የጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ ስንብት (በፍርድ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደጃዝማች ዘውዴ ገ/ሥላሴ አገላለጽ)

መጋቢት 21 ቀን 1953 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 63 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የታኅሣሥ ግርግር በመባል በታሪክ መዝገብ የሚታወቀውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በግንባር ቀደምነት ያካሄዱት የነበሩት የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ በተቀበሉት ፍርድ መሠረት በስቅላት የተቆጡበት ዕለት ነበር።

የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ
የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ

የእልፍኝ አስከልካዩ ኮሎኔል አሰፋ ደምሴ (በኋላ ጄኔራል) መጋቢት 20 ቀን 1953 ዓ.ም ከሌሊቱ 9፡00 ስልክ ደውሎ “የጄኔራል መንግሥቱን የሞት ቅጣት ፍርድ ጃንሆይ አጽድቀውታል፡፡ ቅጣቱን በጧቱ እንድታስፈጽም አዘዋል፡፡

አንደኛ ክፍለ ጦር መድፈኛ ግቢ በቶሎ እንገናኝ” አለኝ፡፡ እንዳለኝ ቶሎ ተዘጋጅቼ ከተባለው ቦታ ስደርስ፣ ሽብር የተነሣ ይመስል በአካባቢው የነበረው ግርግር ሌላ ነበር፡፡ ከዚያ ለጄኔራል መንግሥቱን ሰላምታ ከሰጠሁት በኋላ የሞት ቅጣቱ የሚፈጸመው በዕለቱ ጧት መሆኑን ነገርኩት፡፡ ምንም ዐይነት የመደንገጥ ወይም የመናደድ ነገር አላሳየም፤ ምንም አልመሰለውም፡፡ ዝም ብሎ ተቀበለው፡፡

ኮሎኔል አሰፋ ቀለም ከመነከሩ በቀር በጣም ተራ የሆነ ስስ መርዶፍ፣ እጅጌው አጭር ሸሚዝና ቁምጣ ሱሪ የወህኒ ልብስ አምጥቶ ኑሮ “ያን ይልበስ” አለ፡፡ “አይሆንም” ብዬ በመጨቃጨቅ ጊዜ ካሳለፍን በኋላ፣ እኔ “ለጃንሆይ ይነገር እንጂ ይህንን ልብስ አልብሼ ቅጣቱን አላስፈጽምም” ስላልኩ፣ ሌሊት ጃንሆይ እንዲሰሙት ተደርጎ “እሽ የራሱን ልብስ ይልበስ” ብለው ስለፈቀዱ፣ የራሱን ልብስ ከለበሰ በኋላ በስሪ ኳርተር መኪና ላይ “ተሳፈር” ስንለው፣ “እሱን እሺ፤ ነገር ግን አንድ ጥያቄ አለኝ፤ ብትቀበሉኝ” አለ፡፡ “እሺ ጠይቅ” አልነው፡፡

“እዚህ ያሉት ወታደሮች ባይኔ አጥርቶ አለማየት ምክንያት ወደ ሽንት ቤት ስሄድ እቸገር ስለነበር ደግፈው ወስደው በማድረስ፣ በመመለስና የሚያስፈልገኝን ሁሉ በማድረግ ውለታ ውለውልኛልና እንዳመሰግን ብትሰበስቡልኝ ፈቃዳችሁን እጠይቃለሁ” አለ፡፡ ፈቀድንለትና የተሰበሰቡትን አመሰገናቸው፡፡ ወታደሮቹ ወጣቶች ስለነበሩ በሁኔታው መቆጨትና ማዘናቸው በፊታቸው ላይ ይታይ ነበር፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከታሪክ ማህደር : ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የመሯት ስድስቱ የኢትዮጵያ ብፁዓን አቡነ ፓትሪያርክዎች

