December 9, 2024
4 mins read

አስቸኳይ ጥሪ ከአርበኛ ዘመነ ካሴ ለመላው የአማራ ህዝብ!

zemene Kassieእንደምን ሰነበታችሁ?አርበኛ ዘመነ ካሴ ነኝ።
ህዳር 27-2017 አም አርብ እለት ድርጅታችን የህዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ላልተወሰ ጊዜ የሚቆይ የአገልግሎት ተቋማት እቀባ እና የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ክልከላ መመሪያ ማስተላለፉ ይታወቃል።

ትዕዛዙ ከሰኞ ሕዳር ሰላሳ ቀን 2017 ዓ. ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን ጥሪው የስራ ማቆም አድማን የሚጨምር መሆኑን በድጋሜ ማሳወቅ እወዳለሁ። ይህን ትእዛዝ ተላልፎ የተገኜ ግለሰብ ወይንም ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል።አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዳለቀ በጥቂት ቀናት ውስጥ የአውሮፕላን በረራንም ላልተወሰነ ጊዜ ሙሉ በሙሉ የምናስቆም ይሆናል።

በዚህ አጋጣሚ ለመላው አማራ አርሶ አደሮችና የከተማ ነዋሪዎች አንድ አጭር ግን ታሪካዉ ጥሪ ማድረግ እንፈልጋለን።እንደሚታወቀው ገና ከፅንሰቱ የአማራን ህዝብ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ አስፈትቶ ዱላ እንኳን ከልክሎ ፥የህዝባችን ጉልበትና ወኔ መስለብ የሚችልበትን ጊዜና አጋጣሚ ሲጠብቅ የቆየው ጠላት በተለይ በዚህ ወር ውስጥ የአባውራ ቤት ሰብሮ እየገባ የአርሶ አደሩንና የከተማ ነዋሪውን መሳሪያ እየነጠቀ ይገኛል።

መሳሪያውን ከአማራው አርሶ አደርና ከተሜ እጅ ነጥቆ በስነልቦናም በጉልበትም ባዶ የሆነ አማራን ከመፍጠር ባለፈ የነጠቀውን መሳሪያ ጎዳና ላይ አፍሶ ወደ ውትድርና ማሰልጠኛ ተቋማት ላጋዛቸው ህፃናት ሊያስታጥቀው መዘጋጀቱን ድርጅታችን ደርሶበታል።ስለዚህ የአማራ ህዝብ ሆይ ለስነልቦናህ ጋሻ፥ለማንነትህ ዋሻ፥ለቤትህና ለበረትህ መከታ፥ለቤተሰብህ አለኝታ፥ለታሪክህና ነባር እሴትህ ዋልታ የሆነውን መሳሪያህን እንድትጠብቅ አደራ እንላለን።ሁለት አማራጮች እጅህ ላይ አሉ፥

1)መሳሪያህን ይዘህ ፋኖን በመቀላቀል ዘላለማዊ ጠላትህን ለዘለአለም ማሸነፍ እና ህልውናህን ማረጋገጥ

2)በየአካባቢህ ለሚገኝ የፋኖ መዋቅር በጊዚያዊነት በውሰት መስጠት።

የአማራን ህዝብ ከጥጃ ብረቶቹ እና ጥጆቹ ለይተህ ማሰብ አይቻልም። እስትንፋሶቹ፥ክብሩና ኩራቱ፥የማንነቱ አስኳሎች ናቸው።ጥጆቹ አለሙ የጥጃ ብረቱ ቅስሙ ናቸው።ስለዚህ ሁሉንም ዋጋ ከፍለን እንጠብቃቸዋለን።በዚህ ሂደት ውስጥ አርሶ አደሩና የከተማ ነዋሪው ተባባሪ እንዲሆን አደራ እንላለን።

(አንድ ህዝብ፥አንድ ትግል፥አንድ ድል!!)
(ክፋት ለማንም በጎነት ለሁሉም)
(አዲስ ትውልድ፥አዲስ አስተሳሰብ፥አዲስ ተስፋ)

ህዳር 29/2017 ዓ.ም
©️አሻራ ሚዲያ

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop