July 31, 2024
12 mins read

የኢትዮጵያ የጦርነት ኢኮኖሚ! እና የማሞ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎች!!!

ፂዮን ዘማርያም (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

eeco 3456696

WHAT IS TO BE DONE? Bombard the Headquarter!!! Régime Chang!!!

የዓለም ባንክና የዓለም ዓቀፍ ገንዘብ ተቆም (አይኤምኤፍ)  የኢትዮጵያን ብር የገንዘብ ምንዛሪ ተመን እንዲያስተካክል በገበያ ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሪ ተመን ሥርዓት (A FREE-FLOATING EXCHANGE RATE SYSTEM) የብሔራዊ ባንክ ይፋዊ የውጪ ምንዛሪ ተመን መሠረት አንድ ዶላር በ57.77 ብር ሲሆን በጥቁር ገበያ 120 ብር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በገበያ መር የውጪ ምንዛሪ ተመን መርህ የሃገሪቱ ኢኮኖሚ እንዲመራና በጥቁር ገበያ ምንዛሪ ተመን ዋጋ እንዲወሰን ወሰኖል፡፡ በጥቁር ገበያ የአንድ ዶላር በ140 ብር ሲመነዘር የአንድ እንጀራ ዋጋ 35 ብር ሆኖል፡፡ ከዓለም ባንክና የዓለም ዓቀፍ ገንዘብ ተቆም 10.5 ቢሊዮን ዶለር ለመበደር እናት አገር ኃብት የሸጠን የብልጽግናን መንግሥት ከሥልጣን ማውረድ ጊዜው አሁን ነው፡፡

  • የኢትዮጵያ ብሔራዊ በጀት 2017 ዓም 17 ቢሊዮን ዶላር ወይም (971ቢሊዮን ብር) በሠላሳ በመቶ ቀንሶ አድሮል፡፡ 301 ቢሊዮን ብር ኪሳራ ተከስቶል፡፡ በተጨማሪ የካፒታል በጀት የሚገዙት ማሽነሪዎች፣ ትራክተሮች፣ መኪኖች፣ ኬሚካል ወዘተ ዋጋ ጨምሮል፡፡
  • የኢትዮጵያ ሠላሳ አንድ ንግድ ባንኮች ተቀማጭ ገንዘብና ካፒታል ኃብት በሠላሳ በመቶ ባንኮች ኪሳራ (Banking Crisis) ደርሶባቸዋል፡፡ እያንዳንዱ ባንክ ያለው ብር በዶላር ሲሰላ ሠላሳ በመቶ ቀንሶ አድሮል፡፡
  • የኢትጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ 50 መንግስታዊ የልማት ኢንተርፕራይዞች የዋጋ ተመናቸው  38 ቢሊዮን ዶላር  የነበረ ሲሆን፣ በገበያ መር የውጪ ምንዛሪ ተመን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ  ሠላሳ አንድ በመቶ ቅነሳ መሠረት 11.780 (አስራ አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ ሰማንያ ሚሊዮን) ዶላር የዋጋ ቅነሳ ተተደርጎባቸዋል ማለት ነው፡፡
  • ለኢትዮጵያብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት ፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት  የአማራ ፋኖ፣ የኦሮሞ ኦነሠ እንዲሁም የትግራይ መከላከያ ሠራዊት የአንድ ክላሸን ኮቨ ዋጋ ከ800 እስከ 1500 ዶላር የነበረ ሲሆንበአሁኑ ገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ተመን እጥፍ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ የህዝብ ኃብት ነውና ይጠበቅ እንላለን፡፡ Mid-Range Models: Mid-range AK-47 rifles from reputable manufacturers might cost between $800 to $1,500, depending on features, quality, and the manufacturer.የኮነሬል አብይ መንግሥት የአንድ ቢሊዮን ዶላር የጦር መሣሪያ መግዛቱ ይታወሳል፣ በቅርቡም ከተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የጦር ተሸከርካሪዎች በብድር ሸምቶል አሁንም የሚያገኘውን ገንዘብ ለጦር መሳሪያ መሸመቻ ማዋሉ አይቀሬ ነው፡፡ አማጽያን ኃይሎች የፖለቲካ ሳይንስ፣ የኢኮኖሚ ሳይንስና የዲፕሎማሲ፣ የዴሞክራሲና የስብአዊነት ትምህርቶችን ጫካ እያላችሁ በምሁራን ማጥናትና መወያየት የጫካ አንባገነኖችንና የመንደር የጦር አበጋዞችን በመዋጋት ወደፊት አገር ለማስተዳደር በህዝባዊ ምርጫ ብቻ እንደሆነ መረዳት ያሻል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት ግፍ ሞልቶ ፈሰሰ፣የኮነሬል አብይ የትሪሊዮን ብር መሬት ሽያጪ ማምከን!!! የሥርዓት ለውጥ የብልጭልጭ ፕሮጀክቶች የገንዘብ ምንጭን ማድረቅ፣ የአዲስ አበባ የትሪሊዮን ብር መሬት ሽያጪ ማምከን!

ለኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት  (Ethioipan National Defence  Force )የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት ግፍ ሞልቶ ፈሰሰ፣ የኮነሬል አብይ የአዲስ አበባ ንዋሪዎችን ካርታ በማምከን ትሪሊዮን ብር መሬት ሽያጪ ፕሮጀክቶች በማስቆም የኦህዴድ ብልፅግና መንግሥት ማውረድ ይቻላል፡፡ የኮነሬል አብይ አህመድ የብልጭልጭ ፕሮጀክቶች የፓርኮች፣ ሎጆች፣ፚፚቴ፣ ወዘተ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለግብርና ልማት፣ለሰው ኃይል ልማት ቢውል ለብዙ ሚሊዮን ሰዎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥነትን ችግር ይቀርፍ ነበር፡፡ የፕሮጀክቶቹ ወጪዎች ከፍተኛ ሲሆኑ ሚሰጡት የስራ እድል ዝቅተኛ መሆን የገቢና ወጪ ጥናት ላይ ያልተመሠረተ እንዲሁም ፕሮጀክቶቹ ግልፅና ተጠያቂነት የማያሳዩ በጋዜጣና ሬዲና ቴሌቢዝን ጫረታ ወጥተው ለኮንትራክተሮች ያልተሰጡ በመሆናቸው እንቃወማቸዋለን፡፡

የዓለም ባንክና የዓለም ዓቀፍ ገንዘብ ተቆም (አይኤምኤፍ) የብልጽግና መንግሥትን እጅ ጠምዝዞ  የኢትዮጵያን ብር የገንዘብ ምንዛሪ ተመን እንዲያስተካክል ገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ተመን ሥርዓት (A FREE-FLOATING EXCHANGE RATE SYSTEM) ወስኖል፡፡ የብሔራዊ ባንክ ይፋዊ የውጪ ምንዛሪ ተመን መሠረት አንድ ዶላር በ57.77 ብር ሲሆን በጥቁር ገበያ 120 ብር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በገበያ መር የውጪ ምንዛሪ ተመን መርህ የሃገሪቱ ኢኮኖሚ እንዲመራና በጥቁር ገበያ ምንዛሪ ዋጋ ተመን ወሰኖል፡፡ በዚህም መሠረት ወደፊት ለመስራት የታቀዱ ፕሮጀክቶች ዋጋ አሁን በሠላሳ በመቶ ወደፊት በእጥፍ እንደሚጨምሩ መገንዘብ ይኖርብናል፡፡

{1} የጫካው ቤተ-መንግሥት ፕሮጀክት (The Chaka Project) የአስራአምስት ቢሊዮን ዶላር ወይም የአንድ ትሪሊዮን ብር

{2} የቦሌ ኤርፖርት ፕሮጀክት፣(The Bole Airport Project) አምስት ቢሊዮን ዶላር

{3} የነገዋ አዲስ ፕሮጀክት፣ (Addis Tomorrow Project) ሦስት ቢሊዮን ዶላር

{4} ላ ጋሃር ፕሮጀክት፣(La Gare Project) ኤግልስ ሂልስ ሁለት ቢሊዮን ዶላር

{5} የመሶቦ ታወር ፕሮጀክት (The Mesob tower) አራት መቶ ሚሊዮን ዶላር

{6} ወሎ ሠፈር ፕሮጀክት (Wello Sefer Project) አራት መቶ ሚሊዮን ዶላር

{7} ሸገርን ማስዋብ ፕሮጀክት (Beautifying sheger Addis Ababa) ሁለት መቶ ዘጠና ሚሊዮን ዶላር

{8} አዲስ አፍሪካን ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ኤንድ ኢግዚቪሽን ሴንተር ፕሮጀክት (Addis Africa International Convention and Exhibition Center) ሁለት መቶ ሰባ ሚሊዮን ዶላር

