የ ኢዜማ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ውጤት ማሳወቅ – ስመራጭ ኮሚቴ

ፓርቲያችን በሰኔ ወር በሚያካሄደው 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ፤ ለፓርቲው ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ምርጫ አመልካቾችን ከሚያዚያ 25 እስከ ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ.ም መቀበላችን ይታወቃል።  በዚሁ መሰረት ለዕጩ ተወዳዳሪዎች ግንቦት 17 ቀን 2014ዓ.ም ውጤታቸው በየግላቸው ተገልጾላቸዋል፡፡ በምርጫ ተግባራት የግዜ ሰሌዳ መሰረት የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ ስለተጠናቀቀ፤ የዕጩዎቻችንን አጠቃላይ ውጤት ከዚህ በታች አያይዘናል፡፡
በየደረጃው ለምትገኙ አመራሮች ይህ ምርጫ የፓርቲያችንን ገፅታ በሚገነባ መንገድ፤ የመተዳደሪያ እና የፓርቲያችንን የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብ፤ እንዲሁም የፓርቲውን እሴት ባከበረ መንገድ እንድታከናውኑ እናሳስባለን፡፡
በአስመራጭ ኮሚቴ የግዜ ሰሌዳ መሰረት ሰኔ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ይፋዊ የምረጡኝ ቅስቀሳ ይጀምራል፡፡ ቅስቀሳው ፓርቲውን በሚያጠናክር መልኩ በምክንያት እና በሀሳብ ላይ ሊመሰረት ይገባል፡ ፡ በቅስቀሳ ተግባራት የስነ-ምግባር ደንብ እና በሌሎች መመሪያዎች ከተደነገገው ውጪ ለመንቀሳቀስ የሚሞክር ዕጩ፣ አመራር እና አባል ግንቦት 26 ቀን 2014 ዓ.ም ስራ ላይ እንዲውል በብ/ስ/አ/ኮ በተፈቀደው የጉባኤ እና የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብ መሰረት ተጠያቂ እነደሚሆን ለማስገንዘብ እንፈልጋለን፡፡
በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የምትገኙ የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች ይህ ምርጫ በኢትዮጵያ የፓርቲዎች የውስጥ አመራር አመራረጥ ታሪክ ላይ አስተማሪ ሆኖ እንዲያልፍ የናንተም ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ሕግ እና ስርዓት እንዲከበር የበኩላችሁን አስተዋፆ እንድታበረክቱ በአክብሮት እንጠይቃለ፡፡
ስመራጭ ኮሚቴ
ተጨማሪ ያንብቡ:  ብሔራዊ ምርጫን የማካሄድ ሥልጣንና ሕገ መንግሥቱ (ለውይይት መነሻ) ባይሳ ዋቅ-ወያ

3 Comments

  1. ብርሃኑ አሁንም ለውድድር ገባ ማለት ነው? አይ አፍሪካ እዜማም ብአዴንን ሆነ ማለት ነው? ተስፋ ያለውን ድርጅት ሰለቡት አስመራጭ ኮሚቴው ሽመልስ አብዲሳ መሆን አለበት ።

  2. I hate to say but I have to say that this is neither an interesting news nor something that could make any significant difference in the very real sense of politics at all! Changing one puppet of the ruling party with another one and claiming as if it is a democratic practice is total a total political stupidity and a moral dishonesty!

  3. ብሬ ተገዶም ቢሆን ቦታውን ቢለቅ መልካም ነው ሊሰጠው የሚችለው ብዙም ነገር የለውም በየሄደበት ነገር ማበላሸት ነው። ይሄ ፕሮፌሰር የሚለው ቅጥያ ብዙ ሰው ሳያደናግር አልቀረም ምንም ማለት አይደለም እድሜውም ነጉዷል ቢከስርም ቢያተርፍም ሰውን ወደማይጎዳበት ወደራሱ ቢዝነስ ቢሄድልን? እርስ አይሰለቸውም ወይ በዘመናት ሁሉ ደንቃራ መሆን ለክፉዎች ድንጋይ ማቃበል። ኤርምያስ አመልጋ ኢኮኖሚስት ነኝ ቢል ተቀባይነት ይኖረዋል የዚህ ግን ከምንም የሚመድቡት ሰው አይደለም ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share