ከዚያ በስሪ ኳርተሩ ላይ ተሳፍሮ በብዙ ወታደሮች ታጅቦ ተክለሃይማኖት አደባባይ ከመስቀያው ቦታ እንደ ደረስን፣ ወደ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዞሮ እጅ እንዲነሣ አደረግን፡፡ ከዚያ ገመዱን ከዐንገቱ ላይ ሊያገቡ ሲሉ ኮሎኔል አሰፋ ደምሴ “አላይም” ብሎ መሄድ እንደ ጀመረ፣ [ጄኔራል መንግሥቱ] “ጥሩት” ብሎ አስጠራውና “እባክህ እነዚህ ሰዎች አያውቁትምና የገመዱን ቋጠሮ በተገቢው ቦታ እንዲያደርጉት ንገርልኝ” አለው፡፡

ይህን ያለበት ምክንያት በላይ ዘለቀ ሲሰቀል ገመዱ በትክክለኛው ቦታ ባለመሆኑ የደረሰውን ሥቃይ ዐይቶ ስለነበር ነው፡፡ እሱም “እሺ” ብሎ ለሰዎቹ ነገራቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ገመዱን በተገቢው መንገድ አደረጉለትና መኪናው ወደፊት ሄደ፡፡ ብዙም አልቆየ፣ ነፍሱ ወዲያው ዐለፈ፡፡

#ታሪክን_ወደኋላ

ቴሌግራም- t.me/TariknWedehuala

4 Comments

  1. እንቶ ፈንቶው ጸሐፊ

    አሁን ይኸንን በዚህ ሰዓት የምትቀባጥረው ምን ለማትረፍ ነው? ይልቅስ ሰው ተሆንክ አሁን ስላለው ሕዝብንና አገርን ማጥፋት አተነፍስም?

    እፊትህ ያለው ሳይታይህ ያላየኸው የድሮው ቁልጭ ብሎ ታየህ? ስንቱ አይነት ከንቱ ሞልቷል፡፡

  2. Tiru mastawesha new.
    Ye tariku tenagari (tsehafiw/derasiw sayhon) sim yalteTeqesebet miknyat mindin new?
    Beiyzawim
    1. Mengistu neway ye Belay Zelleqen siqilat yasfetseme indeneber
    2. yenne Mengistu mefenqile mengist be gibts in amerika yeteqenabere indenebber
    3. yetegedelut sewoch abzagnochu Ityopiya bemigib rasuan yemiyaschilatin ye nigussu ke rusya gar yetederege ye million rubloch wul yedegefut temerTew indenebber
    biTeqesibet yetarikun awd yetmuala inna Ityopia yallebatin fetenam yemiTequm yadergew nebber.