{9} አዲስ አበባ ኮንቬንሽን ሴንተርስ ፕሮጀክት (Addis Ababa Convention Ceters) መቶ ሚሊዮን ዶላር

{10} የትራንስፖርት ሲስተም ማሻሻያ ፕሮጀክት (TheTransport system Improvement Project) ስድስት መቶ ሰማንያ አንድ ሚሊዮን   ዶላር

የኮነሬል አብይ አህመድ የብልጭልጭ ፕሮጀክቶች የፓርኮች፣ ሎጆች፣ ፚፚቴ ወዘተ ፕሮጀክቶች ለወጣቶችና ለዮኒቨርሲቲ ምሩቃኖች ምንም የሥራ እድል ባለመፍጠራቸው የተነሳ ወጣቶች  ከአገራቸው ተሰደው ለስደት ተዳርገዋል፡-

{11} አንድነት ፕርክ ፕሮጀክት (Unity Park) 50 ሚሊዮን ዶላር ወይም አምስት ቢሊዮን ብር ወጪ በሃያ ሄክትር

{12} የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እድሳት ፕሮጀክት (Renovation of Addis Ababa city hall) በ54 ሚሊዮን ዶላር

{13} አድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት (Adwa center) በመቶ ሃምሳ ስድስት ሚሊዮን ዶላር

{14} አብርሆት ቤተ-መጽሓፍት ፕሮጀክት (City Library) ሁለት መቶ ሚሊዮን ዶላር

{15} የብሔራዊ ቤተ-መንግስት የመኪና ማቆሚያ ፕሮጀክት (National Palace Parking Lot) ሁለት መቶ ሃምሳ ሚሊዮን ዶላር ወይም አምስት ቢሊዮን ብር

{16} መስቀል አደባባይ እድሳት ፕሮጀክት (Meskele Square Redevelopment) ሁለት መቶ ሃምሳ ሚሊዮን ዶላር ወይም አምስት ቢሊዮን ብር

{17} የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮና የሚኒሊክ ቤተ-መንግሥት እድሳት ፕሮጀክት (Renovation: Prime Minister’s Office  and Grand Menelik Palace) ሰባት መቶ ሚሊዮን ዶላር

በሀገሪቱ ቅድሚያ የሚሰጠው ፕሮጀክት፣   

የተባበሩት መንግሥታት የስብዓዊ ጉዳዬች ቢሮ  የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ማርች አንድ ቀን 2024 እኤአ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ በዚህም መሠረት በ2024 እኤአ በኢትዮጵያ ለ15.5 (አስራአምስት ነጥብ አምስት) ሚሊዮን ህዝብ  ሁለገብ ስብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ያስፈልገዋል፡፡  ከኢትዮጵያ ህዝብ 4.4 (አራት ነጥብ አራት) ሚሊዮን ህዝብ የሃገር ውስጥ ተፈናቃዬች ሲሆኑ በተለያዩ ግጭት፣ በጦርነትና፣  የዓየር ለውጥ ቀውስ የተነሳ ሁለገብ ድጋፍ ይሻሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥትና የስብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች በጋራ  3.2 (ሦስት ነጥብ ሁለት)ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡US$3.2 billion required in 2024 to provide multisectoral humanitarian assistance to 15.5 million Ethiopians – Government of Ethiopia, humanitarian community joint appeal. 4.4 million internally displaced people severely impacted by conflict, hostilities and climate shocks require scaled up multi-sectoral assistance.

 

  • የብልጭልጭ ፕሮጀክቶች የገንዘብ ምንጭን ማድረቅ፣የአዲስ አበባ የትሪሊዮን ብር መሬት ሽያጪ ማምከን!
  • በከተሞች ህዝባዊ እንቢተኝነት በቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማና በሌሊቱ ሦስት ሰዓት የኡኡታ ፊሽካና ክላክስና እቃ ማንኮኮት የአድማ ጥሪ ማድረግ ያሻል!!!

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Ephrem Madebo
Previous Story

የሰሞኑ የማክሮ ኤኮኖሚ ጫጫታ

192640
Next Story

 አብይ በፊ/ማ ብርሃኑ ላይ እርምጃ ወሰዱ | በዐማራ ክልል ተባብሶ የቀጠለው ውጊያ | የኦሮሚያው ግዳጅ ውትድርና | ይልማ መርዳሳ በአብይ እጅ ውስጥ ገቡ | ፋ-ኖ ለሽመልስ አብዲሳ ጠንከር ያለ ተግባራዊ ምላሽ ሰጠ |

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop