September 12, 2024
2 mins read

ንጉሰ ነገስቱ ከስልጣናቸው እንዲወርዱ የተቋቋመው የደርግ አባላት በቀረበው ትዕዛዝ በሻለቃ ደበላ ዲንሳ የተነበበላቸው ደብዳቤ

መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም

ከ 48 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት

GXQtoP9WwAA4 OS

ንጉሰ ነገስቱ ከስልጣናቸው እንዲወርዱ የተቋቋመው የደርግ አባላት በቀረበው ትዕዛዝ በሻለቃ ደበላ ዲንሳ የተነበበላቸው ደብዳቤ

ሻለቃ ደበላ ዲንሳ ለንጉሱ ሰላምታ ካቀረቡ በኃላ ንግግራቸው ጀመሩGXQtoP XcAA8RvI

ምንም እንኳ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የኖረው ዘውድ ህዝቡ በቅን ልቦና የአንድነት ምልክት ነው ብሎ የሚያንበት ቢሆንም ከ ሃምሣ አመታት በላይ ከአልጋ ወራሽነት ጀምረው ሃገሪቷን ሲመሩ ከህዝብ የተሰጦዎን ክብር ስልጣን አልአግባብ በልዩ ልዩ ጊዜ ለራስዎና በአካባቢዎ ለሚገኙት ቤተሰቦችዎና ለግል አሽከሮችዎ ጥቅም ላይ በማዋል ሃገሪቷን አሁን ላለችበት ችግር ላይ እንድትወድቅ ከማድረጎም በላይ እድሜ ሰማንያ ዓመት በመሆኑ በአካልም ሆነ በአዕምሮ በመድከመዎ ከእንግዲህ ወዲህ ይህን ሃላፊነት ሊሸከሙ አይችሉም።

ንጉሠ ነገሥቱ:

ያላችሁትን በጥሞና አዳምጠናቹኃል። ለሀገር በጎ አስባችሁ ከተነሳችሁ የአገር ጥቅም ከራስ ጥቅም ማስቀደም አይቻልም። እኔ እስከ ዛሬ አገራችንና ህዝባችንን አቅማችን በፈቀደውና በምንችለው ሁሉ አገልግለናል። አሁን ተራው የኛ ነው ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ

 

ሻለቃ ደበላ ዲንሳ:

ለግርማዊነትዎ ሲባል ሌላ ቦታ የተዘጋጀ ስለሆነ ወደ ተዘጋጀልዎ ስፍራ እንዲሄዱ እጠይቃለሁ ።

ከዚያም ከቤተመንግስት በቮልስ ዋገን መኪና ኮሎኔል ዳንኤል አስፋው በመሾፈር ወደ ተዘጋጀላቸው ስፍራ ማለትም ወደ አራተኛ ክ/ጦር ተወሰዱ።

Ethio

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Go toTop

Don't Miss

ዋለልኝ መኮንን

ዋለልኝ መኮንን ዳግም ሞቷል! – ሙሉዓለም ገ/ መድህን

“ዋለልኝ መኮንን” የሚለው ሥም በኢትዮጵያ (የቅርቡ) የሃምሳ ዐመት ፖለቲካዊ ትርክት
walelegn and Marta

ከታሪክ ማህደር: ዋለልኝ መኮንን ማነው ? ያልተሳካው የአውሮፕላን ጠለፋ

ህዳር 29 ቀን 1965 ዓ.ም ከ 50 ዓመት በፊት ልክ