቤተሰቦቼ ለመጨረሻ የተገናኘነዉ። ከዚሁ ቀን በኋላም በኢሞዉ መደወያ ላይ ያሉት የቤተሶቦቼና ወዳጆቼ ፎቶግራፎችም የህያዉያን አልመስልህ አሉኝ። በየቀኑ እነዚህን ምስሎችንና ጽሁፍን ስመለከት ጸጸት ይለቁብኝ ነበር – – “ጦርነት እያጠላ መሆኑ ገብቶኝ ሳለ ሚስቴንና ልጄን ከመቀሌ ወደ አዲሰባ ለምን ዞር አላደረግኳቸዉም?” የሚል ጸጸት ሲሞሮምረኝ ቆይቷል – – ።
    አመሪካ አገር አብራኝ ካለችዉ እናቴ ጋራ ስንነጋገር “ባለቤቴን ለምን ገንዘቡን በዛ አድርጌ አላኩላትም?” በየ እራሴን በምወቅስበት “በአንድ ምሽት፡ በድንገት እኮ ነዉ ሁሉም ነገር ቀጥ ያለዉ። ቴሎፎ ባይቋረጥ አንድ ነገር ማድረግ ይቻል ነበር” ብላኛለች ካንዴም ሁለቴም፡ ስታጽናናኝ።
    ከዜህ በፊት ባለቤቴን ዳጎስ አድርጌ ገንዘብ ስልክላት “ለምን? ከበቂ በላይ ነዉ – -!” ትለኛለች። እኔም “የሚሆን አይታወቅም። ምን ግዜም ከእጅሽ በቂ ገንዘብ ቢኖርሽ ጥሩ ነዉ” እላት ነበር። ታዲያ፡ ዛሬ ዲሰምበር 13 2020 እንደገለጸችልኝ፡ ጦርነቱ ከመሆኑ ከጥቂ ቀናት በፊት የላኩላትን ገንዘብ ከባንክ ሳታወጣዉ ስለቀረች የባንክና የተሌፎን አገልግሎት በድንገት ቀጥ ሲል ጊዜ ከእጅዋ ምንም ገንዘብ አልነበራትም።
    – በደርጉ ጊዜ በ17 አመታት ዉስጥ በትግራይና ኤርትራ ጦርነት እያየንና እየሰማን አድገናል። ምጽዋ በሻቢያ ተይዛና አስመራ ዙርያዉን ተከባና ተጨንቃ ከአንድ አመት በላይ በቆየችበት ጊዜም ከከተማዉ ነበርኩኝ። ነገር ግን እንዳአሁኑ ወቅት ህዝብ ያለ ቴሌፎን፡ ዉሃ፡ መብራትና የባንክ አገልግሎት ለአንድ ወር ዝግትግት ያለበት ሁኔታ አልነበረም። ትግራይን ያጋጠማት ይህንኑ ነበር። ለዚሁ ሁሉ ተጠያቂ ማን ነዉ? እንዲህ ለማድረግ ባለመብቱስ ማን ነዉ? ቤተሰቦቻችን ከፍተኛ አደጋ ዉስጥ ለመክተት ማን መብት አለዉ? በእዉነቱ የትግራይ ህዝብ ይህን ጉዳይ አጥብቆ መጠየቅ አለበት።
    “ህግ ለማስከበር – – ” ይላል ይየፌደራል መንግስት። “ሳይቀድሙን፡ እራሳችን ለመከላከል – – ” የትግራዩ መንግስት ምክንያት ያቀርባል። ነገር ግን በማሃሉ ፍዳዉን ያየዉ የትግራይ ነዋሪ ምን ይላል?
    “የሰሜን እዝ ተመታ – – ” የሚለዉ የፌደራል መንግስቱ ማብራርያ፡ የጦርነቱን ምክንያት አደገኛ አድርጎታል።
    ለእንደኔ አይነቱ፡ ልክ የደርግ መንግስት ወድቆ ክረምት ሲሆን አዲስባ ከፒያሳ በረንዳ ላይ የገዘኋት መጽሃፍ “አፍሪካና አምባገነን መሪዎችዋ፡ ዘአፍሪካንስ፡ የምትለዋ መጽሃፍ ያሳፈረችዉ – – “አፍሪካ ዉስጥ ሰላም መጣ ብሎ መተማመን አይቻልም። ምን ግዜም ጦርነት ሳይታሰብ ይፈነዳል” የምትለዋ አረፍተነገር ነዉ ጦርነት በተቀሰቀሰ አጋጣሚ ከአምሮየ የምትመጣብኝ። ከኢህአዴግ ንግስና በኋላ ጥቂት አመታት እንደተቆጠሩ የፈነዳዉ የኢትዮ-ኤርትራዉ ጦርነት ይህቺንኑን አረፍተነገር ነበር ያስታወሰኝ። የዶክተር አቢይ የፍቅርና የሰላም መርሆ ከታወጀ በሶስት አመታት ዉስጥ ከትግራይ ክልል መንግስት የተገባዉ ጦርነት አሁንም ያቺኑ አረፍተ-ነገር ነዉ ያመጣብኝ።
    ለጦርነታችን ማናችዉም ማብራርያና ምክንያት ልንሰጠዉ እንችላለን። ዞሮ ዞሮ ግን “አፍሪካ ዉስጥ ሰላም ሰፍኗል ብሎ መተማመን አይቻልም” ነዉ መደምደሚያዉ።
    – መቀሌ ዛሬ እሁድ ዲሰምበር 13 2020 ድምጽዋ እንደተሰማ ከአንድ ወር በኋላ ያገኘኋት ባለቤቴ “ዋናዉ ጭንቀቱ ነበር የገደለን። በተለይ መጨረሻ ላይ አስቸጋሪ ሆኖብናል። ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመቱ አዳግቶን ነበር” አለችኝ።
    “ገንዘብስ። ተቸገርሽ ነበር አይደል?” ስላት “እንደ አጋጣሚ በማንዋል ሰርተዉ አባቴን ደሞዝ ሰጥተዉት ነበር። እህልም አስፈጭተን ይዘን ቆይተናል። ዉሃ ነበር ከፍተኛዉ ችግራችን።”
    “ወደ ገጠር ትሸሻለች ብየ ፈርቼ ነበር” ስላት፡
    “ስዎች እንሂድ ብለዉን አበር። እኔ ግን ልጄን የት አስተኛዋሎህ? ይታመምብኛል ብማለት አብምቢ ብያሎህ። ለራሴ አልተጨነቅኩኝም። እዚሁ ከተማ ዉስጥ የሚሆነዉን እንቀበላለን ነዉ ያልኩዋቸዉ” አለችኝ።
    “ልጄ ጦርነቱ አላስጨነቀዉም?” ስላትም
    “ሚጎቹ በአከባቢ ስለደበደቡ ድምጹ አሸብሮታል። ከዚህ ቀደም በእጁ እያመለከተ አየር – – ብሎ ይደሰት ነበር። አሁን ግን አዉሮፕላን ሲያይ አየወድም” ብላኛለች።
    እህቴንም ብቴሎፎ ሳወራት “ከፍተኛ ጭንቀት ነበር። በተለይ ‘ቲፒ ኤል ኤፍ’ ከከተማዉን ለቀዉ ሊወጡ ሲሉ ፍንዳታዎች ነበሩ” ብላኛለች።
    ስለሶት አመቱ ልጄ ስጠይቃትም “ፍንዳታዎች ሲሰሙ አሁንስ ወዴት ነዉ የምንሄደዉ? ብሎ ጠይቋል አለችኝ። ስለሚጎቹ ስትነገረኝም “አየር እንዳትመታሽ ብቻሽን አትሁኚ። ወደኛ ቤት ነይ” ብሎኛል አለችኝ።

    – ይሄዉ ነዉ – – ። ጦርነቱና ብጥብጡ ወደ ሶስተኛዉ ትዉልድ ዘልቋል። አዲስ የተወለዱ ልጆቻችንን ልክ እንዳባቶቻችን፡ ጦርነት፡ አለመረጋጋትና የኢኮኖሚ ቀዉስ እያወረስናቸዉ ነዉ። እኛዉ እራሳችን ችግሩን ስለምንፈጥረዉ መፍትሄዉ የለንም። በዚሁ ምክንያትም መከራችን ከፍ ያለ ይሆናል።

  8. የእጅ አዙሩ አማራን የማጥፋት የኦሮሙማ ፕሮጀክት በቤንሻንጉል

    ወያኔ ቤንሻንጉል ብሎ በፈጠረው ክልል ውስጥ አሁን ላይ በተባባሰ ሁኔታ እየተካሄደ ያለው የንጹሃን አማራወች፡ ጉምዞች፡ አገዎች ወዘተ ጭፍጨፋወች በአማራና በቤንሻንጉል ክልል መካከል እንደተፈጠረ ውጥረት አድርጎ መውሰድ ፍጹም የተሳሳተ ነው፡፡ የቤንሻጉሉም ሆነ የወለጋና የሌሎች ቦታወች የአማራዎች ጭፍጨፋ ምስጢር አንድና አንድ ብቻ ነው፡፤ ይህም ወያኔ ጀምሮትና ብዙ ግፎችን ሰርቶበት ያልተሳካለትን አማራን የማዳከምና የማጥፋት ዘመቻ ቅጥያ ነው፡፡ የአሁኑ ተረኛ ኦሮሙማም በማፍዘዝም ይበሉት በማደንዘዝ ወይንም አረመኔያዊ ድርጊታቸውን በፈለጉት በሌላ ስም ይጥሩት አላማው አማራን አዳክሞና አጥፍቶ ኦሮሞን በአማራ ላይ የበላይ፡እንደዚሁም አማርኛን አዳክሞ ኦሮሞኛን በአማርኛ ላይ የበላይ አድርጎ ኢትዮጵያን እንደ አዲስ በኦሮሞ ቅርጽ፡ ወርድና ስፋት የማበጀትና የመስራት ስራ ነው፡፡ የማይሆን የኬኛዎች የቀንም የማታም ቅዠታቸው ነው፡፡ ይህ ሴራ ሁሉም ኦሮሙማወች ተማምለው የጀመሩት ያልተቀደሰ ብቻ ሳይሆን ሊሳካ የማይችል መጨረሻው የአገር መውደቅን የሚያስከትል ሴራ ነው፡፤ በመጨረሻም ራሳቸው ኦሮሙማወች እርስ በርስ ተበላልተው ድራማው በውድቀት እንደሚጠናቀቅ ፈጣሪ እድሜ ይስጠን እንጅ በእርግጠኝነት ሲፈጸም እናየዋለን፡፡

    ለዚሁ የኦሮሙማ ፖለቲካ ቁማር መሪውና ኮማንደሩ ዶ/ር አብይ አህመድ እንጂ ሽመልስ አብዲሳ/ ጃዋር/ መራራ/ ዳዉድ ኢብሳ/አዲሱ ቂጤሳ ውይንም ሁለቱ ሌንጮዎች ……ወዘተ አይምሰሏችሁ፡፡ እነሱ ታዛዦች ናቸው፡፡እንዳትሳሳቱ፡፡ብዥታም አይኑርባችሁ፡፡ በጀግኖቹ የአማራ ልዩ ሀይል (ነፍጠኞች) በየአውደ ውጊያዎቹ ቆራጥና አኩሪ ፍልሚያ የተሽመደመደው የወያኔ ጦር ከግስጋሴው በወሳኝነት ከተገታ በኋላ ፈጥኖና መልሶ በተደራጀው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላያንሰራራ ድባቅ ተመትቷል፡፡ይህ ሁሉ በመገባደድ ላይ እያለ አሁን ላይ የሚቀር አንድ ታላቅ አገራዊ ጉዳይ በእንጥልጥል ላይ አለ፡፡ይህም የአገሪቱ ፖለቲካ ከእንግዲህ ወዴት የሚለው ነው፡፡ለዚሁ አብይ ጉዳይ ጠ/ሚ/ሩ የቀሩት ሁለት ተጻራሪ አማራጮች ብቻ ናቸው፡፡ሌሎች ማጭበርበሪያ ካርዶች ከወያኔ ጋር ተቀብረዋል፡፡

    አማራጭ አንድ፦ ለአገሪቱ ይህንን ሁሉ ውድቀት ያመጣባት መሰረታዊ ችግር በዘር ላይ የተመሰረተው የደደቢት ህገ መንግስት መሆኑን በማመን ይህንን ህገመንግስት ዛሬዉኑ ማገድና በምትኩም በዘር ላይ ያልተማከለ ፌደራላዊ ህገመንግስትን በቶሎ ተግባራዊ ማድረግ፡፡ ከዚያም የወያኔ ታናሽ ወንድም የሆነውን ኦነግን በኦነግ ሸኔ ስም ለመቀባባት ከመሞከር ይልቅ ህወሀትንና ራሱን ኦነግን በአሸባሪ ድርጅትነት መዝግቦ ከፖለቲካ እንቅስቃሴ ማገድ፡፡የተረኛውን የኦሮሙማ አስተሳሰብንና አደረጃጀትንም ሆነ ሌሎች በአገሪቱ ውስጥ በዘር ላይ የተመረኮዘ አስተሳስብ/አደረጃጀት የሚያራምዱትን በሙሉ ድርጊቱን በወንጀል ተግባር ፈርጆ በህግ እንዲታገዱ ማድረግ፡፡

    አማራጭ ሁለት፦አሁን ያለዉን በዘር ላይ የተዋቀረ ህገ መንግስትን ማስቀጠልና በተረኝነትም የመሪነት ቦታ ላይ ያለው የኦሮሙማ ፖለቲካ አገሪቱን ወደ ማትወጣው አዘቅት ይዟት እንዲወድቅ መፍቀድ፡፡ አማራጭ አንድ የሚበጅ፡ የሚፈለግ፡ ለአገሪቱ በሽታዎች ሁሉ ፈውስን የያዘ ብቸኛ አማራጭ ነው፡፡ በአማራጭ ሁለት ከተሄደ ግን አሁን በመፍረስ ጠርዝ ላይ የምትገኘው አገራችን እንደአገር መቀጠል ስለማትችል ትፈራርሳለች፡፤ የእርስ በእርስ ጦርነቱም የሰው ልጅ በታሪክ አይቶት ያማያውቅ ዘግናኝ ይሆናል፡፡ በውጤቱም ማንም አይጠቀምም ብቻ ሳይሆን ማንም በሰላም ሊኖር አይችልም፡፡

    ከሁለቱ ውጭ ሌላ አማራጭ በመሀል የለም፡፡ ህዝቡ የሚሻለውን ያውቃል፡፤ የመሪነቱን ቦታ የያዙት ዶ/ር አብይም የሚጥማቸውን እራሳቸው ያውቃሉ፡፡

  9. አልወሃ ምላሽ

    “ከትግራይ የተወሰዱ ግዛቶች ናቸዉ – – – ” እየተባለ ሲነገር ነበር የምንሰማዉ። የተወሰኑት ወደ የበጌምድር፡ የተወሰኑት ደግሞ ወደ ወሎ ጠቅላይ ግዛት – – ። ግን ለምን? ለዚህ መልሱ ትግራይን ወይም የትግራይ ገዢዎችን ለመቅጣት የሚል ነዉ መልሱ።
    ወደ ኋላ ተመልሰህ የሆነዉን በደንብ ማወቅ የሚያስፈልግ ቢሆንም – – ራያ፡ ወልቃይት – – የተባሉት ግን በርስትነት ካልታዩ በስተቀር፡ የማን ናቸዉ? ተብሎ ወደ ጭቅጭቅና ግጭት የሚያስገቡ መሆን የለባቸዉም። ዞሮ ዞሮ በነዚህ ቦታዎች ህዝብ ነዉ የሚኖረዉና።
    አንድ ቀን ወደ አዲስ አበባ ስሄድ “እስከዚህ ነበር የትግራይ ግዛት – – – ” አበረዉኝ አዉቶባስ ዉስጥ የነበሩ ሽማግሌ በእጃቸዉ እያመለከቱ አሳዩኝ። ቦታዉ አልዉሃ – – አልዉሃየ – – የሚባለዉ ነበር።
    የትግራይ ክልል ከተመሰረተ በኋላ በየቦታዉ ለስራ ስዘዋወር ነበር። ከዳንሻ ጀመሮ እስከ ሁመራ። ከባድመ ጀምሮ እስከ ጨርጨር፡ ባላ፡ አላማጣ። ማይጸምሪ፡ እምባማድረ፡ እስከ ሽሬ። ዓዲ ረመጽ – – እንዲህ እንዲህ ብሎ በትግራይ ክልል ዉስጥ በስራ ያልተንቀሳቀስኩበትና ያላየሁት ቦታ ብዙም አይደለም።
    ከማይጸምሪ ቀጥሎ ያለዉ ዓዲ አርቃይ ወደ ክልል አማራ ገብቷ። ከዋጃ ወድያ ያለዉም እንዲሁ። ይህ አከላለል ግን ከግምት ያስገባዉ ምንድ ነበር? ብየ ሁሌም እራሴን እጠይቃሎህ።
    አላማጣ ከተማ ለስራ ተጉዘን የከተማዉ “ኮረፌ” ለመቅመስ ከገበያ አከባቢ ተቀምጠን ሳለ ተራራዎቹን ወርደዉ ለገበያ የመጡ ከአጠገባችን ቁጭ ብለዉ ኮረፌ የሚጠጡ የራያ ባላገሮች የሚናገሩትን አዳምጥ ነበር። ቋንቋዉ ትግርኛ ነዉ። ያስገረመኝ እሱ ነበር። ሆኖም አላማጣ ከተማ አማርኛ ይሰማል። ከገጥር ያለዉ ህዝብ ግን ትግርኛ ተናጋሪ ነዉ።
    እርግጥ ነዉ ከመሆኒ ወድያ፡ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ኦሮምኛ ተናገሪ ይገኛሉ። እነዚህም በትግራይና የኦሮሞ ጎሳ ተስፋፊዎች በተደረገዉ ዉግያ ወደ ትግራይ ዘልቀዉ እንዳይገቡ የተገደቡ ህዝቦች ቅሪት ናቸዉ። አላማጣ ከተማ ዉስጥ፡ ከአገዉ ምድር – – ከሰቆጣ አከባቢ የመጡ ሰዎች ታገኛለህ። የአለማጣ ነዋሪዎች የተለያዩ አከባቢዎች ስብስቦች ናቸዉ። አንዳንዶቹም የአማርኛና ትግርኛ ቃላቶች አዳቅለዉ ይናገራሉ። አብዛኛዉ ለማለት “አብዘሓኝኡ” ይላሉ። አላማጣና ኮረም ከተሞች አማርኛ ቢሰማ ተንቀሳቅሰዉ በሰፈሩ ሰዎች ምክንያት እንጂ ሌላ አይሆንም። ከኮረም ወደ አላማጣ ማዉጫ ላይ “ሜዳ ሓያሎ – – – ” የሚሉ የትግርኛ ስሞች ታገኛለህ። ወደ ጎንደር ወገን ደግሞ እንደነ ዓዲ አርቃይ የተሰኙት አሉ። እናም ይህ ነገር ህዝቡ ማን ነበር? የሚለዉ እንድትጠይቅ ያስገድዳል።
    በጣልያን ወረራ የተነሱ ቪዲዮዎች እስከ ደባርቅ አከባቢ የነበረዉ ህዝብ በትግርኛ ሲዘፍንና እስክስታዉን ሲያወርደዉ ይሳያሉ። ይህም ያ- ህዝብ የወለዳቸዉ በግዜ ሂደት አማርኛ ተናገሪ ሆነዉ ቀርተዋል ወይ? እንድትል ያደርጋል። እንግድያዉ የትግራይ ህዝብ አሰፋፈርና ይዞታ ወደ ኋላ ተሂዶ መመርመርና መወቅ ያስፈልጋል፡ እነዚህ ቦታዎች የማን ናቸዉ ብሎ ክርክርና ጭቅጭቅ ዉስጥ የሚገባ ከሆነ።
    በ27 አመት የኢህአዴግ አገዛዝ ወደ ዳንሻ፡ ሑመራ፡ ማይካድራ፡ ሽሬ እስከ መቀሌ – – – ከጎንደርና ሩቅ የኢትዮጵያ አከባቢዎች የመጡ ሰዎች በብዛት መጥተዋል። በተጨማሪም መቀሌና ሌሎች የትግራይ ከተሞች ዉስጥ ሳይቀር የወጣቱ ቋንቋ አማርኛ ሆኖ ነበር። መቀሌ ከታክሲ ዉስጥ በሞባይል ቴሌፎን ሲናገሩ የምሰማቸዉ ወጣቶች ድንገት ትግርኛ ሲደባልቁ ነዉ የትግራይ ተወላጆች መሆናቸዉ የምገነዘበዉ። አማርኛዉን ተክነዉበታል። አዲስባ የሚኖረዉ ጓደኛየ ስለዚሁ ስናወራ “ወደ አፋርና ሶማልያ አከባቢዎች ሁሉ ተንቀሳቅሻሎህ። ወጣቱ በአማርኛ ነዉ የሚያወራዉ” ሲለኝ “እንግድያዉ የአማርኛ ድራማዎችና ሙዚቃዎች ተጽእኖ ውጤት ይሆናል – – ” ብለን ደምድመናል።
    የቋንቋ ክልሎች ቢፈጠሩም ህዝብ ከሌላዉ ከቋንቋ ጋራ ምንም ችግር የለዉም። አከላለሉ ዘረኝነት አላስፋፋም። ፖለቲካ ሲጨመርበት ነዉ ችግር የሚሆነዉ። ዋናዉ ነገር፡ የሚካለሉ ቦታዎች ለአንድ ክልል ህዝብ ታሪክ፡ ቋንቋና ባህል – – መብትና ፍላጎት፡ እንዲሁም የኢኮኖሚ ብልጽግና ወሳኝነት እንዲኖራቸዉ ይገባል። በርስትነት ከታየ ግን እነዚህ እሴቶች ዋጋቸዉ ይጠፋል። ዉጤቱም ግጭትና አለመረጋገት ሆኖ ይቀጥላል።

  10. አላማጣ ነዋሪዎች ማን ናቸዉ?

    የአላማጣ ነዋሪዎች ከትግራይ፡ አማራ ክልል ወይም እራሳቸዉን ችለዉ ዞን እንዲሆኑ ያላቸዉን ሃሳብ ለማወቅ የብልጽግና ሰዎች አነጋገሩዋቸዉ የሚል ወሬ በዜና እየሰማን ነዉ።
    የአላማጣ ነዋሪዎች ከአገዉ ምድር፡ ከወሎ አከባቢና ከተለያዩ የተቀሩት የትግራይ አከባቢ መጥተዉ የሰፈሩባት ከተማ ናት። እናም እነዚህን ነዋሪዎች ነዉ ሃሳባቸዉን እንዲሰጡ እየተጠየቁ ያለዉ? ወያስ ሌላ ነዉ እየሆነ ያለዉ?
    ነገር ግን ዙርያዉን እስከ መሆኒ ያለዉ ህዝብ፡ አላማጣ ከተማቸዉ አይደለችም እንዴ? መጠየቅ ካለበት እንድያዉም ዋና ከተማችን – – የሚላት እስከ ኮረም ያላዉ፡ እስከ መሆኒና ማይጨዉ ያለዉ፡ እስከ ባላና ጨርጨር ያለዉ፡ እስከ ዋጃና ቆቦ ያለዉና በተለይ ዙርያዉን በገጠር ለረጅም አመታት የኖረዉ የራያ ህዝብ ነዉ።
    አለማጣ ዉስጥ የከተመዉን፡ አብዛኛዉ መጤ የሆነዉን ለይቶ ሃሳብ መጠይቅ ግን ትርጉሙ ምንድን ነዉ?

  11. ተወዳጅዋ የአባይ ሜድያዋ ሮዛ መሀመድ የሰራችው ስህተት

    ህዳር 26 ቀን 2013 ዓ.ም ( January 4, 2021) አባይ ሜድያ እንግዳችን – “በትግራይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመ ነው” – በሚል ርእስ ክብሮም በርሀ ከተባለና ወያኔ ጠፍጥፎ ከሰራው ባይቶና ከሚባል የወያኔ ተለጣፊ ድርጅት የመጣ ግለሰብ ጋር ያደረገችውን ውይይት በአንክሮ ተመልክቸዋለሁ፡፡

    https://www.youtube.com/watch?v=i-sZn8_ozus&t=1616s

    በአጠቃላይ ውይይቱ በባይቶና በኩል በቂ የወንጀለኝነት ሽፋንን በሰፊ የፕሮፓጋንዳ ስራ ለመሸፈን ዝግጅት ተደርጎበትና መድረኩንም እንደጦር ሜዳ ቅስቀሳ ለመጠቀም ታስቦ የተለመደ የወያኔን ጀብደኝነት በይፋ ለማሰራጨት የቀረበ ሲሆን ከጋዜጠኛዋ መአዛ ሞሃመድ በኩል ግን በቂ ዝግጅት ሳይደረግበት እንደመደበኛ ውይይት ታስቦ የቀረበ ነበር፡፡በአጭሩ ውይይቱ መካሄድ የማይገባው የነበረ ሲሆን ከተጀመረ በኋላም ቢሆን ግለሰቡ በንግግሩ ከሚረጫቸው መርዞች በመነሳት ተልእኮው ከመደበኛ ውይይት ውጭ መሆኑ ታምኖበት በአዘጋጇ ወዲያዉኑ መቋረጥ ነበረበት ፡፡

    ሮዛ ፦ የሰራሽው ስህተት ነው፡፤ ለምን የደብረጽዮንን ረዳት ወይንም የጌታቸው ረዳን ምክትል ለመሆን የሚንጠራራን ሰው አምጥተሽ ታስጨፍሪብናለሽ? ይህ ሰው ለህግ መቅረብ እንጅ ለነጻ ውይይት በእናንተ ሜዲያ ላይ መቅረብ ፈጽሞ አልነበረበትም፡፡ መቅረብ ከፈለገም መቅረብ የነበረበት በእነ አሉላ ሰሎሞን የወያኔ ሜዲያ እንጅ የህዝብ በሆነው የአባይ ሜዲያ ላይ በፍጹም መሆን አልነበረበትም፡፡ምክንያቱም ሰውየው እንደ ሰፊው ምህዳር በመሳሰሉ መድረኮች ላይ ሰፍ እያለ በመቅረብ በጸረ ኢትዮጵያ አቋሙ ከበፊት ጀምሮ ይታወቃልና፡፡ወያኔዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ከዘረፉት በትሪሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ውስጥ እናንተንም ከፈሏችሁ እንዴ ለማለት አንደፍርም፡፡ አባይ ሜዲያን ጠንቅቀን እናውቀዋለንና፡፡ ስህተት ግን ተሰርቷል፡፡ የተጠቀመበትን የተረሳና ያረጀ ወያኔያዊ የቅስቀሳ ስትራቴጅ ስናየው ግን አዝነናል፡፡ሰውየው የሚያስበው እንደከብት ነው፡፤ ወያኔ ደደቢት ዋሻ ውስጥ ያሰረው ፍየልን ይመስል የማያውቀው ጉዳይ ውስጥ ሁሉ እየገባ ይጮሀል፡፡ ከጩሀቱ አልፎ ተርፎም አሉላ ሰሎሞን ዋሽንግተን ዲሲ ቁጭ ብሎ እንዳናፋው ሁሉ ሰውየሽም አንቺው ጎን ቁጭ ብሎ ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ብሎሻል፡፡ ወደፊት ይለይልናል ብሎ ዝቷልም፡፡ በአገሪቱ ብሄራዊ ጦር ላይ ወያኔ “መብረቃዊ ጥቃት” ብሎ ስለሚመጻደቅበትና በጨለማ፡ ያልታጠቁ አስር ሽህ ወታደሮች ስለመታረድ ጉዳይ ስትጠይቂው እርሱ የሚያሳስበኝ ነገር አይደለም ብሎሻል፡፡በወያኔ ቆስቋሽነት በትግራይ ውስጥ በአሁኑ ሰአት ጦርነተ እየተካሄደ መሆኑን በመዘንጋቱና ማንኛውም አይነት ጦርነት አያሌ አፍራሽ ክስተቶችን እንደሚያስከትሉ ባለማገናዘቡ እርሱን የሚያሳስበው “ስለትግራይ ገበሬዎች ሰብል አለመሰብሰብ ችግር፡ የሚበሉት ስላጡ የትግራይ ህጻናት ችግር ፡በጦርነቱ ስለተገደሉ የትግራይ ሰዎች ችግር በጦርነቱ ምክንያት ስለተፈጠረው መፈናቀል” ወዘተ ነው ሲል በግልጽ ያለሐፍረት መልሶልሻል፡፡ ላቀረብሽለት መሰረታዊ ጥያቄሽ ዙሪያ ያወራልሽ የራሱን የተዘጋጀበትን የቅስቀሳ አጀንዳ እንጅ ጥያቄሽን አልመለሰልሽም፡፤ አንቺም ጥያቄየን አልመለስክልኝምና “ጥያቄወቼን መልስ ስጥባቸው” ብለሽ ደግመሽ አልጠየቅሽውም፤፡ በማይካድራም ከሽህ ባላይ አማራወች በመታወቂያቸው ተመርጠው በወያኔ ስለመታረዳቸው ስትጠይቂው በድጋሜ “እኔ የሚያሳስበኝ ስለ አንድ ማይካድራ ሳይሆን ስለትግራይ ነው” ብሎ ነው የመለሰልሽ፡፡ እንደገና ቪድዮሽን ሄደሽ ተመልከችው፡፡ ስለዚህ እኔ አንቺን ብሆን ኖሮ ቢሮዬ ጠርቸ የማነጋግረው ሰው ይህንን ያህል እብሪት፡ ቅጥፈትና ዛቻ የተሞላበት ነገር ሲናገረኝ ከቢሮየ አስወጥቼ በማባረር ፖሊስ ለህግ እንዲያቀርበው በሙሉ በቪዲዮው ላይ የዘላበደውን ለፖሊስ አስረክብ ነበር፡፡ አንቺ ግን አስችሎሽ ብቻ ሳይሆን በሚገባ ሳትዘጋጅ በውይይቱ ቀጥለሽበትና ስድብና ዛቻ ጠጣሽ፡፡(የሚሰማሽ ከሆነ ነው)፡፡

    ወያኔ 27 አመት ሙሉ የፈጃቸውን የሰዎች ብዛትና ሌሎች ስፍር ቁጥር የሌላቸው ከባባድ ወንጀሎችን ለአሁኑ ብቻ ወደ ጎን እንተወው እንበል፡፡ ትናንትና በ10ሽዎች የሚቆጠሩ የአገሪቱ ወታደሮች በወያኔው ጁንታ በአሰቃቂነቱ ወደር በማይገኝለት ጭካኔ ሲታረዱ ምንም ያላለው የባይቶና ታጋይ ታራጆቹ ኢትዮጵያዊያን እንዳልሆኑ ሁሉ ቅንጣት የመቆርቆር ስሜት ለይስሙላ እንኳን አላሳየም፡፡ በማይካድራ በመታወቂያ እየተለዩ አማራወች ሲታረዱ ስለአራጆቹ ወንጀለኝነት አንዲት ቃል አልተነፈሰም፡፡ መአዛ፦ ሰውየሽኮ የወያኔ መሪዎች አንቱ የተባሉ ታላላቅ ሰወች ያሉበት ድርጅት መሆኑን አሁንም በኩራት እየነገረሽ ነው፡፡ የዛሬ አመት (Jan.23,2020) በአውሎ የወያኔ ሜዲያ ላይ ቀርቦ ስለስርአቱ የተናገረው ከህወሀት ጋር የጠበቀ ቁርኝቱን በገሀድ ያሳያል፡፤ “ ህወሀት የተላጠ የኤለክትሪክ ገመድ ነው፡፡ በእሱ ትግራይን እናጥርበታለን” ብሎ ነው የተናገረው፡፤ በሌላ በኩል ደግሞ ይሄው ሰውየሽ የሚለውኮ ንብረት ብቻ ሳይሆን የትግራይ መሬትም ተወስዷል ብሎ ነው የሚጮህብሽ፡፤ ያው ጀግኖቹ አማራዎች በደማቸው ያስመለሱትን ወልቃይት፡ ጠለምት፡ ጠገዴና ራያ መሆኑን ይመስላል፡፡እነዚህን የአማራ የደም መሬቶች ለማስመለስ ለምን ራሱ ሄዶ አይዋጋም?? ባዲሜንማ ታላላቅ ወንድሞቹ መለስ ዜናዊና ስዩም መስፍን አለም እያዬ ፍርድ ቤት ቀርበው ፈርመው አስረክበዋታል፡፡ መአዛዬ ፦ ሰውየሽ ከጎንሽ ቁጭ ብሎ እትዮጵያዊ አይደለሁም ሲል ውይይቱን ወዲያዉኑ ማቋረጥ ሲገባሽ ከሚገባው በላይ ልቅ አድርገሽ ካለልክ እንዲያጓራ አደረግሽው፡፡ ያውም እርሱ ራሱ ሊናገረው በሚጠላው አማርኛ ቋንቋ የሞተውን ወያኔ ነፍስ ሊዘራበት የቻለውን ያህል ቅስቀሳም ሊሰራ ሞክሯል፡፡

    የሚያደምጡት ቢኖሩም የሚያምኑት ግን ያው የወያኔ ምናምኖች እንጅ ኢትዮጵያዊ የሆንን ሁሉ ከወያኔና ከርዝራዦቹ እንድወራረድልን የምንፈልገውና የምንጠብቀው ገና ሀ ብሎ ጀመረ፡፡ የሚወራረድ ገና ብዙ ሂሳብ አለ፡፤ በጣም ብዙ፡፡ በመጨረሻም አንቺ ምናልባትም ይህንን ባለማወቅ እንደሰራሽው “እኛ” ብናምንም ከቅሬታችን ጋር በርቺ ልንልሽ እንወዳለን !!

  12. የውጭም የውስጥም የኢትዮጵያ ጠላቶች ሆይ፦እባካችሁ እነዚህን ሁለት ሀቆች አጢኑ !!!
    ሀቅ ቁጥር አንድ፦
    በትግራይ ውስጥ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ቢያሳዝንም ይህ የሆነው ግን ከሁሉም በፊት ወያኔ በፈጸመው ታሪካዊ ስህተትና አረመኔያዊ ጭካኔ ነው፡፤ በተለይ የኢትዮጵያ መደበኛ ሰራዊት በዘር ተለይቶ መታረዱ ያንገሸገሸው ከኦነግና ወያኔ ደጋፊዎች ውጭ ያለው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የመንግስትን አቁዋም ይደግፋል፡፤ እንዳውም መንግስት በቶሎ ወሳኝ እርምጃ ባለመውሰዱ ህዝቡ ቅሬታ አለው፡፡ ወያኔ የሰራው ህልቆ መሳፍርት የሌለው ወንጀል ገና ብዙ ማወራረዶችን ይጠብቃል፡፡ ይህ እውነታ እንዳለ ሆኖ በመሬት ላይ ካለው ሀቅ ውጭ ያለው የወያኔ ጥቅመኞች አለም አቀፍ ጸረ ኢትዮጵያ ቅስቀሳና ጫጫታችሁ የሚቀይረው ቤዛ ቤስቲን የለም፡፡ የተቋረጠባችሁም የዘረፋ ገንዘብ አይመለስም፡፡ በሩ ተዘግቷል፡፡ ወላ ሀንቲ!!! እስከመጨረሻው ርቀት ድረስ ተሂዶ ወያኔ ገና ይጠራረጋል፡፡የወያኔ ርዝራዦች ሆይ፦ ይልቁንስ አሁን ያላችሁበትን ሁኔታ ሊገልጽ የሚችለውን የመርዝ ብልቃጡን የመለስን <> ዘፈን በሙዚቃ አጅባችሁ አዳምጡት፡፡ DJ አሉላ ቢሆን ይመረጣል፡፡ አድማጮችም ከስብሀት ጀምሮ ወደታች በደረጃ !!!
    ሀቅ ቁጥር ሁለት፦
    ከሞተው ወያኔ ውርጃ ጋር ተያይዞ የጨነገፈው ኦሮሙማ በዘረፋ በዘረኝነትና በዘግናኝ የጭፍጨፋ ስራዎቹ ከወያኔ የባሰ ነው፡፤ በታሪክም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ጸረ ኢትዮጵያ ስብስብ ነው፡፡ በህዝቦች ጭፍጨፋና በአገር መዋረድ ላይ ያስከተለው ጠባሳ ምንጊዜም አይሽርም፡፡ መፍትሄውም በቶሎ ተደራጅቶ ስብስቡን ማስወገድና እንደውራጁ ወያኔ አርቆ መቅበር ብቻ ነው፡፡

  13. ይድረስ “ያሻግሩናል” ላላችሁና ከመናቆር ላልወጣችሁ
    ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን!!!
    ጌድዮን በቀለ
    አርሊንግተን ቨርጂንያ ፌብሯሪ 2/2021
    “ሰባተኛው ንጉስ” አብይ አህመድ ትንቢቱ ሳይፈጸም፤ ገና ዙፋናቸው ሳይረጋ ፤ማንም “በጉልበት” ሳይነካቸውና ሳይነቀንቃቸው ፤ በዚህ ፍጥነት ፤በገዛ ራሳቸው አልጋቸውን ነቅንቀው ሊገለብጡት ቆርጠው መነሳታቸውን ያሳዩናል የሚል ግምት አልነበረኝም። በዚህ ፍጥነትም ከኔ ወዲያ ላሳር በሚል ማን አህሎኝነት ትዕቢት ተወጥረው “ተገዳዳሪዬ፤ ተፎካካሪዬ” እያሉ ሲያንቆለጳጵሷቸው የነበሩ ተገዳዳሪዎቻቸውን ዝቅ አርጎ በማየት አባዜ ይወጠራሉም ብዬ አልገመትኩም ነበር። ባደባባይ ሲያሰሙን ከነበረው ጆሮአችንን እንዲጥመው አድርገው ካወረዱልን ቃላት አንጻር “ያሉትን ይኖሩታል” ብዬ ብቀበልና ብጠብቅ አይፈረድብኝም፤ ምክንያቱም እኔ የማወቃት ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊ ከነተረቱ “የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ” ሲል የኖረ ፤ቢያንስ ቢያንስ ባደባባይ ለተናገረው ቃሉ ሲል አንድያ ህይወቱን ከመስጠት የማይመለስ ለቃሉ የታመነ መሆኑን ስለማውቅ።
    ይሁንና ባለተስፋው “ሰባተኛ ንጉሥ” እኛ ከምናውቀው ኢትዮጵያዊ ተክለ-ሰብዕና በተቃራኒው ወርደው ሲገኙና፤ በዚች አጭር የስልጣን ዘመናቸው ከፈጸሙት ይቅርታ የማይገባው “የመርህ-አልባነትና ፤ተአማኒነት” ችግር ባለፈ፤ ለሰሞኑ የኦሮምያ ሰልፍ የሰጡት ቡራኬ ሰውየው ምን ያህል ራስን በማጥፋት በሽታ መለከፋቸውን የሚያሳይ ነው። በኦሮሚያ ብልጽግና ካድሬዎቻቸው አስተባባሪነት የተመራውና ኦሮምያ የተባለውን ክልል ዋና ማእከሉ ያደረገው ሰልፍ ከሰላማዊነቱ ይልቅ ተንኳሽነቱ በማመዘኑ “መጣንባችሁ”፤ “ አትመጧትም” ወይም ደግሞ “የኛም- የኛ” “ የናንተም- የኛ” የሚል ውስጠ-አግላይ መልእክት በማስተላለፍ የተዋጣለት ሆኖ አልፏል። በውጤቱም ከፊት-ለፊታችን ለተደቀነው አስከፊ የእርግጫ ዘመን ፈር ቀዳጅ መሆኑን አመላክቶናል።
    በዚህ የተነሳ “ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር “ እንዲሉ “ ይሻግሩናል” በማለት እስከዛሬ የሚያጅቧቸው የኔ ቢጤዎችና “በአብይ መጀን” ልክፍት ጭራቸውን ሲቆሉ የከረሙ፤ “ በመደመር” እንቶ ፈንቶ ቁርባን፤ ከባለተራው ዙፋን ስር ወድቀው የሚንከላወሱ፤ “የአብያችን” ዘማሪዎች በድርጊቱ አንገታቸውን ካልደፉ ስለጤንነታቸው የምንጠይቅበት ጊዜው አሁን ነው።
    ላለፉት 29 አመታት በጠመንጃ አሸንፌአለሁ ባለ ወንበዴ ቡድን መሪነት ዘጠኝ ትናንሽ ቦታ የሰባበራትን አገር፤ የሞት ማተቧን ውል በህገመንግስት ደንግጎ ፤ በሰደፍ ረገጦ ትንፋሽ እስኪያጥረን ሲገዛን ከርሞ፤ የፈጠረቀበት ክንዱ ሲዝል ፤ የመግዛት አቅሙ ሲዳከምና ጨርሶም ከወንበሩ ሲባረር፤ አበሳችን ያለቀለት መስሎን ነበር።
    የተጠበቀው ቀርቶ በስፍራው” የለውጥ ካባ” ያጠለቁት “ብልጽግና “ በሚባል የክርስትና ስም ብቅ ያሉት “ኢህአዴግ ቁጥር ሁለቶች” ወይም የኢትዮ 360ው ኤርምያስ ለገሰ እንደሚጠራቸው “ኢህአዴግ ሲቀነስ ተሃህት ፤ሲደመር አጋር ፓርቲዎች(ሶማሌ፤አፋር፤ጋምቤላ፤ ቤን ሻንጉል)” ወይም “ኦዴፓ-ብልጽግና” ስብስቦች፤ የፈጣሪያቸው ዎያኔን ያህል ፈጥርቀው የሚይዙበት የጋራ ክንድ ቢያጥጣቸው ቋጥሮ ይዟቸው የነበረውን ጠመንጃ አዳክመው በየጎጣቸው ባደነደኑት ክንድ ፤ከእንካ ስላንቴ እስከ ትከሻ መለካካት ተሸጋግረው ፤ለሽህዎች አመታት የኖረችውን ህልው ኢትዮጵያ ልኬታው በውል ወደማይገመት እልፍ ትናንሽነት ለመቀየር ይሆነኝ ብለው የተነሱ፤ በራሳቸው ህልውና ላይ የዘመቱ ራስ-ጠል ቡድኖች ስብስብ እጅ መውደቃችንን በዚህ ሰልፍ አረጋግጠውልናል። “አገር ሲያረጅ ጃርት ያበቅላል ይሏል “ ይሄው ነው።
    ቀድሞውንም ኢትዮጵያን በሰባራ-ሰላላ ድልድይ ላይ አቁሞ “ ያዝኩሽ-ጣልኩሽ” እያለ አንቀጥቅጦ የገዛት ዎያኔ -ኢህአዴግ፤ ራሱ በሰራው የጎጥ ፈንጅ፤ የቆመበት ውሽልሽል ድልድይ ሲደረመስ፤ እንዳይመለስ ሆኖ ከመፍለስና ከመደምሰስ፤ አላመለጠም። ተሃህትን የሰሩት ሰዎቹ ቢገፈተሩም፤ ቡድኑ ዘርቶት የሄደው አምካኝና በፈጠራ ትርክት ላይ የተተከለው ስርአት ተሸካሚዎች እንደ አሜባ ተባዝተው በተረኛነት ስሜት የመጠፋፋቱን ዘመቻ አስፋፍተውና አጠናክረው ቀጥለዋል። በዚህም የተነሳ ተሃህትን ያጠፋውን መርዝ ተግተው ራሳቸውን ጨምሮ ያመነባቸውን ህዝብ ሳይቀር እጅግ ወደላቀው ጥልቅ አዘቅት ይዘውት ለመውረድ እየተንደፋደፉ ይገኛሉ; ፡
    የሰሞኑ ሰልፍ ቅርጽና ይዘት በዋነኛነት ተፈጣሪዎቹ ከሟች ዎያኔ ያስቀሩት የመጥፊያ ቅርሶች አንደኛው እንደሆነ የመጀመሪያ ማረጋገጫችን ነው። ይህንን እጅግ አደገኛና አፍራሽ ሰልፍ ያቀናበሩና የመሩ የኦዴፓ ካድሬዎችና መንግስት ፤ አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ከማንም በላይ በራሳቸውና እንመራዋለን ወይም እንወክለዋለን በሚሉት ህዝብ ላይ የጥፋት አዋጅ ማወጃቸውን ከእብሪትና፤ ማናለብኝነት የተረፈ ጆሮና ልቦና ካላቸው ቆም ብለው እንዲመረምሩት የሚከተለውን እላለሁ፤
    ሀ- የያዛችሁት መንግስት የናንተ ነው፤ አገሩ ቢፈርስና፤ ቢናድ፤ እጅግ ቢያንስ የምትፎክሩበት፤ የምታዋርዱትና፤ የምትሳለቁበት ህዝብ አይኖራችሁም
    ለ- ገፍታችሁ ገፍታችሁ አገሩን ካፈርሳችሁት፤ እንኳን የምትሳደቡበት፤ የምትቆሙበት የእግር መርገጫ መሬት አይኖራችሁም፤ ኢትዮጵያ ስትፈርስ እንደምታልሙት ዘጠኝ ወይም አስር ትናንሽ አገር ተፈጥሮ የድርሻችሁን ይዛችሁ የምትፈረጥጡ እንዳይመስላችሁ። እሱ “ሱሚ ነው” ያኔ የምትጓጉላት “ኦሮሚያ’፤ “አማራ”፤ “ዎላኢታ”፤ “ትግሬ” “ሶማሌ” ቤንሻንጉል” ምንትስዮ ብሎ ነገር አይኖርም። አይድረስ እንጅ ከደረሰ “እንደ ይጎዝላቪያ” መሆን ምንኛ የጽድቅ ያክል፤ የመባረክና የሚመኙት የቅንጦት ጥያቄ እንደሚሆን አንድ አፍታ እንኳ ትንፋሽ ወስዳችሁ አስቡት ፤
    ሐ. ከዚህ ወዲያ ተከባብረንና ተቻችለን ለሁላችን የምትስማማ አገር ተመካክረን ማቆም ከተሳነን፤ ከባለጊዜነት አዙሪት ወጥታችሁ፤ የመንግስት ስልጣን ይዛችሁም፤ ባንኩንም፤ታንኩንም፤ ያለገደብ አግበስብሳችሁም፤ እንደተራበ ህጻን በተበዳይነት ስነልቦና እያለቃቀሳችሁና እያስፈራራችሁ “ በኬኛ” ድርቅና ስነልቡና እንገፋበታለን ካላችሁ ፤ ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ገና ግባተ መሬቱ ያልተጠናቀቀውን ፈጣሪያችሁን ወያኔን ለመጠየቅ ቅሊንጦ በጃችሁ ነው ሊባሉ ይገባል(ይሄ አባባል በተረኛነት ስሜት የተለከፉትን ቡድኖች እንጅ የኦሮሞንም ሆነ የሌላውን ማህበረሰብ በፍጹም አይጨምርም)
    በምርጫ ያልተገነባችው ኢትዮጵያ፤ከምርጫ የምታገኘው ርባና ያለው መፍትሄ ስራይ ሊኖራት አይችልም። ምክንያቱም አስቀድሞ ውጤቱን በሚያመላክቱ የዋዜማ መርዶዎች መዳረሻውን እያየነው ስለሆነ ። ምርጫ ቦርድም ሆነ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የጨዋታው ህግ እንዳይኮላሽ በቁርጠኝነትና በህግ ካላስቆሙት በስተቀር፤ ውጤቱ እንዘጭ፤ እንቦጭ ከመሆን አያልፍም።
    ያገራችን ዋነኛ በሽታ በጥልቁ ስር እየሰደደ የሄደውና በህግ ሽፋን-በግድ እንዲቀጥል መንግስታዊ ቡራኬ የተሰጠው የባለጊዜ ፖለቲካችን ነውና ፤ በዶ/ር አብይ አፍ የምትሰማዋ ኢትዮጵያ በተግባር እየሰሯት ካለችው ኢትዮጵያ ጋር መጋጨቷን ማስቆም ካልተቻለ፤ ሁሉንም ዜጎቿን ፤በፍቅር፤በአንድነትና በእኩልነት ከማኖር ይልቅ ፤ በተግባር ‘ዘር-ዘር” እየተጫወቱ ያዩትን ሁሉ በመሰልቀጥ አባዜ ተለክፈው ለሚክለፈለፉ አባሎቻቸው አደብ እንዲቀሩ ካላስደረጉ “አትፈርስም” በሚል ከማዘነጊያነት ያልዘለለ ፈሊጥ አገር ሆና ልትቀጥል አትችልም፤
    በተቃራኒው ሰርክ የሚያፈራርሳትን የዘረኝነትና፤ ተረኝነት ሴራ አባዝተው እየበተኑ፤ በትረ-መንግስት ጨብጠውም፤ ኢኮኖሚያዊና መህበራዊ ተቋማትን፤ ወታደራዊና የደህንነት ስልጣኑን በጅ አርገው ስለመበደል፤መጭቆንና ተገዥነት እያላዘኑ መቀጠል ፤ “ፍትህ ጎደለብን፤ ህልውናችን አደጋ ላይ ወድቆብናል” ባሉ ሀዝቦች ቁስል ላይ ጨው እየነሰነሱ ያለርህራሄ ቁስላቸውን እያፍረጠረጡ፤ በማስፈራራት መዘባነን ፤ለከፋ ሞትና ውርደት ይዳርግ እንደሆነ እንጅ ያአዲሳቤ አራዳ እንደሚለው ለማስተባበያነት እንኳ አይነፋም።
    ላለፉት ሶስት አመታት “ያሻግሩናል” በሚል ተስፋ፤ አንዴ “ደሞዝ ጠያቂ” ሌላ ጊዜ “መንግስት ገልባጭ” ያሏቸውን የቤተመንግስቱ ወታደሮች ስፖርት አሰርቶ መልስ ጀምሮ እስከትናንትናው “የህግ ማስከበር” ጦርነት ያለሃፍረትና ይሉኝታ የለቀቁበትን፤ ነጭ ውሸት ተሸክሞ፤ ሲያጠፉ ጥፋታቸውን እያለባበሰ፤ ባደባባይ ሲዋሹት “ ሲቀልዱ ነው፤ እንዳይባባስ ለማለዘብ አስበው ነው፤ …” እያለ አፍረታቸውንም፤ ነውራቸውንም፤ ቅሌታቸውንም ተሸክሞ፤ እራሱ እየለበሰ፤ እያቃና ሲደግፋቸው የከረመውን ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሜዳ ላይ አስጥተው ፤ ወደ መረጡትና ቀድሞውንም የኔ ወደሚሉት ክልል መሪነት የወረዱት ጠቅላይ የሁላችንም መሪ ይሁኑልን ሲባሉ፤ የሁላችንም አስተዳዳሪ ለመሆን ለአቅመ ኢትዮጵያ መሪነት ያልደረሱ፤ ከሰፊ አገር መሪነት ይልቅ የመንደር ጎበዝ አለቅነት የሚበልጥባቸው መሆኑን፤ ለሰልፉ በሰጡት ቡራኬ አረጋግጠዋል።
    በዚህ ድርጊታቸው “አዳኛችን መጣ” ብሎ በድፍን ኢትዮጵያ የገጠር መንደሮች ሳይቀር ያለማንም ቆስቋሽ፤ ያለ ውሎአበልና፤ የማባበያ ድጎማና ቲ-ሸርት፤ ባደባባይ ወጥቶ ደስታውን የገለጸላቸውን ፤ኢትዮጵያዊ አንገቱን ጨርሶ እንዲደፋ አስደርገውታል። በሌላ በኩል እሳቸው ዛሬ የመረጡት “ባለ ጊዜነትን ታካኪ አድርጎ” በድጋፍ ስም ወጥቶ ፤ ከቀድሞ ጌቶቹ በወረሰውና በተለመደው ዘለፋ ሲራገም የዋለው “የኦዴፓ-ብልጽግና መራሽ ሰልፈኛ” በአለ-ሲመታቸውን ተከትሎ ከወጣው ሰልፈኛ ጎን ድምጹ አልተሰማም፤ ወይም እዚህ ግባ የሚባል ተሳትፎ አለማድረጉ የሚታወስ ነበር።
    ስለሆነም ሰውየው ያለምንም ማስያዣ፤ እጅግ ባጭር ጊዜ ተስፋውን የጣለባቸውን ስልሳ አምስት በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፍ አሽቀንጥረው ጥለው፤ በገዛ ፈቃዳቸው ከዴሞክራሲያዊነት፤ ወደዘላለማዊ እድሜ ፈጅ መሪነት፤ ከታላቅ አገር አስተዳዳሪነት ወደ ዘውግ -ጎሳ አለቃነት” ዝቅታን ሲመርጡ፤ በመጭው ምርጫ ላይ ሊኖረን የሚችለውን የዴሞክራሲያዊ፤ፍትሃዊና፤ ተአማኒነት ፤ተስፋ፤ አጨልመውታል።
    በዚህ የተንሳ ከወዲሁ እንዲህ ብለን እየቆዘምን እራሳችንን በማነቃቃት እንድንጣራ ተገደድን፤
    “ተነሳ ጓዴ ምራኝ መንገዱን፤
    የጌታችንን፤ “ንጉሣችንን” አየነው ጉዱን” የሚለውን የኖረ የግፏንን እንጉርጉሮ ስንኝ እያንጎራጎርን ፤ ባናቱ ”አሻጋሪያችን አብይ አህመድ” “…ሳሩን እያሳየህ ወደ ገደል ንዳው…” የርካብና መንበር ጭውቴ ፤ እንጨምርበታለን።
    ከሁሉ- ከሁሉ አዲሶቹ ተረኞች የምርጫዋ እንቁልልጭሽ እስክትጀመር እንኳ ትግስት ማጣታቸውና ፤ በኦሮሙማ ስሌት ሊሰለቅጧት ያሰቧትን ኢትዮጵያ እጣ-ፈንታ ገና ከማለዳው ማረጋገጣቸውን ታዝበን የጉባይ እያልን እንጣራለን፤ እናሳስባለን።
    ከዚህ ወዲያ በቃለአባይነት የተካኑት፤ ደግመው ደጋግመው በመዋሸት የሰለጠኑትና ውሸታቸውን በሌላ ውሸት ሲያስተባብሉ ቅንጣት ሃፍረት ወይም ነውር የማይሰማቸው “አሻጋሪያችን” ደግመው ደጋግመው የሚነግሩንን “ኢትዮጵያ አትፈርስም” ቧልት ከምር ቆጥረን ከተዘናጋን የደነቆርነውና በቁም የሞትነው እኛ እንሆናለን።
    እኛ የምናውቃት ኢትዮጵያ ከፈረሰች ውላ አድራለች። ይልቁንስ ያለች መስላ ከ28 አመት በፊት በህግ የፈረሰችና በጠመንጃ ሰንሰለት ተጠፍራ “ በምናልባት!” የቆመች፤ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ነች፤ እውነተኛዋ ኢትዮጵያ ያለችው መፍረሷ ባልተዋጠላቸው ሚሊዮን ዜጎችዋ ልብ ውስጥ ነው። “አትፈርስም” የሚሉን መሪ፤ ሌት ተቀን ጥፋቷን የሚያፋጥነውን ስርአት ሙጥኝ ብለው በያዙበት ፤ የወያኔን ስርአት አቅፈው ደግፈው እያሳደጉ ፤ደብረጽዮንን በሙሉ፤ ሳሞራን በብርሃኑ ጁላ፤ አባይ ጸሃየን በአባ ዱላ፤ ጌታቸው አሰፋን በተመስገን ጥሩነህ.. በመተካት ምላሳቸውን በሆዳቸው እያወጡ ሲያላግጡብን ዝም ካልናቸው፤ እጣ-ፈንታችን እንደጸጉራም በግ፤ አለች ስትባል ተበትናና ተበጣጥሳ ለቁጥር የሚያታክት፤ለያዥ ለገራዥ የሚያስጨንቅ እልፍ ትትንሽ ፍንጥርጣሪነት ስትቀየር ቆሞ ለማየት እንኳ ሳንታደል አብረን ተያይዘን መጥፋት ይሆናል።
    የቀድሞ ጌታውን ፈንግሎ የስልጣን ማማ ላይ ፊጢጥ ያለው የኦዴፓ-ብልጽግና ጌታው በወደቀበት መንገድ ፤ለመጓዝ ቆርጦ መነሳቱን በካድሬዎቹ ትዛዝ ባስወጣው የክተት ሰልፍ አረጋግጦልናል። የሰሞኑ ሰልፍ የምርጫው ፍጻሜ ምን ሊሆን እንደሚችል አመላካች ብቻ ሳይሆን የማንቂያም ደውል ነው። ይሄ ካላባነነንና ካልስደነገጠን እንደሟርት ስንቆጥረው የኖርነው የይጎዝላቪያ እጣ ባገኘነው ብለን የምንጓጓለት፤ ቢገኝ እንደጽድቅ የሚቆጠር፤የሚመኙት እንጅ የማያገኙት እድል እንደሆን የምንረዳበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።
    ከዚህ ሁሉ በፊት ኢትዮጵያ እንድትቀጥልና ሁላችንም የምናተርፈው አገራችን ከዚህ ከተደቀንባት የመበታተን አደጋ ስትተርፍ በቻ ነው የሚል ሙሉ እምነት ያላቸው ወገኖች በረባ ባልረባ፤ በግለሰባዊ ፍላጎት በመሃከላቸው ያለውን የጎንዮሽ መናቆር አቁመው አስቀድሞ አካሂያዱ ሊወሰንለት እያኮበኮበ ባለው ምርጫ እንደ አንድ አዳኝ ሃይል ተቀናጅተው ኦዴፓ-ብልጽግናን ካልመከቱ ለሚደርሰው ማናቸውም ጥፋትና ውርደት ተጠያቂ ከመሆን አያመልጡም። ከጥፋቱ ተርፎ ወሬ ነጋሪ የተገኘ እንደሆነ።

  14. ሠላም የዘሃበሻ አዘጋጅ ሄኖክ _ የካቲት 10 ቀን 2013 ዓ/ም ስለኢሳት ያቀረብከው የሹክሹክታ መረጃ በእወነት ልበልህ በጣም_በጣም አንጀቴን ያራስከው ፥ በዚህም በጣም አመሠግናለሁ ፥ ከ7ዓመታት በላይ ለኢሳት ገንዘቤን ስረጭ ከርሜያለሁ ፥ ይሄ በየወሩ የማዋጣው እንጂ በየድግሱ ለኢሳት እየተባለ የሚዋጣውንማ ቤት ይቁጠረው ፥ ለዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መቀለጃ መሆኑን በፍጹም አላውቅም ነበር ፥ ኢሳት የግንቦት 7 መሆኑንም ያወቅሁት በጣም ዘግይቼ ነበር ፥ ለትግራዩ ፋሽስትና ነፍሰ_ገዳይ ህወሃት ከነበረኝ የመረረ ጥላቻ የምከፍለውን ገንዘብ በፍጹም ክምንም አልቆጥረውም ነበር ፥ በእርግጥ ኢሳት በወቅቱ ትልቅ ሥራ ሠርቶዋል ፥ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በደረሰበት ሁሉ ሸፍጥና ተንኮል እንጂ በፍጹም ቀናነት የሌለው ሰው ነው ፥ ዛሬ የኢሳትን ጉድ ጉልጉል አድርገህ ለኢትዮያውያን በማሳወቅህ በእጅጉ ትልቅ ምሥጋና ይገባሃል ፥ ሄኖክ አንተ እውነትና እውነት ብቻ ተከተል ፥ የእኛ ሀገር መንግሥታት ምን ጊዜም ከሕዝብ ጎን ቆመው ስለማያውቁ የመንግሥትን ፖሮፖጋንዳ አትመናቸው ፥ እውነቱን ብቻ እያወጣህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መረጃ ስጥ ፥ አንተ ከሕዝብ ጋር እውነቱን ተከትለህ የምትሄድ ከሆነ ምንጊዜም ሕዝብ ከአንተ ጋር ነው ፥ በርታ … ሌሎች ለሕዝብ ያልደረሱና መነገር ያለባቸውን ሁሉ ማንንም ሳትፈራ እንደ አየር መንገዱ እያጋለጥህ ለሕዝብ እውነቱን ብቻ አቅርብ ፥ መልካም ጊዜ እመኝልሃለሁ ፥ ኃ/ሚካኤል ከሜሪላንድ አሜሪካ @

  15. በዐቢይ አሕመድ የሚመራው የኦሮሙማ የአፓርታይድ አገዛዝ በኢትዮጵያ ላይ እየፈጸመው ያለው ወረራ!
    ይህን ከታች የምታነቡትን ጉድ ተረኛነት እያላችሁ ተረኛነትን አታቃሉት። ተረኛነት እየተባለ ለሚቀረበው ነገር ማነጻጸሪያ እየሆነ የሚቀርበው ወያኔ ባለተራ በነበረበት ዘመን “የኢትዮጵያ” መከላከያ ሠራዊትን፣ “የኢትዮጵያ” አየር መንገድን፣ “የኢትዮጵያ” ስደተኞች ጉዳይ አስተዳደርን፣ ወዘተ የባንክ ሒሳብ ወደ ትግሬ ባንክ አላዛወረውም። የዐቢይ አሕመድ የአፓርታይድ አገዛዝ የሕወሓትን የነውረኛነት፣ የተረኛነትና የአፓርታይድ ክብረ ወሰን የሰበረው በመንግሥትነት በተሰየመ በአስር ወሩ ነው።
    ይህ ከታች የምታነቡት የዐቢይ አሕመድ የኦሮሙማ የአፓርታይድ አገዛዝ በኢትዮጵያ ላይ እየፈጸመው ያለው ተግባር ጦርነት የሚያስነሳ ወረራ ነው።
    ዐቢይ አሕመድ ይህን ሁሉ ነገር ሲፈጽም የብሔራዊ ባንክ ገዢ ተደርጎ የተጎለተው የብአዴኑ ግዑዝ ይናገር ደሴ እና የጉዳዩ ባለቤቶች የሆኑት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቦርድ አባላት አንዳች የሚያውቁት ነበር የለም።
    ዐቢይ አሕመድ “የአገር መገለጫ ምልክት ነው” ሲለን የነበረውን “የኢትዮጵያ መከላከያ” ንብረት በኦሮሞ እጅ ተጠቃሎ እንዲቀመጥ ያደረገው መከላከያ ተብዮውን ለአንድ ክልል ጥቅም እንዲሰራ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ስም የሚጠራውን መከላከያ ሠራዊት በሚመለከት ከኢትዮጵያዊው ተቋም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በላይ የኦሮሞን ባንክ እንደሚያምን፤ ከኦሮሞ ውጭ ሌላውን ኢትዮጵያዊ እንደማያምን እየነገረን ጭምር ነው።
    ይህ ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ ስም የሚጠራውን የመከላከያ ሠራዊት ንብረት ለኦሮሞ ጥቅም በተቋቋመ ባንክ ውስጥ ተጠቃሎ እንዲቀመጥ በወሰነው ውሳኔና ሕወሓት የሰሜን ዕዝ ተብዮው የትግራይን ጥቅም ሊያስጠብቅ አይችልም ብሎ ሲያስብ በዕዙ ላይ ወረራ ፈጽሙ ጦሩ እንዲበተን ባደረገው ጥቃት መካከል ልዩነት የለም። ሁለቱም ተግባራት የአገር መገለጫ የሚባለውን መከላከያ ሠራዊት አፍርሶ ለአንድ ክልል ጥቅም እጅ የሰጠ ቅልብ ጦር ለማቋቋም ያለሙ ናቸው። please share.
    ▶Achamyeleh Tamiru

  16. ሚሚ እባላለሁ የምኖረው ዊንፔግ ካናዳ ሲሆን በዚህ አካባቢ አዲስ ምግብ ቤት ከባለቤቴ ዘላለም ጋር ሆነን ከፍተናል በዚህ አስከፊ በኮረና ዘመን ጁላይ 2020 ታዲያ ይህንን አስመልክቶ የዊንፔግ ሲቲቪ ና ሲቢሲ የሚባሉ ሚዳዎች ዘግበዋል 2020 established business በሚል ስለዚህ አንተም ከቻልክ እንድታስተዋውቅልን ነው የምጠይቅ ብዙ ግዜ ፕሮግራም ላይ የኢትዩጲያን ምግብ ስለምታበራታ እኛም ይህንን ዕድል ከሰጠከን ብዬ ነው ሁሉንም ዜና ና ፁሁፍ እልክልአለው

  17. ወንድማችን ሰላምህ ይብዛልህ። ከረጅም ግዜ ጀምሬ ነው የምከታተልህ። በጣም ግሩም ስራ ነው የምታቀርበው። ሁሉም እንዳንተና ኢሳት ቢሰሩ በወአአደድኩ ሚዛናዊ የሆነና የእውነት ዜናዎችን የምታምርና የምታዝናና ሹክሹክታዎችን እና ሰበር መረጃዎች ብሎም በአለም ነዋሴ የምታስተላልፈውንም በጣም ነው የምወድልህ። በርታ አንድ ቀን አገርህ ገብተህ የራስህ ጣቢያ ኖሮህ ለመላው ህዝብ ትሰራለህ የሚል ተስፋ ነው ያለኝ። ቸር ሰንብት በርታ። ፈጣሪ ህዝቧንና አግሪቱን አብዝቶ ይባርክ። አንተንና ቤተሰብህን ከክፉ ይጠብቅ።

  18. በሴራ ተሾርቦ የተገመደ ድርድር አያዛልቅም

    ለአማራ ክብር፣ ከአማራው ተዘርፈው ለነበሩ የወልቃይትና ራያ መሬቶቹ ተመልሰው በአማራ ስር እንድተዳደሩ ለማድረግና ይህንኑ በተግባር ለማረጋገጥ፣ በልዩ ሁኔታ ሲዋደቁ ለሞቱ የአማራ ልዩ ሀይልና፣ ለፋኖ አባላት፣ እንደዚሁም ከሌሎች ክልሎችም ዘምተው በግንባር ለተሰለፉ የየክልሎች ህዝባዊ ሀይል አባላት፣ ለጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በሙሉ ታላቅ ክብር አለን፡፡ በማስቀጠልም ለኢትዮጵያችን መቀጠልና ለአገራችን የግዛት አንዲነት መረጋገጥ ከባንዳው ትህነግ ጋር በየግንባሩ ሲዋጉ የወደቁትን ጀግኖቻችንን አርማ አንሰተን ትግሉን እስከ ወሳኝ ድልና የትህነግና የርዝራዦቹ ወደ መቃብር መውረድ መረጋገጥ ድረስ በፍልሚያው በየፈርጁ በሙሉ ልብና ዝግጁነት እንቀጥላለን፡፡

    ትህነግ ነቀርሳ ነው፡፤ ነቀርሳ ደግሞ ተነቅሎ መጣል አለበት፡፡ አለበለዚያ አመርቅዞ ይገድላል፡፡ ስለሆነም በአገራችን ላይ ጥገኛ ትሎች የሆኑት ትህነጎች ሌላ አገግሞና አድብቶ የመነሻ እድል/ጊዜ ሊሰጣቸው አይገባም፡፡ በምንም መመዘኛ ከየትም በሚመጣ የድርድርና የሽምግልና ጥያቄ የመንግስት መልስ መሆን ያለበት እንደሚከተክለው ብቻ ነው፡፤ “መጀመሪያ አሸባሪ ተብሎ በአገሪቱ ሸንጎ የተፈረጀው አሸባሪውና ወንጀለኛው ትህነግ ከድርድር በፊት በቅድሚያ መሳሪያውን አስቀምጦ ወደነበረበት መቀሌ ተመልሶ ለህግ ተገዥ መሆኑን በተግባር ያረጋግጥ ከዚያም በአገሪቱ ህግ መሰረት ሸንጎው ተሰብስቦ ይወስናል” ነው መልሱ መሆን ያለበት፡፡ ይህ ብቻ ነው መሰጠት ያለበት ተገቢው መልስ፡፡እዚህ ላይ የአነ አብርሀም ሊንከንን ታሪክ ያገናዝቧል፡፡

    የመንግስት ብቸኛ መልስ ይህ ካልሆነ ግን የአገራችንን ችግር በተለየ መልኩ ደግሞ የአማራንና የአፋርን ህዝብ መከራ በድብቅ ለማራዘም የሚደረግ የሴራና የሸፍጥ ፖለቲካ መሆኑ ታውቆና ህዝቡም ይህንኑ ተረድቶ እንደማይቀበልውና ወደ አመጽ እንደሚገባ ግንዛቤ መወሰድ አለበት፡፡ እንደ እድል ሆኖ (BLESSING IN DISGUISE) ታፍኖና መሳሪያውን በህዳሞች ተነጥቆ የኖረው የአማራ ህዝብ ወያኔ በጫረው እሳት አሁን ተደራጅቷል፣ ይበልጥ እየተዘጋጀም እየተደራጀም ይገኛል፡፡ይህ መሰል አደረጃጀቱና ሁሉም መከራ ያዬው የአማራ ገበሬና ነጋዴ በያለበት ምንጊዜም መሳሪያውን በቤቱ ይዞ ውጭ ሲውጣ በጀርባው ማንገቱ ማንም ፈቀደ አልፈቀደ ይቀጥላል፡፡ ፋኖም አደረጃጀቱንና ህዝባዊ ሀይልነቱን አጠናክሮ በመቀጠል ባለበት አካባቢ ለራሱም ለኢትዮጵያ መቀጠልም አስተማማኝ ሀይል ሆኖ ይኖራል፡፡ አማራው ከደረሰበት መከራና ከተሰራበት ይቅርታ የለሽ ሸፍጥ ተነስቶ ከእንግዲህ ወዲያ ለማንም ቅጥረኛ በሉት ተውተርታሪ ፖለቲከኛ አይመለስም፡፤ ለእውነተኛና ለትክክለኛ ፌደራላዊ ስርአት፣ ለህዝባዊነትና ለሀቀኛ ዳኝነት ብቻ እንጅ፡፡ ስለሆነም ወያኔ የያዛቸውን የአማራና የአፋር መሬቶች በሙሉ ለቅቆ ወደመጣበት ወደ መቀሌ እስካልተጠቃለለ፣ ይህም በተግባር እስካልተረጋገጠና “አሸባሪ’ ተብሎ በሸንጎው ለተጣለበት የአገሪቱ አዋጅ ተገቢውን ቅጣት ወይንም ምህረት በይፋ ከሸንጎው እሳክላገኘ ድረስ በመንግስት አመራር ላይ ባሉ ባለሁለት ቢለዋ በላተኞች/ፖለቲከኞች የሚደረገው ውሽልሽል ፖለቲካ በሙሉ ፈራሽ ነው፡፤ ነውር ለሚያውቅ ሁሉ ድርጊቱ መታሰቡ ብቻ ነውርም ነው፡፤ ስለዚህ ድርድር ተብሎ ነገርን ከሸንጎው ውሳኔ ውጭ የኢትዮጵያ መንግስት ፈጽሞ መቀበል የለበትም፡፤ ከባዱ ስህተት የሚፈጠረው መንግስት ወያኔ ከእንግዲህ ወዲያ በማያሰጋ መልኩ ተመትቷል፣ ከባድ መሳሪያ የለውም፣ አየር ላይ በንኗል፣ ሊያንሰራራ አይችልም …ወዘተ ብሎ በቀደዳ ለህዝቡ የሚያሳፍር ውሸት እንደዋሸውና እንደተዋረደው አሁንም ያንን መሰል ስህተት መልሶ ከሰራ ነው፡፡

    ትህነግ ተጠቃልሎና ተጠራርጎ ወደመጣበት እስካልተመለሰና ከዚያም ቀጥሎም ለህግ እስካልቀረበ ድረስ ድርድር ብሎ ነገር አይታሰብም፡፡ የመጣው የውጭ ጫና ከየትም ይምጣ፡፤ ህዝቡ አሁን በህይወቱ ከደረሰበት በደልና እልቂት የባሰ ነገር አያጋጥመውም፡፡ቢመጣበትም ይችለዋል፡፡ መንግስት ይህንን አልሰማም ካለ ያኔ ነው ህዝቡ አይምሬ አፋሙዙን ወደመንግስት የሚያዞረው፡፤ ያኔ ነው ወንድ ከወንድ ተለይቶ ነገሮች በእውነተኛ መልካቸው ስርአት የሚይዙት፡፤

    ስለሆነም ህዝቡን ወደዚህ መግፋት በራስ አንገት ላይ ሸምቀቆ ከማጥለቅ አይተናነስም፡፡ ስለሆነም በድጋሜ መንግስትን እናስጠንቅቅ፡፡ እንምከር ፡፡ድርድር በሚል ሴራ መንግስት ሌላ ስህተት ከሰራ አፈሙዙ የሚዞረው ወደራሱ(ወደመንግስት) እንደሚሆን ማንም ቅንጣት ጥርጣሬ ሊኖረው አይገባም፡፡

    ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !! ሞት ለወያኔና ርዝራዦቹ !!!

    እውነቱ ነኝ ፣ (ከባምቢስ)

  19. የወቅቱ ኢትዮጵያችን ሁኔታና በመጥፎ ድርጊቶች ውስጥ የተፈጠሩ ጥሩ አጋጣሚወችን የመጠቀም ችሎታ
    (ድንቁ ሞላ)
    ወያኔ ከስልጣን እንደተወገደ ወዲያዉኑ መወሰድ የነበረባቸው ወሳኝ እርምጃወች ባለመወሰዳቸው ለምሳሌ፦ህገ መንግስቱን ማገድ፣ ወያኔን ለፍርድ ማቅረብ፣ የተዘረፉ ንብረቶችን ወደ ህዝብ ማዞርና ወዘተ ባለመደረጋቸው እነዚያ ስህተቶች ተደምረው አሁን ለተፈጠሩት ችግሮች ዋና ግብአቶች ሆነዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁን ያለው የፖለቲካ ሁኔታ እንደሚያሳየው ጠ/ሚ/ር አብይ አህመድንና በዙሪያው ያሉትን ሹማምንቶችን የሚያሳስባቸው የሚመስለው ወያኔ ማፍፈግፈግ እየተደረገለትና በጦር አዛዦች ሴራ ከባድ መሳሪያወች እየተሸጡለት እየገሰገሰና ህዝብ እየጨፈጨፈ መምጣቱና ከውጭውም የሚመጣው የተደራደሩ አለበለዚያ የጉዞ ማእቀብና የኢኮኖሚ እቀባ እንደርግባችኋለን የሚለው ማስፈራሪያ ነው ተብሎ ይታመናል፡፡ ብዙወቻችንም የኦሮሙማን የስካሁኑን የተረኝነት አመራርና አሰራር በተግባር እንዳየነው አብይ አህመድ ለቪዛ ክልከላውና ለተደራደሩ ማስፈራሪያው ሸብረክ ይላሉ የሚል ግምት ነበረን፡፡ እርሳቸው በግልጽ ደብዳቤያቸው ላይ ካሰፈረሩት ሀሳብ ስንነሳ ግን አቋማቸው ሸብረክ ያላለ መሆኑን በማወቃችን ደስተኞች ብቻ ሳንሆን በዚህ ጉዳይ ላይ ከጎናቸው የተሰለፍን መሆኑን እናረጋግጣለን፡፡ ህዝቡ ነጻነቱን፣ የአገሩን ሉአላዊነትና ዳር ድንበሩን የሚነካበትን አይታገስም እንጅ ረሀቡን፣ችግሩንና፣ የኋላቀርነት ኑሮውን በእርዳታና በድጎማ ሳይሆን ራሱን በስራ በመቀየር መለውጥ እንዳለበት ከተረዳ ዉሎ አድሯልና የእኮኖሚ ማእቀቡ የሚያስከትለውን ችግር ከነጻነቱ አስበልጦ አይመለከተውም፡፡
    ወያኔ ይህንን ሁሉ ድራማ የሚሰራው ለአንድ አላማ ብቻ ነው፡፡ ይህም በተደራደሩ ሰበብ ስምምነት ተፈጠረ ተብሎ ለም የሆኑት የወልቃይትና የራያ መሬቶች እንዲመለሱለት ከተደረገ በኋላ ትንሽ ቆይቶ በሪፈረንደም ስም በአንቀጽ 39 አማካይነት ተገንጥሎ ታላቋን ትግራይ በማቋቋምና ውደሱዳን የመግቢያንና መውጭያ በሩን በባለቤትነት ይዞ ኢትዮጵያን ሲያደማ ለመኖር የሚያስችለውን እቅድ ለማሳካት ነው፡፡ የውጮቹም ይህንን ያህል በውስጥ ጉዳያችን እየገቡ የእንትና መሬት ወዘተ የዚህ ክልል ልዩ ሀይል ወዘተ የሚሉት ለጤና አይደለም፡፤አንድ ተረፈ የሚባል የዱሮ ሰፈራችን ሰው ንግስት የምትባለውን ሌላኛዋን ጎረቤታችንን አክስቷ ቤት ለሆዷብቻ ተቀጥራ የምታገለግለውን መቆያ የምትባል ታዳጊ ወጣት በሰበብ አስባቡ አክስቷ ቤት እየገባች እየወጣች ቁም ስቅል እያሳየቻት መሆኑን አይቶ ንግስትን ሊቦጭቃት ሲፈልግ እንዲህ ይላት ነበር፡፡”ይህች ተፍ ተፍ የመቆያን ቂጣ ለመመንተፍ” ይላት ነበር፡፡ ያ አባባል ዛሬ ላይ ለእኔ አስተማሪ አባባል ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ተደራደሩ እያሉ ተፍ ተፍ የሚሉት የውጭ ሀይሎች ለኢትዮጵያ ህዝብ አዝነው ሳይሆን ለወያኔ መልሶ ማንሰራራትና ይህም ማንሰራራት በጎረቤት ላሉ ጠላቶቻችን ሱዳንና ግብጽ በአገራችን ላይ ለሚያደርጉት ሴራና ጥቃት አገራችንን ይበልጥ ተጋላጭ ለማድረግ ሁኔታወቹን ለማመቻቸት ነው፡፤ ስለሆነም የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ይህንን ተንኮል ጠንቅቆ ስለሚያውቀው በአገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት በአዋጅ አሸባሪ ተብሎ ከተፈረጀው ከወያኔ ጋር ድርድር የሚባል ነገር አይኖርም፡፤ ምናልባትም በጦርነቱ ከተረፉ ጀሌወቹ ጋር ሊታሰብ የሚችለው ፍርድም ሆነ ምህረት ሊመጣ የሚችለው ወያኔ ድል ተመትቶ ሞቶና ተቀብሮ ህጋዊ አሰራር በመላዋ ትግራይ ከተረጋገጠ በኋላ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ አቋም ውጭ የሚሆን የኢትዮጵያ መንግስትም የፖለቲካ ድርጅትም ካለ በህዝቡ ተጠራርጎ መተፋትና መወገድ ነው እጣ ፈንታው የሚሆነው፡፡ ወያኔ በሰሜን እዝ ላይ የከፈተው ጦርነት የኢትዮጵያን ህዝብ በሙሉ ከጫፍ እስከጫፍ በአንዲነት እንዲቆም ያደረገን ጥር አጋጣሚ ቁጥር አንድን ፈጥሮልናል፡፡ የማእቀብ ማስፈራሪያውም እንዲሁ ወያኔ በውስጣችን ተክሎት ሄዶ የነበረውን የዘረኝነትን መርዝና ጎጠኝነትን ከስሩ ነቅለን ለመጣልና በአንድት ኢትዮጵያ በምትባል አገራችንና በኢትዮጵያዊነታችን ላይ አጠንክሮ የሚያቆመንን አጋጣሚ ቁጥር ሁለትን ፈጥሮልናል፡፡እነዚህ በመጥፎ ሁኔታወች ውስጥ የተፈጠሩ ሁለት ጥሩ አጋጣሚወች ሳያመልጡን በቶሎ ልንጠቀምባቸው ይገባል፡፡ ፈረንጆች ይህንን አይነቱን በመጥፎ ሁኔታ ውስጥ የሚከሰት ጥሩ አጋጣሚን (Blessing in Disguise) ይሉታል፡፡ስለሆነም ጠ/ሚር አብይ አህመድም የአገሪቱ ህዝብና ፖለቲከኞችም ሁሉም በየፈርጁ ጉድለቱን በሟሟላትና ማድረግ ያለበትን በየፈርጁ ሁሉም በማድረግ የአጋጣሚወቹ ሙሉ ተጠቃሚ ለመሆን ሁሉም የየበኩሉን ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
    ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁን በስልጣን ላይ ያለውን መንግስትና አገሪቱን ከባድ ውድቀት ውስጥ የሚከትተው የወያኔ ጦርነት ወይንም የውጭው ማስፈራሪያ ሳይሆን አሁን መሽተት እንደጀመረው አይነት ሴራ ማለትም የአማራ ክልል አስተዳደር በፌደራል መንግስት ግፊትም ይሁን በራሱ አነሳሽነት በፋኖ አደረጃጀት ውስጥ ጣልቃ መግባት ከጀመረ ነው፡፤ በዚያች ያልታሰበች መጥፎ ሰአት ወያኔ የሰሜኑን እዝ በጨፈጨፈ ማግስት ወደ መሀል አገር ጀምሮት የነበረወን አደገኛ ግስጋሴ ከባድ መስዋእትነትን ከፍሎ በመግታት የአገሪቱንና የመንግስት ባለስልጣናትን የሁሉንም ደም ያፈሰላቸውን ይህንን የአማራ ልዩ ሀይልና የአማራ ፋኖን አደረጃጀቱን በፍራቻም ሆነ በሌላ ምክንያት ለማስቆም መሞከርና ጣልቃ መግባት በምንም መንገድ መታሰብም መደረግም የለበትም፡፡ ይልቁንስ ይህንን የአገር አለኝታ የሆነ ትኩስና ነፍጠኛ ሀይል በአማራው ህብረተሰብ ውስጥ ሲወርድ ሲዋረድ ተያይዞ ለዘመናት የመጣ አደረጃጀት ባህሉና ስሪቱ መሆኑን በመረዳት ማገዝና ማበረታታት ያስፈልጋል፡፤ ሀቀኛና ትክክለኛ የህዝብ ቆጠራ ቢደረግ ከ40 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው የአማራ ህዝብ ከማንምና ከምንም በላይ በውስጡ ያለውን ፋኖን ይተማመንበታል፡፡ የፋኖ ሀይል ምንም ቢያድርጉት ካመነበትና ከተሰለፈበት አላማ የማይታጠፍ ሀይል ነው፡፤ ምንጊዜም እየትንቦገቦገ ለህዝቡ ብርሀን፣ ሙቀትና የደህንነት ዋስትናን የሚሰጥ ትኩስና አስተማማኝ የአካባቢና የአገራችን ኢትዮጵያ አለኝታ ሀይል ነው፡፡ጎጠኞች፣ ዘረኞችና ብሎም ሆዳሞች ሊጠሉት ይችላሉ፡፤ አድርገውታልም፡፤አልተሳካላቸውም እንጅ ሊያጠፉትም ሞክረው ነበር፡፤ ይህንን ሀይል ኢትዮጵያዊያኖች ይወዱታል፡፤ ይመኩበታልም፡፤ ምክንያቱም ይህ ሀይል ጎጠኞች እንደሚገምቱት ሳይሆን ለስልጣን አስጊ ያልሆነና ጠባብነት ያልተጠናወተው ምሉእ ኢትዮጵያዊ ሀይል ነው፡፡ በአገሪቱ የሽህ አመታት የጦርነትና የአልበገሬነት ታሪክ ውስጥ በብዙ አውደ ዉጊያወችና የአገር መከላከል ግንባሮች ውስጥ ሰፊ አስተውጽኦና የድል አድራጊነት ታሪክ አለውና፡፡ ይህንኑም ታሪክ የእሁኑ ዘመንም ፋኖ በተግባር አሳይቷል፡፡አሁንም እያሳየ ነው፡፤ስለሆነም ይህንን ነፍጠኛ የፋኖ ሀይል ተንከባከቡትና እግዙት እንጅ በውስጡ ገብታችሁ እንዳትበጠብጡት፡፤ ይህ ሀይል በእናንተ ቀጥተኛም ሆነ ስውር ሴራ የተበጠበጠ እለት የሁሉም ነገር ማብቂያ እለት መሆኑን ከውዲሁ ተረዱት፡፡

  20. ወያኔ ሲጀመር አንስቶ የሚሰራው ስራ በሙሉ ጥፋት ነው፡፡ የትግራይ ህዝብ ደግሞ ወዶም ሆነ ተገዶ ከውስጡ የበቀሉና በጥፋት መርዝ የሰከሩ ወያኔወችን ተከትሎ ወደ መቀመቅ እየወረደ ነው፡፤ ያስፈጁትን የትግራይ ወጣት ቁጥር በሚመለከት በኋላ ሀቁ ሲወጣ የትግራይ እናቶች እንባ በእንባ ይሆናሉ፡፡
    በህልውና ጦርነቱ ውስጥ የኢትዮጵያ ጦር ጠላቱ የሆነውን ወያኔን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ወያኔ የመሳሪያ አይነቱን እንድመርጥለት አይፈቅድም፡፤ ወያኔን ለማስወገድ በየአውደ ዉጊያው ከመጥረብያ፣ ዱላና ቢለዋ ጀምሮ ማንኛውንም አይነት በህልውና የመጣ ጠላትን የማጥፊያ መሳሪያን መጠቀም የጥፋቱ ተከላካይ ሙሉ መብትና ምርጫ ነው፡፡””ከጦርነት ህግ ውጭ በጦር አውሮፕላን ተመታን”” እያላችሁ ማላዘናችሁ ማፈሪያም አስቂኝም መሆናችሁን ስለሚያረጋግጥ አይገርምም፡፡ለካ ውሸታሞች ብቻ ሳትሆኑ የማታመዛዝኑ ደንቆሮወችም ናችሁ፡፡
    ውሸት የማይታክታችሁ የትህነግ ርዝራዦች ሆይ፦ ቀጥሎስ ምን ትዋሹ ይሆን?? በመቶ ሽህ የሚቆጠሩ ወጣቶችን በሀሽሽ ጭምር እያሰከራችሁ ለማይጨበጥ ቅዠታችሁ አስጨርሳችሁ፡፡ በመጨረሻ ላይም በጦርነቱ ተሽንፋችሁ ወደ ታላቋ ሳይሆን ከራያና ወልቃይት ውጭ ወደነበረችው “ነባሯ” ትግራይ ስትመለሱ የዋሻችሁለትና ልጆቹን ያስጨረሳችሁበት የትግራይ ህዝብ ምን ይላችሁ ይሆን??? ለነገሩ እውቁ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም “ከፋብሪካ የወጣ ሳሙና ነው” ሲሉ ነገሩን ጨርሰውታል፡፡ እዚህ ላይ የሀሙራቢ ህግስ ይሰራ ይሆን?? ይታያል፡፡ አሁን ላይ አሜሪካም ነቃችባችሁ፡፡ ቀደዳችሁ ግን ለተጋሩ በአጓጊነቱና በባዶው ሞራል ገንቢነቱ ለተቀረው አለም ደግሞ በአስቂኝነቱ አሁንም ቀጥሏል፡፡
    በነገራችን ላይ ተረኛው ኦሮሙማስ ከዚህ ምን ይማር ይሆን???
    ወያኔወችና ርዝራዦቹ ሆይ፦አንካካድ፡፡ ወደዳችሁም ጠላችሁም በእርግጠኝነት ማመን ያለባችሁ ወይንም እንድታምኑ የምትገደዱበት ማንም በምንም ሊቀይረው የማይችል አንድ እውነት አለ፡፡ ይሄውም የራያና የወልቃይት ለም የአማራ መሬቶች የዘለአለም ቅዠታችሁ ብቻ ሆነው ይቀራሉ!!
    በእውነት መካካድን የምትጠየፉ ከሆነ ጦርነት የጀመራችሁበት ዋና ምክንያት እነዚህ አሁን አማራው በትግሉ ያስመለሳቸውንና አሁን በቁጥጥሩ ስር አድርጎ ያስከበራቸውን የራሱን ነባር የወልቃይትና ራያ ርስቶቹን ለመንጠቅ ነበር፡፤ይህ የመሬት ነጠቃ ሙከራ ላይሳካላችሁ ተደምድሟል፡፡ የፈለጋችሁትን ስም ስጡት በሽምግልና፣ በለውጥ፣ በድርድር ፣ በውጭ ጫና ወዘተ በሉት፡፡ አይሳካም እንጅ ካስኬዳችሁም ኦሮሙማንም ታከኩ፡፡ የቅዠት መንገዶቻችሁ ሁሉም ዝግ ናቸው፡፡ ያለምንም ሌላ ዝብዝንኬና ምክንያት ድርደራ ወያኔ ጦር የመዘዘበት ዋና ምክንያት የግፍ ጽዋው ሞልቶ ከአገር መሪነት ስልጣኑ ሲባረር ለ27 አመታት ከአማራው ነጥቆ ይዟቸው የነበሩትን የወልቃይትና የራያ ለም የአማራ መሬቶቹን መልሶ በመውሰድ ታላቋ ትግራይን እንደአገር መስርቶ ለመገንጠል ነበር፡፡ከዚያች እለት ጀምሮ በእብሪት ያበጠውና በቅዠት የተዋጠው የወያኔ ጉዞ ሁሉም ኪሳራ በኪሳራ እየሆነ ሄድ፡፤ የኪሳራው ገጾችም ሲገለጡ እንዲህ ይነበባሉ፡፤
    ጦርነቱን እኛ አልጀመርንም እንዳትሉ ጸሀይ የሞቀው አለም ያወቀው በቂ መረጃ አለ፡፡በዚህ የአብሪት ጦርነት የትግራይ፣የአማራና አፋር ህዝብ ኑሮ ላይመለስ ተመሰቃቅሏል፡፤ ብዙ ህዝብ አልቋል፡፤ ብዙ ንብረት ተዘርፏል፡፡ ልማት ወድሟል፡፤ ይህንን ኪሳራ አንድ ብላችሁ መዝግቡት፡፡ የቋመጣችሁላቸውን የራያና ወልቃይት መሬቶች ምንጊዜም አታገኟቸውም፡፡ ይህንንም ኪሳራ ሁለት በሉት፡፡ ካለእነዚህ ለም መሬቶች መገንጠሉም በብዙ የውስጥና የውጭም ተጨባጭ ምክንያቶች አይሳካም፡፡ይህንንም ኪሳራ ሶስት በሉት፡፡ የትግራይን ህዝብ ከአማራው፣ ከአፋሩና ከኤርትራ ህዝብ ጋር ምንጊዜም ሊሽር በማይችል መልኩ ደም አቃብታችሁታል፡፤ይህንንም ኪሳራ አራት ብላችሁ መዝግቡት፡፡ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ 27 አመት ሙሉ እስከአጥንቱ ድረስ ስለጋጣችሁት ሊዛመዳችሁ ይቅርና እንደገና ሊያያችሁ እንኳን አይፈልግም፡፡ እስከሚያንገሸግሸው ድረስ ጢባጢቤ ተጫውታችሁበታል፡፤ይህንንም ኪሳራ አምስት በሉት፡፡
    የወያኔ ጀሌ ሰራዊት ክዘረፋው ባሻገር ምንም ቁጥር ሊገልጸው የማይችለው ኪሳራን በአፋርና በአማራ ክልል አድርሷል፡፡ምሳሌ፦ የመነኩሴን ሚስት መድፈር፣ እርጉዝ ሴትን መድፈር፣ ታናናሽ ሴት ልጆችን እናቶች ፊት መድፈር፣ ሚስትን ባል ፊት መድፈር፣ እህትማማቾችን እየተፈራረቁ መድፈር፣ የእህል ክምርን ማቃጠል፣ የአማራ ከብቶች ስለሆኑ ብቻ እንሰሳወቹን በመርዝና በጥይት መግደል ፣ አንድን ቤተሰብና አንዲን መንደር ፈጅቶና አቃጥሎ አስክሬኖች እንዳይቀበሩ በመከልከል በጅብ ማስበላት ….ወዘተ ለጆሮና ለህሊና የሚከብዱና ተዘርዝረው ያማያልቁ ታሪክ ወደፊት መዝግቦ የሚያወጣቸው አያሌ ወንጀሎችን ፈጽሟል፡፡
    ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ የፈለገ ጊዜ ቆይቶም ቢሆን በሆነ መልኩ ሰላም መጥቶ እንደነገሩ እርቅ ይውረድ ቢባል እነዚህን ሁሉ ሰቅጣጭ ወንጀሎችን በጅምላ ከፈጸመ አንድ የሀብረተሰብ ክፍል ጋር እንዴት ተብሎ ነው ግንኙነት ሊፈጠር የሚችለው?? ፈጽሞ አይሞከርም፡፡ወያኔ የፈጸማቸው እንሰሳዊና አረመኔያዊ ድርጊቶች ተነግረው አያልቁም፡፤ ስለሆነም እናንት ወያኔወች ሆይ፦ ይህንን ሁሉ ግፍ በእብሪትና በቅዠት በህዝብ ላይ ከፈጸማችሁና ካስፈጸማችሁ በኋላ መጨረሻ ላይ ምን አተረፋችሁ?? መልሱ ምንም ነው፡፤ ተጠያቂነቱና በሰማይም በምድርም ለፍርድ መቅረቡ እንዳለ ሆኖ ሁሉም ህዝብ እንዲህ አምርሮ የጠላችሁና በውጤት አልባው ጦርነቱም ያስጨረሳችሁት በመቶ ሽህወች የሚቆጠሩ የትግራይ ወጣቶች እንደዚሁም የአማራና የአፋር ህዝብ እልቂት ያስገኘላችሁ ምንም ነገር የለም፡፤ በቀሪውም ጊዜ ማለትም እስከመጨረሻዋ የሽንፈትታችሁ ደቂቃ ድረስም የምታሳኩት ምንም ነገር የለም፡፤ ምክንያቱም የቆማችሁበት መስመር ሙሉውን በውሸትና ጥላቻ ላይ ተመስርቶ በቅዠት የተሞላ ብቻ ሳይሆን ጸረ ሳይንስ፣ ጸረ አገርና ጸረ ህዝብ ስለሆነ ነው፡፡ስለሆነም ፍጻሜያችሁ ኪሳራ ነው፡፤ ገባችሁ?

  21. የአብይ አህመድ የ2 ለ1 የቁማር ጨዋታ
    አብይ አህመድ አገርንና ህዝብን አስይዞ 2 ለ1 የፖለቲካ ቁማር እየተጫወተ ነው፡፤ ጨዋታውም እንዲህ ይቃኛል፡፡እብሪተኛው ወያኔ የከፈተውን ጦርነት ኦሮሙማ መራሹ የአብይ አህመድ መንግስት በስውር ይደግፈዋል፡፤አብይ አህመድ የአማራ ክልልን በወያኔ በማስያዝ በወልቃይትና ራያ ላይ ለመደራደር ከጸረ ኢትዮጵያ ሀይሎች ጋር የተደበቀ ስምምነት ፈጽሟል፡፡ የስምምነቱ ማጠንጠኛም አብይ ወሎን አስወርሮ ለድርድር ከወያኔ ጋር በመቀመጥ ካስኬደው ወልቃይትን ጭምር፤ ካላስኬደው ግን የራያን ለም የአማራ መሬት በእርግጠኝነት ለወያኔ ለማስረከብ ፍጥጥሙ አልቋል፡፡ግለሰቡ ተሳክቶለት ይህንኑ ካደረገ በራሱና በቤተሰቡ ላይ የተጣለበት የጉዞ ማእቀብና በአለም አቀፍ ፍርድቤትም የተመሰረተበት የወንጀለኝነት ክስ ይነሳለታል ማለት ነው፡፡ለሀያላኖቹ ምን ያቅታል? በዚህ ጨዋታ ሂደት ውስጥ አብይ 2 ነጥብ ሲያስቆጥር አንድ ነጥብን ይጥላል፡፡ ነጥቦቹን በአጭሩ እንመልከታቸው፡፤ ወያኔወች የራያና ወልቃይትን ለም የሆኑ የአማራ መሬቶች በሴራ እንድወስዱ ሲደረግ ሲያልሟት የነበረችውን ታላቋ ትግራይን በአገርነት ለመመስረት በለስ ቀናቸው ማለት ነው፡፡ በዚህም አድራጎቱ አብይ የአለቆቹን ትእዛዝ በመፈጸሙ ቃል የተገባለትን ያገኛል ማለት ነው፡፤ይህንን ነጥብ አንድ በሉልኝ፡፡ አማራው በስሌት ከግራና ቀኝ ከላይና ታች፣ እንድፈናቀል ፣እንዲያልቅና እንዲንኮታኮት ስለተደረገ ለኦሮሞው የበታች ሆኖና ጸጥ ለጥብሎ በበታችነት ይገዛል ማለት ነው፡፡በውጤቱም ኦሮሞ ይብለጥ አብጦ የተረጋጋ ገዥ ሀይል ይሆናል ማለት ነው፡፡ይህንን ደግሞ ነጥብ ሁለት በሉት፡፡ እነዚህ ሁለት ነጥቦች ለአብይ የቁማር ጨዋታው የድል ነጥቦቹ ናቸው፡፤ሶስተኛው ነጥብ ለአብይ አህመድ የሽንፈት ነጠላ ነጥብ ተብሎ ይወሰድ፡፡ በዚህም ነጥብ አብይ አሳዛኝና አሳፋሪ ቁማር የተጫወተበት የአማራው ህብረተሰብ ጋር ጥላቻውና መቃቃሩ ስር ሰድዶ አድፍጦ ይቆያል ማለት ነው፡፡ይህ የ2ለ1 ጨዋታ ማካካሻ የሌለው የቁማር ጨዋታ ነው፡፡
    በጦርነቱ ሂደት ደሴና ኮምቦልቻ ለቀናት በፋኖ፣ ልዩ ሀይልና በመደበኛ ጦሩ በወያኔ ሳይያዙ የቆዩ ቢሆንም ዛሬ ማለትም ጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓም በወያኔ እጅ ወድቀዋል፡፡ደሴ የተወጋችው በወራሪው የትግራይ ጦር ከውጭ ብቻ ሳይሆን ይልቁንም በሚቆጭ ድርጊት ይበልጥ የደማችው በከተማዋ ውስጥ ለአያሌ አመታት በኖሩ የትግራይ ባንዳወች ነው፡፡ ኮምቦልቻ ከተማ በኢንዱስትሪ ሀብቷ በአማራ ክልል ውስጥ በቁጥር አንድ ትጠቀሳለች፡፡ወያኔ ከተማዋን በያዘ ቅጽበት ወዲያዉኑ ንብረት መዝረፍና በትልልቅ መኪኖች እየጫነ ወደመቀሌ ማጋዝ ጀምሯል፡፤ ይህንን በትልልቅ መኪኖች የሚፈጸም የዘረፋና ወራሪ ጦርን የማመላለሱን ስራ የማያየው የአብይ አህመድ አየር ሀይል ወደ መቀሌ የሚበረው በአማራ ክልል አየር ላይ ነው፡፡ የትኛው ይቀድማል? ፍርዱን ለናንተ እንተወው፡፡ ለነአብይ አህመድ ግን የትኛው መንገድ በቶሎ ወደ ሴራ ፖለቲካቸው ስኬት እንደሚወስዳቸው ስለሚያውቁ ያደረጉትን አድርገዋል፡፡
    አንድ እውነትን ግን ማንም ሊክድ አይችልም፡፡አብይ አህመድ በአውሮፕላንና በድሮን አልፎ አልፎ ለይስሙላ የሚያስደርገው የማጥቃት ሙከራ የማያመርቃ ሆኖ ወረራውን ያላስቆመበት ዋና ምክንያት አየር ሀይሉ ስላልቻለ ሳይሆን ድርጊቱ ለይስሙላ የሚደረግ ስለሆነ ብቻ ነው፡፡ ከባባድ መሳሪያህንና የያዝከውን ገዥ መሬት ለወያኔ አያስረክበህ “አፈግፍግ” የሚለውም የአዛዦች መመሪያ እስካሁን ኮዱ (ቅኔው) ላልተፈታላቸው ይብላኝላቸው እንጅ የአማራ ህዝብስ ዘግይቶም ቢሆን ሴራው ተገልጾለታል፡፡ በሌላ አቅጣጫም ማለትም በወለጋና በቤንሻንግል ክልሎች በኦነግና በጉምዝ ጸረ አማራ ሀይሎች በየቀኑ እንደቅጠል የሚረግፈው የአማራወች ህይወት ለአብይ አህመድ ምኑም አይደለም፡፤ እንደመሪ ብቻ ሳይሆን እንደ ሰው የአብይ ማንነት እጅጉን ይገርማል፡፡አብይ መጀመሪያ ወያኔ ዱቄት ሆኗል አለ፡፤ ቀጥሎም የተናጠል ተኩስ ማቆም አድርገን ከትግራይ ወጥተናል አለ፡፡ቀጥሎም ወያኔ እየገፋ ሲመጣ “አፈግፍጉ” አስባለ፡፡ቀጥሎም ተነስ፣ክተት፣ ዝመት የትም መቸም ለኢትዮጵያ አሰኘ፡፡ጥቂት ሳይቆይም የምን ተነስ፣ ዝመት፣ ክተት – ይልቁንስ የዉጊያ ዝግጅትህን ትተህ ትራክተር ያዝ፣ እረስ፣ አምርት ብሎ ለአፍታም ሳይቆይ ቃሉን በምላሱ አጠፈው፡፡ አሁን ደግሞ ወረራውን ወታደሩ ብቻውን ሊመክተው ስለማይችል ለሁሉ አቀፍ ህዝባዊ ጦርነት ሁሉም ይነሳ አለ፡፤ ይህንን ባለ በማግስቱ ግን የወያኔን ግስጋሴ ለመግታት ደሴና ኮምቦልቻ ገና ሳይያዙ ትንቅንቁ በተጧጧፈበት እለት ጎጃም ያለው በፋኖ የሰለጠነ ጦር ብሎ ለመዝመት ሲጠይቅ መሰሪው አብይ በድንዝዞቹ የአማራ ክልል ወኪሎቹ አማካይነት በብልጽግና ስር ካልሆናችሁ በስተቀር ትጥቅ አይሰጥም ተብሎ እንድበተኑ ተደረገ፡፤ እንግዲህ በአጭሩ አብይ አህመድ ማለት እንደመሪም እንደሰውም ይህንን ይመስላል፡፡
    አማራ ሆይ፦እንዳትረሳ፡፡በጦርነቱ ተሰደው ደሴና ኮምቦልቻ የነበሩ ሽማግሌ፣ አሮጊትና ህጻናት የወሎ ስደተኞች አዲስ አበባ አትገቡም ተብለው የተከለክሉበትንና በተቃራኒው ግን ከጥቂት አመታት በፊት ተፈጥሮ በነበረው የኦሮሞና የሶማሌ ግጭት ወቅት የኦሮሞ ስደተኞች ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ የዲሞግራፊ ቅየራን ጨምሮ ምን እንደተደረገላቸውና ይህም ለአንተ ምን ማለት እንደሆነ የሚጠፋህ አይመስለንም፡፤አንተ አሁን ላይ መንግስትም መሪም የለህም፡፤ ከቦታህ ነቅለው ሊጥሉህ ነው፡፤ስለዚህ መፍትሄው አንድ ብቻ ነው፡፤ ራስህን ነጻ አውጣ፡፡እንዴት ለሚለው ጥያቄ “በያለህበት ተደራጅተህ ጠላትን በማሸነፍ”ብቻ ነው መልሱ፡፡መከራውን ተቋቁመህ ፣በፋኖወች የተፈጠረውን ህዝባዊ ንቅናቄ ተቀላቀል፡፡አይናብራው ልጅህ ጀኔራል አሳምነው ጽጌ በአብይ አህመድ ሴራ ከመገደሉ በፊት እንደ ትንቢት እንዳስጠነቀቀህ ሁሉ ይሄውና አሁን በገሀድ ተከበሀል፡፤ህልውናህም በአደጋ ውስጥ ነው፡፡በቅድሚያ በውስጥህ ለጠላት የተሸጡ የአማራ ሆድ አደሮችንና ለዘመናት አንተን መስለው አብረውህ እየኖሩ ለወያኔ የሚሰሩና ጊዜ ጠብቀው መሳሪያ የመዘዙብህ የወያኔ ደጋፊና አባላት ላይ ለይተህ ሳታወላውል በያሉበት ፈጣን እርምጃ ውሰድባቸው፡፡ውስጥህን አጥራ!! እንዳላዘኑልህ ሁሉ ልታዝንላቸው ፈጽሞ አይገባም!! እንዳትታለል፡፡ከእንግዲህ ወዲያ መጥፋትም መዳንም ያለው በአንተና በአንተው እጅ ብቻ ነው፡፡ በግለሰብ ደረጃ ሊታረሙ ከሚችሉት በስተቀር በድፍኑ ብልጽግና፣ ብአዴን ብሎ ነገር የለም፡፡ሁሉንም እስካሁን አይተሀዋል፡፤ከፋኖ፣ ከአማራ ልዩ ሀይል፣ከአማራ ህዝባዊ ሀይልና ከጎንህ ሆኖ በግንባር አብሮህ ከተዋደቀው የመከላከያ ታችኛው የሰራዊቱ ተዋጊ ጓድ በስተቀር በሌሎቹ ተክደሀልና እንዳትዘናጋ፡፡ትግልህን ዳር ለማድረስ ሞት ወይንም ነጻነት ብለህ አምርረህ ተነሳ፡፤ በዚህ ቆራጥ አቋም ከተጓዝክ ራስህን፣ ህዝብህንና ብሎም አገርህን ኢትዮጵያን በእርግጠኝነት ታድናለህ፡፡

  22. የምንወዳችሁ ዘሀበሻወች ሆይ፦
    “የአማራው ሶስት እውነታወች’ በሚል ርእስ December 23 ,2021 በዘሀበሻ ድረ ገጽ ላይ ወጥቶ የነበረው ወቅታዊ ጽሁፍ የብዙ ሰወች መነጋገሪያ ሆኖ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ጽሁፉ ከ2 ቀን በኋላ ከድረ ገጹ ላይ ተነስቷል፡፡ ይህንንም ያወቅሁት ጽሁፉን እንዲያነቡት ከነገርኳቸው ሰዎች አፍ ነው፡፤እኔም ደግሜ ብፈልገው ላገኘው አልቻልኩም፡፡ ብዙ ሰወችም ጽሁፉን ሊያነቡት ፈልገው ድረ ገጹ ላይ እንዳላገኙት ከኢንፎርሜሽን ቅብብሎሾቹ ተረድቻለሁ፡፡ ይህ ለምን ሆነ? ጽሁፉ የተነሳው በስህተት ከሆነ ይህንኑ ምክንያታችሁን ገልጻችሁ በድረ ገጹ ላይ መልሳችሁ ጫኑት፡፤ ጽሁፉ የተነሳው በኢድቶሪያል ችግር ነው እንዳይባል የጽሁፉ ይዘት ያንን የሚያስብል አይደለም ብቻ ሳይሆን ከዚህ ጽሁፍ በማንኛውም እይታወችና መመዘኛወች ብዙ የከረሩ ጽሁፎችን በዘሀበሻ ላይ ደጋግመን አንብበናል፡፡ በዚህም ተበረታታናል፡፡
    ከሁሉም ክልሎች ይበልጥ በመንደርተኞች የተጎዳውን የአማራን ህዝብ ያለበትን እውነታ የሚያሳየውን ይህንን ጽሁፍ እንዲታነሱ በስርአቱ ውታፍ ነቃዮች/ምንጣፍ ጎታቾች ማስፈራሪያ ደርሶባችሁ ሊህን ይችላል፡፡ ታዲያ ይህ ከሆነ የእናንተ ጋዜጠኝነትና ለእውነት ቆመናል ማለት የት ላይ ነው? ከመአዛ መሀመድ፣ ከታምራት ነገራ፣ ከስክንድር ነጋ…ወዘተ ጋር ሲነጻጸር የእናንተ የጋዜጠኝነት ቦታችሁ የት ላይ ነው የሚገኘው??

  23. ዐውደ፡ቀለም፡ክለሳ፡1.3_20140621፡ወጥቷል!

    የተከበራችኹ፡አንባብያን፥

    ነጻው፡የጽሑፍ፡ማምረቻ፡መግበር፡”ዐውደ፡ቀለም”፡ዐዲስ፡ክለሳ፡(ክለሳ፡1.3)፡ወጥቷል፤ ከመርበቢያው፡ከ፦

    awde-qelem.net

    በነጻ፡መቅዳት፡ይቻላል።

    ይህ፡ዐዳስ፡ክለሳ፡የጨመራቸውና፡ያሻሻላቸው፡ገጽታዎች፡የሚከተሉት፡ናቸው፦
    1፤ ኹለት፡ዐዳዲስ፡መግበሮች፡ታክለውለታል፤
    • አንደኛው፡መግበር፥ የቃላት፡መተረሪያ፡መግበር፡ነው፤ በርሱ፡አማካይነት፡ማንኛውም፡ሰነድ፡ወስጥ፡የሚገኙትን፡ቃላት፡በነጠላ፡ሰብስቦ፡ባዲስ፡ሰነድ፡ውስጥ፡መመዝገብን፡ያስችላል።
    • ኹለተኛው፡መግበር፥ የጽሑፍ፡መሰደሪያ፡መግበር፡ነው፤ ባንድ፡ሰነድ፡ውስጥ፡በመሥመር፡የተዘረዘሩ፡ልቅ፟ሞችን፡በፊደል፡ተራ፡መሰደርንና፡ባዲስ፡ሰነድ፡መመዝገብን፡ያስችላል።
    2፤ የሚከተሉት፡ማሻሻያዎችም፡ተደርገዋል፤
    • አንደኛው፡ማሻሻያ፡የቃላት፡ማተራጐሚያውን፡ይመለከታል፤ ርስ፡በርሳቸው፡ይተራጐሙ፡የነበሩት፡የዐማርኛ፣ የእንግሊዝኛ፡እና፡የፈረንሳይኛ፡ቃላት፡በክለሳ፡1.2፡38,000፡ደርሰው፡ነበር፤ ክለሳ፡1.3፡ይህን፡አኃዝ፡41,000፡አድርሶታል።
    • ከ200፡የሚበልጡ፡ሀገሮች፡ስሞችና፡የመናገሻ፡ከተሞቻቸው፡ስሞች፡በራሳቸው፡አጠራሮችና፡ባማርኛ፡አጠራሮቻቸው፡መዝገበ፡ቃላቱ፡ውስጥ፡በነቂስ፡ተመዝግበዋል። እንዲሁም፡ከ900፡የማያንሱ፡የኢትዮጵያ፡አውራጃዎችና፡ወረዳዎች፡ስሞች፡በትኽክለኛ፡አጻጻፋቸው፡ተመዝግበዋል።
    • ያማርኛ፡ጽሑፍ፡ፊደልን፡ማረሚያው፡መግበር፡ደግሞ፥ ካ5%፡እስከ፡10%፡የሚደርስ፡የችሎታ፡እድገትን፡አግኝቷል።
    • ሌሎችም፡ጥቃቅን፡ማሻሻያዎችና፡ዕርማቶች፡ተደርገዋል።

    ላልስሙ፡እንድታሰሙልን፡በትሕትና፡እንለምናለን።

    ካክብሮት፡ሰላምታዬ፡ጋራ፥
    ዐውደ፡ቀለም

  24. ለምትፈልገው ነገር ካልታገልክ ላጣሀው ነገር አታልቅስ!
    በኤጀንሲ ስም ለዘመናዊ ባርነት የተዳረጉ
    1, በቤንሻጉል ክልል ኢትዮ-ቴሌኮም ሪጅን ከ95% በላይ
    2, በአፋር ክልል ኢትዮ-ቴሌኮም ሪጅን ከ87% በላይ
    3, በሱማሌ ክልል ኢትዮ-ቴሌኮም ሪጅን ከ91% በላይ፣
    4, በደቡብ ክልል ኢትዮ-ቴሌኮም ሪጅን ከ90% በላይ
    5, በኦሮምያ ክልል ኢትዮ-ቴሌኮም ሪጅን ከ94% በላይ
    6, በአማራ ክልል ኢትዮ-ቴኮም ሪጅን ከ94% በላይ
    7, በጋምቤላ ክልል ኢትዮ-ቴሌኮም ሪጅን ከ96% በላይ
    የኩባንያው(የኢትዮ-ቴሌኮም) ሹፌሮችን ማን ይሆን መፍትሔ ሚሰጣቸው?
    በኩባንያው ውስጥ በሹፌርነት ሙያ ከአንድ ዓመት እስከ ከዘጠኝ ዓመት እና አሁንም እያገለገሉ ይገኛሉ ግን ኩባንያው ለሰራተኛው የሚሰጠውን ጥቅማጥቅም ለኤጀንሲ ሹፌሮች አይሰጥም ለምሣሌ፦ ዘንድሮ ለሁሉም የኩባንያው ሰራተኞች ቦነስ ሲሰጥ ለኤጀንት ሹፌሮች አልሰጠም ፣ እንዲሁም በ2015ዓ.ም አመታዊ የደሞዝ ጭማሪ ለካምፓኒው(ለኢትዮ-ቴኮም) ቋሚ ሰራተኞች( ቋሚ ሹፌሮች) 25% ሲጨመርላቸው ለእኛ ለኤጄንሲ ሹፌሮች አልተጨመረም ምን አለ እኛም እንደ፣ ኩባንያው ሠራተኛ ብንታይ መቼ ይሆን የኩባንያው ሠራተኛ ምንሆን እረ መላ በሉን 2015 ዓ/ም የመፍትሔ አመት ይሁንልን። ለሚመለከተው አካል አቅርቡልን ለኢትዮጵያ አምላክ ብላችሁ እኛስ ሰሚ አላገኘንም፣ ከአመት አመት ይሻሻላል ስንል ይህው ዘጠኝ አመት ሞላን ዘጠኝ አመት ሰርተን 3174 ብር ነው ደሞዛችን በመስሪያቤቱ ህግ እና ደንብ መሠረት 3174ብር ሚባል ደሞዝ የለም በሀገራችን እንደ ሁለተኛ ዜጋ ተቆጥረን ከሁሉም ጥቅማጥቅም ተገልለን የህክምና ለቋሚ ሰራተኛ በሀገሪቱ ባሉ ማንኛውም የግልም ሆነ የመንግስት ሆስፒታሎች 100% ነፃ የስልክ የትራንስፓርት የቤት ኪራይ እና መሰል ጥቅማጥቅሞች ተከልክለን በየ ሶስት አመቱ ለተለያዩ ኤጀንቶች ተላልፈን እየተሰጠን ግብር ለማይከፍሉ ኤጀንቶች የስራ ግብር ለማይሰጡ ኤጀንቶች ተላልፈን እየተሰጠን በዘመናዊ ባርነት ውስጥ እንገኛለን እባካችሁ ችግሮቻችን ተረድታችሁ መፍትሄ እንድናገኝ ተባበሩን

  25. ኢትዮ ቴሌኮም የኢትዮጵያውያን ሀብት ነው የሀገሩን ዜጋ አንዱን ቋሚ ሰራተኛ አድርጎ እንደልጅ አንዱን ኮንትራት ሰራተኛ አድርጎ የባርነት ስርአትን መተግበሩ አሳዛኝም አሳፋሪም ተግባር ነው ኮንትራት ሰራተኞቹ ለድርጅቱ ያላቸውን ታማኝነትና ቀናኢነት ላየእና የስራትጋታቸውን ለተመለከተ በምን ምክንያት ኮንትራት እንደተደረጉ መገረም ውስጥ ይከታል ይሄንን እውነታ በቋሚነት የሚሰሩ አጋሮቻቸው ምስክርነቱን ይስጡበት እንደሀገር በሀገር ሀብት እኩል የመጠቀም መብት የሚከበርበት ጊዜ ዛሬ ነው……።

  26. በተደጋጋሚ በትችት (ኮመንት) አምዱ ላይ የማስተላልፋቸውን ተለጥፈው ባለማዬቴ አዝኛለሁ።ምክንያቱ ምንና ከማን እንደመጣ ባውቀውም ከመግለጽ በመቆጠብ ምላሹን ከሚመለከተው ከዚህ ገጽ ሃላፊ እጠይቃለሁ።በዝምታም የሚታለፍ ከሆነ የዲሞክራሲና የጋዜጠኝነት ሙያ ባፍጢሙ ተደፍቷል ማለት ነው።ያንን ለማቅናት ከሚታገሉት ጋር የምችለውን ለማድረግ እሞክራለሁ።ትዝብት ነው ትርፉ!እዬጻፍኩ በቆይታ ላይ(Under observation) የተቀመጡትን መልእክቶቼን በፎቶ ለማስረጃነት ስለማስቀምጣቸው ባስፈለገ ጊዜ ይወጣሉ።

  27. I really enjoy the articles, the latest news and breaking news, analysis, video, photos
    Trusted news coverage
    Thanik you Zehabesha

  28. Dear Zehabesha (Alyou Tebeje),

    The phone number provided by your website is not working. Please provide me with a correct one.

    With thanks,

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share