ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት እና ራያ የመላ አማራ ሕዝብ ቀይ መስመሮች ናቸው!!! – ተዘራ አሰጉ ከምድረ እንግሊዝ።

Demeke Zewdu (Col.), the founder and leader of the Wolkite Identity and Restoration Committee - Wolkite, it is a matter of restoring a lost identity.
Demeke Zewdu (Col.), the founder and leader of the Wolkite Identity and Restoration Committee – Wolkite, it is a matter of restoring a lost Indigenous People.

ሰሞኑን በየሚዲያው (በይነ- መረቦች) የሚናፈሱ ውል የለሽ ወሬዎች እየተንሸራሸሩ እና ብቅ ብቅ እያሉ ይገኛሉ።

እነዚህም የኩሸት ወሬዎች እና ሴራዎች “ኮለኔል ደመቀ ዘውዱ ከአማራ ፋኖ ትግል እራሱን አገለለ” እንዲሁም ወልቃይት እና ራያ ከአማራ ማንነታቸው ተነጥለው እራሳቸውን ችለው ክልል ሊሆኑ ነው” የሚሉ ይገኙበታል።

ከሁለተኛው ፍሬ ፈርስኪ ማለትም “ወልቃይት እና ራያ ከአማራ ማንነታቸው ተነጥለው እራሳቸውን ችለው ክልል ሁነው ሊዋቀሩ ነው” የሚለውን ተልካሻ ወሬ እና ሰማይ እና ምድር ቢደበላለቅ እውን ሊሆን የማይችለውን ትርኪ -ምርኪ ህሳቤ ስንገምግመው።

ወልቃይቴዎች የኖህ ልጅ የሆነው አባታችን አኩኖ -ወሳባ ከክርስቶስ መወለድ በፊት በ224 ምዕተ ዓመት ከወለዳቸው ልጆቹ ማለትም ከበለው ፣ ከከለው ፣ ከአገው ፣ ከኖቫ ፣ ከላካዶን እና ከሳቫዝ መካከል የአማራው ነገድ የሆነው ከላይ ከተጠቀሱት ወንድማማቾች እና እህትማማቾች መካከል “የከለው” ነገድ ወልቃይትን የመነጠረ እና የተፈጠረበት ምድር መሆኑን በታሪክ የተዘገበ እና ተከትቦ የሚገኝ ሃቅ ነው።

ይህን መሰረት አድርገን ይህን አጓጉል እና ፉርሽ የሆነ የአማራ ጠላቶች ልፈፋ ስናየው የአማራ መነሻ እና መሰረት የሆኑትን ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት እና ራያን “ምን ብለው ሰይመው ሊከልሏቸው” እንደሆነ ግራ የሚያጋባ ቢሆንም እነዚህን የአማራ ውብ እና ለም ዐፅመ እርስቶች በማናለብኝነት ፣ ከእውቀት ነፃ በሆነ አካሄድ እና ታሪክን አዛንፈው “ሊበሏት የአሰቧትን አሞራ ዥግራ ናት ይሏታል” እንዲሉ ይህን ቅዠት የተሞላበት  ህሳቤያቸውን እነብልፅግና እና አጋሮቻቸው ለመተግበር የሴራ ፖለቲካ እያካሄዱ መሆኑን ቁልጭ ብሎ እየታየ መጥቷል።

የቤተ – ሙከራው እንጭጭ ስሌት እንደሚያሳየው ወልቃይት እና ራያ ራሳቸውን ችለው ክልል ቢሆኑስ የሚል ፉርሽ የሆነ ፅንሰ ሃሳብ በአማራው እና በመላ ኢትዮጵያውያን ልቡና እና አስተሳሰብ ለማስረፅ እንደተፈለገ ቀመረ ስሌቱና ሴራው ቁልጭ እና ግልፅ ሆኖም እየታየ እና አየተለፈፈ ነው።

ያም ሆነ ይህ ፣ ግራ ነፈሰም ቀኝ “ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት እና ራያ እንደ ሲዳማ ራሳቸውን የቻሉ ክልሎች ቢሆንስ”  የሚልውን ህሳቤ  በአማራው ዜጋ ስነ-አዕምሮ ውስጥ ለማስረፅ የሚደረገው መፍጨርጨር እና ሙከራ ሚዛን የማይደፋ እና ተግባራዊ ሊሆን የማይችል ፣ የብልፅግና መንግስት የተለመደ ዝብረቃ ከመሆኑም ባሻገር  የአማራን ህዝብ በዚህ የውዥንብር ንድፈ ሃሳብ ለመነጣጠል እና ለማጋጨት መሞከሩ ከማይወጡበት አዘቅት የሚያስገባ እና ከባድ የሆነ ዋጋም እንደሚያስከፍል እንቅጩን ልንነግራችሁ እንወዳልን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የግብጽ ምሁራን ግድቡ አደጋ ይፈርሳል ይሉናል፡፡ በእኛስ ምን እየሠራን ነው? - ሰርፀ ደስታ

“ማንን ይዞ ጉዞ” እንዲሉ ወልቃት ጠገዴ ፣ ጠለምት እና ራያን ከአማራ ነጥሎ ማሰብ “አባይን ያለ ጣና ፣ ተከዜ ፣ ርብ እና ገባሪ ወንዞች እንደ ማሰብ” መሆኑን እነ ብልፅግና ሊረዱት ይገባል እንላለን።

የዚህ ፅሁፍ ከታቢ እንደወልቃይት ተወላጅነት በተለያዩ የአማራ አደረጃጀት ስብሰባዎች እየተገኘ የወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት እና የራያ የአማራ ዕፅመ ዕርስት ባለቤትነት ጥያቄዎች የአማራ ዋና አንኳር ጥያቄ እንደመሆናቸው በየመድረኩ እንደማይነሱ ፣ የመቀዝቀዝ አካሄዶች እንደሚታይ እና በጉዳዩ ላይ ትኩረት ያለመስጠት እዝማሚያ እንዳለ ቢወተውትም ማሳሰቢያው እና ጉትጎታው አድማጭ እንዳላገኘ ትዝብቱን እየገለፀ እና ዝምታው አሳሳቢ እንደሆነም አስረግጦ ያስረዳል።

ህወሃቶች ፣ አፍቅሮት ህወሃት አቀንቃኝ የሆኑ ሚዲያዎች (በይነ-መረቦች) ፣ ወልቃይት እና ራያን በህልማቸው የሚያርዮ ፣ በውንም ፣ በመወለድም ሆነ በመኖር የማያውቋት ትህንጋውያን “ወልቃይት እና ራያን”  “ውሸት ሲበዛ እውነት ይመስላል” እንዲሉ ዘወትር ሲያነሷት ፣ ሲኮለታተፉባት እኛ ባለቤቶቿ አማሮች ግን “በእጅ የያዙት ወርቅ እንደ መዳብ ይቆጠራል ” እንዲሉ በየስብሰባው እና መድረኩ ከማንሳት ተቆጥበናል፣ ብዙም ጫና እየፈጠርን አይደለም ፣ የወልቃይት እና የራያን ሕዝብ የትግል አጋርነት ከጎንደር ሕዝብ ባሻገር በሌሎች አካባቢዎች ያሉ አማሮች ችላ ሳይሉ የፋኖን ትግል እያጧጧፉ ሊወተውቱ እና አጋርነታቸውን ሊያሳዩ የግድ የሚላቸው ጊዜ አሁን መሆኑን እናሳስባለን።

የወልቃይትና የራያን ጥያቄ “ ዝም አይነቅዝም” በሚል ትብዕል ዝምታን ካበዛንበት ፣ በንቃት ካልጎተጎትን እና አርማችን አርገን እኛ አማሮች በሚመለከተው ዓለም አቀፍ ሆነ ሃገር አቀፍ መድረኮች ላይ ጥያቂያችንን ካላቀረብን እና ካላሳሰብን “ ጥያቄውን ችላ ብለውታል” በሚል ህሳቤ ተፃራሪዎች እና የጎመጁት ትህነጋዊያን የአማራን ሕዝብ የመለያያ አጀንዳ አድርገው እንደሚጠቀሙበት እና እያደረጉት መሆኑኑ ልንገነዘብ የግድ የሚለን ጊዜ ላይ ደርሰናል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሳይቃጠል በቅጠል! - አበበ ገላው

ሌላው ጉዳይ ትግል (የፖለቲካ ንቅናቄ) የመሪዎችና የግለሰቦች ጉዳይ ሳይሆን የሕዝብ የደቦ እና የጋራ መፍትሄ ፣ ነፃነት ማስገኛ እና የስልጣን መጨበጫ መሳሪያ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል።

ይህን መሰረት አድርገን የ2005ቱን የአማራ ትግል ጎንደር ላይ ሆኖ ፋና ወጊነቱን ያሳየው ፣ ትግሉ እንዲጎመራ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ “ጭቆና ሞት በቃኝ እና እንቢ አልገዛም” ባይነቱን በጋራ አጠንክሮ በማቀንቀን ህወሃት መዲናዋን አዲስ አበባን “ያሁላችው” ብላ ወደ መቀሌ እድትሸሽ ያደረገውን ኮለኔል ደመቀ ዘውዱን የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ “ ከፋኖ ትግል እራሱን አሸሸ” ብሎ መቀባጠር ውሃ የማይቋጥር መሆኑን ልንገነዘብ ይገባል።

ለወልቃይት እና ራያ ሕዝብ ስለፋኖ ለመንገር ማሰብ “ ልጅ ለእናቷ ምጥ አስተማረች” እንደማለት መሆኑን አስረግጠን እንናገራለን።

እነ ራስ አዳነ ስዮም ፣ እነ ራስ ውብ ነህ ፣ እነ ራስ አያሌው ብሩ ፣ እነ ደጃች ብሬ ፣ እነ ደጃች ወልደስላሴ እና ወ.ዘ.ተ. ጣሊያንን ያንበረከኩበት የፋኖነትን ትብዕል ተላብሰው ፣ የአንበሳ ገዳይ ጎፈሬያቸውን እጎፍረው እና እንቢ ብለው (ፈንነው) ለድል እንደበቁ ዘንግቶ የወልቃይትን ሕዝብ ከፋኖ ለመነጠል ማሰብ ጣና ያለውን ዓሳ አውጥቶ እንደማምከን ይቆጠራል ፣ ማን ሆነ እና ነው የፋኖው መሰረት እና ፋና ወጊ? አንባቢያን ሆይ።

ስለዚህ ኮለኔል ደመቀ ዘውዱን “ከፋኖ አጋርነት እራሱን አገለለ” ብሎ ማዘላበዱ አንድምታው “የወልቃይት ሕዝብ በአጠቃላይ ከፋኖ እራሱን አገለለ” ለማለት እንደተፈለገ ልንረዳ የግድ የሚለን እና “እኛም አውቀናል ጉድጓድ ምሰናል እና ነቄ ብለናል” ልንላቸው ይገባል።

ይህን ካልን ዘንዳ የአማራ ቀንዲል ፣ የአንድነት ተምሳሌት ፣ ደንበር አስጠባቂ እና እልቆ መሳፍርት የሌለው የባሕል እና  የታሪክ ባለቤት የሆነችው ጎንደር በአጠቃላይ ፣ ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት “ ቡና የለም እንጂ ቡናማ ቢኖር አይ ሃገር አይ ሃገር አይ ሃገር ጎንደር” ተብሎ ቢቀኙላትም ፣ የቅኔው ፍችአዊ ትርጉም ግን በደንብ ሊፈታ ያስፈልጋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከብልጠት ወደ ብልህነት - እውነቱ ደሳልኝ

ጎንደር የብዙ የተፈጥሮ ሃብት ባለቤት ስትሆን በተለይ በወልቃይት ፣ ጠገዴ እና ሰቲት ሁመራ እንደ ጥጥ ፣ ሰሊጥ፣ ሙጫ ፣ እጣን ፣ ቦለቄ ፣ የተፈጥሮ ማዕድናት ወ.ዘ.ተ. በገፍ የሚመረትባት እና ከራስ አልፎ ለመላ ሃገረ ኢትዮጵያ እና ለአማራው ሕዝብ የሚጠቅም ድልብ ምርት አምራች እና የተፈጥሮ ሃብት አፍላቂ ምድር መሆኗ ይታወቃል።

እቺን ወርቃዊት የሆነች ምድር የሚመኟት የውስጥም ሆነ የውጭ ኃይላት የትየለሌ ሰለሆኑ በሰላም ፣ በዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት ማጣቷን ለመግለፅ ( ቡና  የሰላም ፣ የመሰባሰቢያ ፣ የአንድነት ምልክት ፣ ዓለም ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ፉት የሚላት ፍሬ በመሆኗ የስንኙ ውስጠ ወይራ ህሳቤ ግን እነዚህ የሰው ልጅ መሰረታዊ መብቶች በቡና አመላካችነት (Symbolism ) ኪናዊ በሆነ አግባብ አገላለፅ ወልቃይት ፣ ጠገዴ እና ጎንደር የመጣው እና የሄደው ሥርዓተ መንግስት ሁሉ ሰላም የሚነሷት ፣ የጦርነት አውድማ ተጠቂ የሚያደርጓት እና የሴራ ፖለቲካ ትብታብ ተጠቂ መሆኗን ለመግለፅ የተደረደረች ስንኝ መሆኗን ልንረዳ ይገባል።

መላ ጎንደር ለረጅም ዘመናት ስላም እና እረፍት እርቋት ስለሰነባበተች በተለይ ከ1966 ዓመተ ምህረት መባቻ ጀምሮ ከራሷ አልፋ ለአማራው ፣ ለጎንደር እና ለሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጥቀም ተስኗታል ለማለት ታስቦ የተቀኘ እና አሁንም ቢሆን የነዚህ የሰው ልጅ መሰረታዊ መብቶቿን ተነጥቃ በጦርነት አውድማ እየታመሰች እንዳለች ልብ ይሏል።

ስለዚህ ማንኛውም የአማራ አደረጃጀት የወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት እና የራያን ጥያቄ ግንባር ቀደም መፈክሩ ሊያደርገው የሚገባ እና ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት እና ራያ የአማራ ዐፅመ እርስት የመሆናቸውን ጉዳይ አንገት ማተባችን ላይ አስረን መንቀሳቀስ የግድ የሚለን ከመሆኑ ባሻገር ፣ እኛ አማሮች ይህ ጥያቂያችን የማንደራደርበት ቀይ መስመራችን መሆኑን ማስረዳት ያለብን ጊዜ ወቅቱ እና ሰዓቱ እንደትላንት ሁሉ አሁንም መቀጠል  እንዳለበት ለማሳሰብ እንወዳለን።

“ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ጠለምት እና ራያ ብረሳሽ ቀኘ ትርሳኝ”

 

 

9 Comments

  1. ተዘራ ትግሬ ታዲያ ከየት አምጥቶ ነው የኔ ነው የሚለው? አገር ቀምተው መከላከያ የሚጠብቃቸውን አርደው አሁን ደግሞ አይናችን ያየነው ይገባናል ማለት ከየት ያገኙት ነው? ኮለኔሉ ተናገር የተባለው ይሄ ቻች ፒጂ ነው ቻች ቻቲ በሚለው መፈብረኪያ እንዳይሆን። ኮለኔሉ ምን አቅሉን ቢስት ፋኖን በዚህ ልክ ይናገራል ብሎ መጠበቅ ከባድ ነው።

  2. Well, I agree with your passionate or courageous way of expressing your sincere opinion!!!

    But a) your absolute thrust what Demeke Zewudu might or might not different from what he was years ago sounds a bit naive as far as a very difficult if not tragic behavior of human being is concerned.

    b) honestly speaking, I do not and cannot understand why he himself come up and tell the hard truth wether positive or negative ?
    C) You may tell me that because he wanted to ignore all this terrible piece of information and just do what believes he to be done. It goes without saying that this kind of attitude will create much more suspicions and untrustworthiness . So, it is better to be courageous enough to come up and tell about the story and move forward with a real sense of leadership !!!
    d) you may try to tell me that it is a matter of tactic . I do not think so . The issue of all the areas which have been just transferred from Amhara to Tigray is crystal clear and Demeke and his fellowmen and fellow women have paid a lot of price because it was and is quite justifiable in terms of history, legality , morality and so on and so forth. So, why he wanted not to tell the truth instead of saying this or that news is untrue or garbage???
    Yes, unless he comes forward and tells about the news , people will continue believing that the news may be true , and that is not good at all!!!

    • ግለሰቡ ይህን ውስብስብ የሆነውን የአለምን ፖለቲካና የትግሬን ተንኮል ጠንቅቆ ያውቃል ማለት ይቸግራል ትግሬ 250፣000 ጦር በተጠንቀቅ ባቆመበት ሁኔታ ነገ እንደ ቀስት ተወርውረው ነብሱን የሚያድኑትን ፋኖንና የአማራን ህዝብ ያስቀይማል የሚል እምነት የለም። በተጓዳኝ መልኩ ዶር ዳኛቸው አሰፋ ዘወትር አገኘዋለሁ ማለቱንም ማስታወስ ለግንዛቤ ይረዳል። ዶ/ር ዳኛቸው ወደዚያ ሲያቀና አቶ ዳን ኤል ክብረትንና አልፎ አልፎ ዶ/ር ሲስይ መንስቴን ይዞ ሳይሄድ አይቀርም። ይህ የጦር ሰው እነዚህ ሰዎች ከግራና ከቀኝ ከተቀባበሉት አሁን የያዝውን አቋም አይዝም ማለት ግን ይከብዳል።
      ለማንኛውም ጊዜ ይፍታው።ኮለኔል ደመቀ ዛሬ ላለበት ክብርና ዋስትና በሃገርና ከሃገር ውጭ ያለነው የማይናቅ አስተዋጾ ስላደረግን ህዝብ አክብሮ ዝምታውን ቢሰብር መልካም ነው። ይህ የምርጫ ጉዳይ ነው ወይ ብልጽግና ነኝ ወይ ገፈት ቀማሽ፤ጦር የተመዘዘብኝ የመከራ ናዳ የወረደብኝ አማራ ነኝ ብሎ እራስን መመደብ ነው።

  3. አወናባጅ የሃበሻ ፓለቲካ ቆርጦ ሲቀጥልና ሲበጥስ መኖሩ የታወቀ ነው። አሁን ደግሞ ጊዜ የሰጠውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በሬ ወለደ ወሬአቸውን እንደ ድላ ቅብብሎሽ ሩጫ ጨምረው ቀንሰውና አባዝተው ይነዙታል። የፓለቲካ ፕሮፓጋንዳ የጦር ሰበቃው አንድ ገጽታ ነው። እየተዘፈነና ክራር እየተከረከረላቸው ገብተው የተማገድትንና እልፍን ያስጨነቁትን የፓለቲካ ሰይጣኖች ተግባር ከሥሩ በመረዳት ህዝባችን ያገኘውን ሁሉ እንዳለ ባይጋት መልካም ነው። ኮ/ሌ ደመቀ የፈለገውን ሃሳብ ለመናገር መብቱ ነው። እሳቱ የሚሞቀው ለቀረበው ነውና! በየጥሻውና በውጭ ሃገር በየስርቻው ተሸጉጠን በስማ በለው እንዲህና እንዲያ ማለታችን ጠቃሚነት የለውም። ሊሰመርበት የሚገባው አንድ ነገር ብቻ ነው። ለኢትዮጵያ አንድነትና ለህዝቦቿ መብት የሚታገሉ ሁሉ የሚታገዙ እንጂ የሚገፈተሩ አለመሆናቸውን ነው።
    አሁን ከጠ/ሚሩ ጋራ መክሮ መቀሌ የተመለሰው ወያኔ 250 ሺህ ትጥቅ ያልፈታ ሰራዊት አለን ብሉናል። ከአዲስ አበባም መንግስት በቃል አቀባዪ በኩል ወያኔን ወረፍ የሚያረግ ንግግር አሰምቷል። ነገሩ ገና አልጠራለትም። ያው ፓለቲካ ሸርሙጣ አይደል ከሻቢያ ጋር ወያኔ አብሮ ዳግም ወደ ሚኒሊክ ቤ/መንግስት ብቅ ለማለት ይሞክር ይሆናል። ሻቢያና ወያኔ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸውና። በተደጋጋሚ በዚህ ድህረ ገጽና በሌሎችም ልዪ ልዪ መጣጥፎች ላይ ሊመጣ ይለውን ለማመላከት ተሞክሯል። ልብ ያለው ልብ ይበል። ሻቢያ የኢትዮጵያን አንድነትና ብልጽግና በጭራሽ ተመኝቶ አያውቅም። ለምርኮ እጃቸውን ባነሱ የኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ ታንክ የነዳ፤ አፋቸው ውስጥ ያለ የወርቅ ጥርስን ሳይቀር ያወለቀ፤ ያለምንም ውሃና ስንቅ ኢትዮጵያ ሃገራችሁ እዚያ ማዶ ናት በማለት ሰዎችን በረሃ ላይ በትኖ ስንቶች እንዳለቁ ሊረሳ አይገባም። ይህን ክፋት እንዳለ የተጋተው ወያኔ ደግሞ በ 17 ዓመቱ ስመ ትግል ጊዜና በመንግስትነት ዘመኑ የፈጸመው በደል ሰማይ ነክ ነው። ግን ዛሬም አልቆመም። ምክክሩ ከአሜሪካ ጋር ነው። አስር ጊዜ ወደ አዲስ አበባ የሚመላለሱት ማይክ ሃመር መቀሌ ሳይረግጡ አይመለሱም። ገና ብዙ ዝብርቅርቅ ነገር ምድሪቱ ይጠብቃታል። ብልህነት፤ ማስተዋል፤ ከሆድ ያለን ሁሉን አለመናገር ወደፊት ለመራመድ ይበጃል።
    ወያኔ ዳግም ለ4ኛ ጊዜ ወረራ እንደሚፈጽም የታወቀ ነገር ነው። 250 ሺህ ሰራዊት አቅፎ ይዞ የሚቀልበው የመስኖ ሥራ እንዲሰሩለት አይደለም። በዚህም በዚያም መሳሪያዎችን አስገብቷል። እድሜ ለሱዳን እሳትም እየነደደ ቢሆን ያቀብላሉ። አቶ ጌታቸው በመንግስትና በትግራይ አስተዳደር መካከል መተማመን የለም ብሎናል። ያስቃል። ሰው እኮ የሚታመነው ከአለፈው ታሪኩ ተነስቶ የአሁኑ ባህሪው ተገምቶ ነው። በበረሃ የራሳቸውን ጓደኞች በተኙበት ያረድ እብዶች፤ ስንዴን በአሽዋ እየለወጠ እርዳታ ሰጭዎችን ያታለለ የማፍያ ቡድን፤ ራሱ ሹሞ፤ አሰልጥኖ ለዘመናት አብሮ የኖረውን የሰሜን እዝ በተኛበት የመታ ድርጅት አሜኔታ አጣሁ ማለቱ ቧልት ነው። ወያኔ ጊንጥ ነው።
    አሁን አንዴ በድምበር፤ ሌላ ጊዜ ረሃብ ገባ በማለት ራሱንና ሌላውን የሚያሞኘው ወያኔ ለትግራይ ህዝብ መከራ ቀዳሚው ተጠያቂ ነው። አብሮ የኖረን ህዝብ በዘርና በቋንቋ ሰነጣጥቆ አሁን ወገቤን ማለት ለማን ይጠቅማል። እኔ ተብሎ ተብሎ የውሃ ግፊት እንደበዛበት ገድብ የትግራይ ህዝብና ታጣቂ ሃይል ትግሥቱ አልቆ ወያኔዎችን በመቀሌ አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣቸው ይታየኛል። ያኔ የተዘረፈውም፤ የተደበቀው በሃገርና በውጭ ያለው ሃብት ሁሉ ሌላ የሚበላው ይሆናል። ደም አፍሳሾች መጨረሻቸው የከፋ ነውና። ፍትህ የዘገየ ቢመስል የቀረ የሚመስላችሁ ንቁ። የንጉሱን ውድቀት፤ የደርግን መንኮታኮት፤ የወያኔን ተሰባስቦ በመቀሌ መከተም ያመጣው ጊዜ ነው። ጊዜ ሲጨልም ድንገት ነው። ወያኔ ያለ ጦርነት መኖር የማይችል በመሆኑ ከእድሜ ልኩ የሃዳስ ኤርትራ መሪ ጋር በማበር ሌላ እልቂት እንደሚከሰት አመላካች ነገሮች አሉ። የኤርትራ ወታደር የትግራይን መሬት ይዞ ገለ መሌ የሚባለው ሁሉ ሆን ተብሎ ቀደም ብሎ ገዢ መሬቶችን ለመያዝ የተደረገ ዝግጅት ነው። የወልቃይትም ሆነ የሌሎችን ስፍራዎች እድል ፈንታም ከዚህ የውጊያ ቀጠና አያመልጥም። መዘጋጀት ዛሬ ነው። ሴት ወንድ ልጅ ሳይል ነገሮችን ማስተማርና ማሳየት አሁን ነው። የቁርጥ ቀን ከመጣ በህዋላ ስለ ማሪያም ብላችሁ ማሩኝ ቢባል ድርቡሾች ስለሆኑ ማንንም አይሰሙም። ኮ/ሌ ደመቀ ተናገሩት የተባለውንም ከማባዛትና ከማራባት ይልቅ እውነቱን ለይቶ ማወቅ ነው። ወሬው ኮ/ሌ ደመቀን ከፋኖ ጋር ለማጋጨት ሆን ብሎ በሴራ የተነዛ ነው። በቃኝ!

  4. እግዚአብሔር ይባርክህ ። ፀሃፊው ከዚህ በፊት ስለወልቃይት የወደፊት ዕጣ ፈንታ ፣ የብልፅግና መንግስትን ሻጥር እና ሴራ ቁልጭ አድርጎ ፅፏል። አሁን ግን የከተበው በኮለኔል ደመቀ አስታኮ የብልፅግና መንግስት ከትህንግ (ህወሃት) ጋር ተጣምሮ የወልቃይትን እና የአማራን ሕዝብ ለማጋጨት ያደረገውን ሰይጣናዊ አካሄድ ቁልጭ አድርጎ አስረድቶናል። ከዚያ ውጭ “ቡና የለም እንጂ ቡናማ ቢኖር አይ ሃገር አይ ሃገር አይ ሃገርጎንደር’ የሚለውን ስንኝ እንዴት አድርጎ እንዳስረዳ እና እንደተነተነ ገራሚ ነው። ዘፈኑን እዘፍነዋለን እንጂ ትርጉሙ አይገባንም ነበር። ጎንደር ደግሞ ቡና ይበቅላል ነገር ግን ገበሬው በተለያየ ምክንያት በሰፊው አልተሰማራበትም።

  5. በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ወዘተ አካባቢ ችግር የሚፈጥሩት ለትግራይ ህዝብ በማሰብ ሳይሆን ኢትዮጵያን ለማፍረስ ያመቻቸው ዘንድ የአማራውን ህዝብ ለመፍጀት ነው። መተከልን ከጎጃም ቆርሰው የወሰዱት ለዚህ ዓላማ ብቻ ሳይሆን የዐባይን ግድም ጭምር ለመቆጣጠር ነው።
    የአማራ/ጎንደርና ትግራይ ድንበር ተከዜ ወንዝ መሆኑን የማያቅና የማይመሰክር ንጹሕ ዜጋ የለም፣ ከልዑል ራስ መንገሻ ስዩም ጭምር።
    ለትግራይ ወገኖቻችን ቢጨነቁ ኖሮ ለጦርነት፣ ለእልቂት፣ ለድህነትና ለእንግልት ባልዳረጓቸው ነበር።
    የትግራይ ህዝብ ለብዙ ሺ ዓመታት ከአማራ ወገኖቹ ጋር በዘርና በሃይማኖት ተሳስሮና ተረዳድቶ የኖረ ነው።
    አሁንም መፍትሄው ፍቅርና መደጋገፍ እንጂ የርስ በርስ ጦርነት አይደለም።
    በብርቱ ይታሰብበት።
    የጭቁኖች አምላክ አይለየን።

  6. መቸም ሰላሳ ዓመት ሙሉ ህወሃት ወልቃይት ፣ ጠገዴን ፣ ጠለምት እና ራያን ለምን ፈለገ? የሚለውን ጥያቄ እንኳን እኛ ትልልቄቹ በኢትዮጵያውያን እና አማሮች ሆድ የተፀነሰ ህፃን ልጅ ያውቀዋል። አጠር አርጌ ሳስረዳህ ለም መሬት ፍለጋ፣ የመስፋፋት አጀንዳ ፣ ከሱዳን ጋር ድንበር ተጋርቶ ለመንገንጠል ፣ የሱዳንን ድንበር ተጋርቶ አማራውን እና ኢትዮጵያዊያንን ተገዳዳሪ ኃይል ኑሮት ግብፅን ወንድም አድርጎ ለመውጋት ፣ ቢቻል እራሱን አስፋፍቶ የአባይን ግድብ ለመቆጣጠር በስግብግብነት እና በቂመኝነት ሃገረ ትግራይን መስርቶ በሕገ-መንግስት ያሰፈረውን ቃሉን እና ምኞቱን ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን መቸም አይጠፋህ።

