March 30, 2024
3 mins read

እንኳን ሞት አለልህ!

Death

መኖሩን እያወክ ሞት ቆሞ ተደጅህ፣
ጭራቅ ያገለገልክ ተገዝተህ በሆድህ፣
መሞት ባይኖርማ ባህር ደም በጠጣህ፣
ንጹሑን ፃድቁን በካራ አሳርደህ!

እርጉዝ በጎራዴ በጦቦያ አስመትረህ፣
ፖለቲካ ዝሙት መደመር አጡዘህ፣
አምላክን ህሊናን ልቡናን የጎዳህ፣
ሁሉን የማይተወው እንኳን ሞት አለልህ፡፡

ቲቪና ራዲዮ ዘጋቢ ነኝ እያልህ፣
ግድብ ውሀ ሙላት እየለፈለፍክ፣
ዜጎች በዘራቸው ተቀልተው እያየህ፣
የዘር ማጥፋት ወንጀል ሆን ብለህ የደበክ፣
እንደ ጎርፍ የሚወስድ እንኳን ሞት አለልህ፡፡

አስር ሰላሳ ዓመት የቀጠልክ መስሎህ፣
ሞልተህ የማትመርገው ከርስህ አስገድዶህ፣
ዘሩ እየተጠራ ሲታረድ ወገንህ፣
ለጥ ብለህ የተኛህ እንጀራ እየጎረስክ፣
እንኳንም ሞት አለ ጠርጎ የሚወስድህ፡፡

እርጉዝ ስትመተር ህሊናህ ሳይወቅስህ፣
ሽፍንፍን አድርገህ ማለፍን የመረጥክ፣
በአንተም የሚመጣ እንኳን ሞት አለልህ፡፡

ፒ ኤች ዲ ዲግሪ ማስተርስ አለኝ እያልክ፣
ድስኩር ስትደሰኩር አለሁ ስትል ከርመህ፣
መደመር ግድብን ፈንድ ፈንድዱ እያልክ ፣
ለነፍሰ ገዳዮች ልሙጥ ካድሬ ሆነህ፣
ዘር ፍጅት ሲፈጠም ምላስክን የለጎምክ፣
ተፊትህ የቆመ እንኳን ሞት አለልህ፡፡

እንደ ብፁእ ቅዱስ ቆብ ተራስህ ደፍተህ፣
ተአንገት ተደረትህ መስቀል አንዠርገህ፣
ክርስቲያን ሲታረድ ድሎትህ አታሎህ፣
በሟች አስራት ፍርፍር ክቶፍህን እየዋጥክ፣
በጎችህን ቆመህ በካራ ያሳረድክ፣
እንኳንም ሞት አለ ችሎት የሚያቀርብህ፡፡

በአሪዎስነትህ መጣፍ የሚያወሳህ፣
በአድርባይነትህ ታሪክ የሚከትብህ፣
በሆዳምነትህ ትውልድ የሚወቅስህ፣
የዘር ፍጅት ወንጀል በመሸፈን ያለህ፣
ረስቶ እማይቀረው እንኳን ሞት አለልህ፡፡

አቶ ሞት እያለ ያን ያህል ተከፋህ፣
መሞትማ ባይኖር የት ይደርስ ኃጥያትህ፣
አስቆርቱ ይሁዳ ሰማእትን የከዳህ፣
እንኳንም ሞት አለ ሲው አርጎ እሚወስድህ፡፡

በላይነህ አባተ ([email protected])
ሐምሌ ሁለት ሺ አስራ ሁለት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
Go toTop