  3. እውቁ ገጣሚ ሻምበል አፈወርቅ ዪሃንስ ”
    ሂዶ ተመልሶ የሚነግረን ጠፍቶ፤
    የመቃብር ዓለም ይኖራል ተፈርቶ”
    በማለት በጊዜአቸው በተግባር አሸብርቀውና ለቀሪው ትውልድ ሥራ ሰርተው አልፈዋል። የእኛ ችግር እጅግ ውጥንቅጡ ከመብዛቱ የተነሳ እኖራለሁ በማለት ሌላውን የሚያሰቃየው ራሱ ተመልሶ ተሰቃይና ሟች ሲሆን ማየት የተለመደ የመጠላለፍ የፓለቲካ ስልት ነው። በታህሳሱ ግርግር ከተገደሉት ወደ 15 የሚጠጉ ሰዎች መካከል ብዙዎቹ ለሃገራቸው በሰው ሃገርና በበረሃ የተንከራተቱ ነበሩ። ለምሳሌ አቶ መኮነን ሃብተወልድን ብንወሰድ ለሃገራቸው ብዙ የለፉ፤ የበራ እይታ የነበራቸው እንደነበሩ ይነገራል። ግን ያው በግፍ የተሞላው የመገዳደል ፓለቲካ እሳቸውንም በላቸው። የሚያሳዝነው ወንድማማቾቹ አካለወልድ እና እውቁ አክሊሉ ሃብተወልድን እንበለ ፍርድ ድርግ በጅምላ ረሸናቸው። በሁለቱ ስመ መኩሸዎች መንግስቱ ንዋይና መንግሥቱ ሃ/ማሪማ ሶስቱም ወንድማማቾች ተገደሉ። የመገዳደል አዙሪት ይሉሃል ይሄ ነው!
    የጄ/መንግሥቱ ንዋይ የመጨረሻ ሰአታትም ሆነ የነበረው ህልም አይጻፍ፤ አይዘከር የሚሉ ጅሎች ታሪክን ለማወቅ አለመፈለገ ነው። ችግሩ ጄ/መንግስቱ በላይ ዘለቀ ከእነ ወንድሙ ሲሰቀል ቆሞ ሲያይ የሚኖር መስሎታል። አልሆነም። እሱም እጣ ደረሰው፤ ሌሎችም ጄ/መንግስቱ ሲሰቀል ቆመውም ሆነ በሩቅ ከንፈራቸውን የመጠጡ ወይም እርሱ በሞት እንዲቀጣ በዚህም በዚያም ሴራ የሸረቡ ሁሉ በአንድ ጉድጓድ ነው የተጨመሩት። ያኔም ሞት አሁንም ሞት። ነገም ሞት። እልፈተ ቢስ ፓለቲካ!
    አሁን እንሆ የብልጽግናው መንግስት ወያኔን ለማስተናገድ የሚያደርገው ሽርጉድ ሁሉ አይሰራም። ወያኔ በኮረም በኩል ያስጠጋው ሃይል የዋግህምራና የአበርገሌን ወረዳዎች ሲቆጣጠር እዚያ ያለው የመከላከያ ሃይል ገላጋይ ሆኖ እየሰራ ነው። ሚሊሻው ለምን ብሎ ሲነሳ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር እንዲጠብቅ የተላከው ሰራዊት ተው እኛ እንለምናቸዋለን ወደ መጡበት እንዲመለሱ በማለት ህዝቡ እንዳይመክት በመከላከል ላይ ይገኛሉ። ከዚያም አልፎ በራያ በጠለምት በወልቃይት ታጣቂን በማስወጣት መከላከያን በማስፈር አዲስ አስተዳደር ለመፍጠር የሚደረገው መፍጨርጨር ሁሉ የእንቧይ ካብ ነው። እንዴት ነው በቋንጨራ የሰው አንገት የቀላው፤ ሰውን ከቤቱና ከህክምና ጣቢያ ጎትቶ ወስዶ የረሸነው የወያኔ ስብስብ በሰላም አብሮ የሚኖረው? ግን ያው የአሜሪካ ተላላኪዎች መቀሌ እንዲህ የሚያመላልሳቸው ለትግራይ ህዝብ ወይም ለኢትዮጵያ ሰላም አስበው ሳይሆን ለራሳቸው የፓለቲካ ስልት ሜዳ ለመቀየስ ነው። ያው እንደምናየው ሩሲያ ከኤርትራው የእድሜ ልክ መንግስት ጋር ጥምረት በመፍጠሯ ተቸግረዋል። የአሜሪካ ዓላማ ቢቻል ወያኔን ወደ ስልጣን በመመለስ ካልሆነ የብልጽግናውን መንግስት በማሳመን ኢትዪጵያ ከኤርትራ ጋር እንድትላተም ለማድረግ ከተያዘው ሰፊ እቅድ አንድ ነው።
    በሌላ ጎኑ በፋኖና በመከላከያ ያለው ፍትጊያ የአማራን ህዝብ የመከራ ዶፍ እያዘነበበት ስለሆነ ወያኔ ግልጽ ወረራ በሚያደርግበት ጊዜ በምንም መልኩ ራሱን መመከት የማይችልበት ሁኔታ ላይ ጥሎታል/ይጥለዋል። ስለሆነም የአማራ ህዝብ መከራና ሰቆቃ በሶስት ሃይሎች የሚፈጸም ይሆናል። በኦነግ፤ በወያኔና በብልጽግናው መንግስት። አሁን ያዙኝ ልቀቁኝ የሚሉት ፋኖዎች ረጋ ብለው ማሰብ ያለባቸው ነገር ህዝቡ እየተጎዳ፤ ልጆቹን እየገበረና እያስገበረ ከመከራ ወደ ሌላ መከራ እየተንደረደረ እንጂ ሰላም ነጻነት የሚባለው ነገር ሁሉ ጭላንጭሉ የማይታይ ዘራፊዎችና ቀሚዎች የሚራኮቱበት ህግ አልባ ክፍለ ሃገራት ሆነዋል። ጦርነት የአንድ ትግል የመጨረሻ ምርጫ ነው። በአማራ ህዝብ ላይ የሄደ የመጣው የሚፈነጨው ጊዜ ሰጠኝ ብሎ ነው። ችግሩ እኛ ነን የከተማና የገጠር አለቆች ሲሉን የፓለቲካ ንፋሱ አቅጣጫ እየቀየረ የቆመው ሲወድቅ፤ የወደቀው ሲነሳ በዘመናችን አይተናል። የአፍሪቃ ቀንድ ችግር ከውጭም ከውስጥም በመሆኑ እሳቱ የሚዳፈን አይሆንም።
    አሁን እንሆ የሞቃዲሾው መንግስትና የሃርጌሳው መንግስት ሊላተሙ እንደሚችሉ የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ። መቃዲሾ በቱርክ እየተደገፈች፤ ፑንትላንድ ደግሞ በኤሜሬትስ የዘይት ሃብት አይዞሽ እየተባለች ሲላተሙ ጪሱም ሌላውም ለኢትዮጵያ ጉዳት እንጂ ጥቅም አያመጣም። ኤርትራም በራሺያና በሌሎች ነባር የኢትዮጵያ የዓረብ ጠላቶች እየተረዳች የትግራይን መሬት ተሻግራ እኔንም እዪኝ ማለቷ አይቀሬ ነው። ጄ/መንግስቱ ንዋይ ካለፈ አሁን ወደ 63 ዓመት ገደማ ሆነው። ኢትዮጵያ ግን እነርሱ ጥለዋት ከሄድልን ሃገር በምንም ያልተሻለች የአፓርታይድ ምድር ከሆነች እንሆ አሁን 34 ዓመታት አለፈን። ታዲያ ነገሩ ሁሉ እንዲህ ጨለማ ከሆነ ያለን ምርጫ ምን ይሆን? አላውቅም። ግን እጅግ አስፈሪ ጊዜ ላይ ቆመናል። የታህሳሱ ግርግር (የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ) ያስተማረን ምን ይሆን? አሁንስ በፋኖና በመከላከያ የሚደረገው ፍልሚያ ትርፉ ለማን ይሆን? መልሱን በውል የሚያውቅ የለም። በምድር ላይ አሁን ያለው ሁኔታ የሚያሳየን ግን ሰቆቃና ሞትን ብቻ ነው። ትርፍ የለሽ የመገዳደል አባዜ ይብቃ!

  4. ከግርማሜ ሞት በኋላ ኑሮ ዋጋ የለውም ባዩ መንግስቱ ይቅርታ እንዲጠይቅና በሂይወት እንዲኖር ምርጫ ቀርቦለት ነበር፣ የእርሱ መልስ ግን የጀመርነው የኢትዮጵያ ድህነት ጉዳይ ስር እንደሰደደ ለጓዶቼ ልነግራቸው ቸኩያለሁኝና ይልቁንስ ቶሎ በሉ ኣሰናብቱኝና ለሞቱት እላኛው ቤት ዘንዳ መልእክቱን ላድርስ በማለት የመጨረሻውን የሞት ፍርድ ሰጥቶ ነው የተሰቀለው !
    ከእርሱ በኋላ የተሰቀሉት ሁሏ የኢትዮጵያ ድህነት እስካሁንም እንዳልተከሰተ ምናልባት ኣድርሰውለት ይሆንን ?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share