    ይህን ለማድረግ ህወሃት በቂ ታሪካዊ ፣ ተጨባጭ እና ሕጋዊ ሰነድ ስለሌለው ከሚቀርበው የአማራ ሕዝብ ጋር አብሮ ከመኖር ይልቅ ” የማያውቁት ሃገር አይናፍቅም” የሚለውን እርግጥ ከኦነግ ጋር መሞዳሞድን ፣ ኮሎኔል ደመቀ ከፋኖ /ከአማራ/ ትግል እራሱን አገለለ እያለ በመዘላበድ አማራን ከወልቃይት እና ራያ ለመነጣጠል ሌላ ጭዋታ ጀምረወል እነ አያልቅባቸው። ኮለኔል ደመቀ መሪ እና የአማራን ትግል አቀጣጣይ ስለሆነ በሕዝብ ጥያቄ ላይ ገብቶ ፋኖ” እንዲህ ነው እንዲያ ነው” ሊል አይችልም ፣ ስራ ላይ ነውና። የውልቃይት እና ራያ ክልል እንሁን ጥያቄ እልተነሳም ፣ አይነሳምም። ሻጥሩ ነገ ወልቃይት እና ራያን ለመሰልቀጥ ሌላ በመርዝ የተለወሰ ሴራ መዶለታቸው ነው። ነግር ግን ወልቃይት እና ራያ የአማራ መሰረቶች በመሆናቸው የታሰበው ሻጥር አይነፋም።

    ዋኘው በስልቱ

  7. .
    መቸም ሰላሳ ዓመት ሙሉ ህወሃት ወልቃይት ፣ ጠገዴን ፣ ጠለምት እና ራያን ለምን ፈለገ? የሚለውን ጥያቄ እንኳን እኛ ትልልቆቹ በኢትዮጵያውያን እና አማሮች ሆድ የተፀነሰ ህፃን ልጅ ያውቀዋል። አጠር አርጌ ሳስረዳህ ለም መሬት ፍለጋ፣ የመስፋፋት አጀንዳ ፣ ከሱዳን ጋር ድንበር ተጋርቶ ለመንገንጠል ፣ የሱዳንን ድንበር ተጋርቶ አማራውን እና ኢትዮጵያዊያንን ተገዳዳሪ ኃይል ኑሮት ግብፅን ወንድም አድርጎ ለመውጋት ፣ ቢቻል እራሱን አስፋፍቶ የአባይን ግድብ ለመቆጣጠር በስግብግብነት እና በቂመኝነት ሃገረ ትግራይን መስርቶ በሕገ-መንግስት ያሰፈረውን ቃሉን እና ምኞቱን ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን መቸም አይጠፋህ። ይህን ለማድረግ ህወሃት በቂ ታሪካዊ ፣ ተጨባጭ እና ሕጋዊ ሰነድ ስለሌለው ከሚቀርበው የአማራ ሕዝብ ጋር አብሮ ከመኖር ይልቅ ” የማያውቁት ሃገር አይናፍቅም” የሚለውን ኪናዊ ስንኝ ወደ ግን አሽቀንጥሮ 900 km ተጉዞ ከኦነግ ጋር መሞዳሞድን ተያዞታል ፣ ከአንድ ሚሊየን ትግራዋይን ኦነግ እንደፈጀበት ዘንግቶ እና ወደ ዳር እድርጎ ሴራ መዶሎቱን ተያይዞታል። አሁን ደግም አዲስ ጭዋታ ኮሎኔል ደመቀ ከፋኖ /ከአማራ/ ትግል እራሱን አገለለ እያለ በመዘላበድ አማራን ከወልቃይት እና ራያ ለመነጣጠል ፣ ለማጋጨት ዝየዳ ዘይደውል ፣ ሌላ ሴራ ጀምረወል እነ አያልቅባቸው። ኮለኔል ደመቀ መሪ እና የአማራን ትግል አቀጣጣይ ስለሆነ በሕዝብ ጥያቄ ላይ ገብቶ ፋኖ” እንዲህ ነው እንዲያ ነው” ሊል አይችልም ፣ ስራ ላይ ነውና። የውልቃይት እና ራያ ክልል እንሁን የሚል ጥያቄ እላነሱም ፣ አይነሳምም። ሻጥሩ ነገ ወልቃይት እና ራያን ለመሰልቀጥ ሌላ በመርዝ የተለወሰ ሴራ መዶለታቸው ነው። ነግር ግን ወልቃይት እና ራያ የአማራ መሰረቶች በመሆናቸው የታሰበው ሻጥር አይነፋም።

    ዋኘው በስልቱ

  8. ዘንድሮም ወሬአችን ሁሉ ስለትግራይ እና ትግራይ ወያኔ ብቻ እንዲሆን ነው ምትፈልጉት ይህማለት ከሃዲን እያሽሞነሞናችሁ እዛ ማዶ እጃችሁን መቀሰር አቁሙ አማራ የራሱን ባንዳዎች አጥሩ ከዛ በክላ ነፃ ትወጣለህ አንድ ታግይ ከከዳ ከዳ ነው ነው የምን ማሽምኢንሞን ነው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share