ዶክተር አክሎግ ቢራራ፣  ያባይ ግድብ ካማራ ሕዝብ ሕልውና ይበልጣልን?

ዶክተር አክሎግ ቢራራ የኢትዮ 360ውን አቶ ሐብታሙ አያሌውን ለመውቀስ ሲል “ያልተገታ ምላስ አማራውን ይጎዳዋል” በሚል ጋጠወጣዊ ርዕስ በከታተበው ጽሑፍ ላይ የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፏል።  መልዕክቱም ያባይ ግድብን በተመለከት ያማራን ሕዝብ እንደ ሕዝብ ለማጥፋት ቆርጦ ከተነሳው ከጭራቅ አሕመድ ጋርም ሆነ ከሌላ ከማናቸውም ቡድን ጋር እወያያለሁ የሚል ነው።  ይባስ ብሎ ደግሞ ዶክተር አክሎግ ቢራራ “አራተኛው የግድብ ሙሌት ስኬታማ እንዲሆን ዐብይ አሕመድ ገንቢ ሚና ተጫውቷል”  በማለት በላዔ አማራውን ጭራቅ አሕመድን ያመሰግነዋል።

ስለዚህም ዶክተር አክሎግ ቢራራን “ያባይ ግድብ ካማራ ሕዝብ ሕልውና ይበልጣልን?” ብሎ መጠየቅ ግድ ነው።  ዶክተር አክሎግ ቢራራ በጽሑፉ የነገረን ደግሞ ያባይ ግድብ ሙሌት ካማራ ሕዝብ ሕልውና እንደሚበልጥበት ነው።  አለያማ ያማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ሙቶ ከተቀበረ በኋላ ዐባይ ተገደበ አልተገደበ ላማራ ሕዝብ ምን ይተክርለታል?

ዶክተር አክሎግ ቢራራ ላማራ ሕዝብ ሕልውና ከፍተኛ ተጋድሎ እያደረገ ያለውን ፋኖውን አቶ ሐብታሙ አያሌውን “አለማወቁን አያውቅም” በማለት ሊያንኳስሰው ሞክሯል።  ስለዚህም አዋቂውን ዶክተር አክሎግ ቢራራን “ያባይ ግድብ የሚገኝበትን ቤንሻንጉል ጉሙዝን ሙሉ በሙሉ ካማራ ሕዝብ ለማፅዳት የጭራቅ አሕመድ ጭራቃዊ መንግስት ጠንክሮ እየሰራና አመርቂ ውጤት እያገኘበት እንደሆነ ሽመልስ አብዲሳ በግልፅ መናገሩን አታውቅምን?” ብሎ መጠየቅ የግድ ነው።

ዶክተር አክሎግ ቢራራ “አለማወቅን ማወቅ ራሱ እውቀት ነው” የሚባለውን ሶቅራጥስ ከኑብያውያን የሰረቀውን ብሂል የፈረንጅ ብሎ ጠቅሷል።  ይህን ሲጠቅስ ግን “ሌባ ጣትህን ወደሌላው ስትቀስር፣ ዐራቱ ጣቶችህ ወደራስህ ይቀሰራሉ” የሚለውን ተመሳሳይ ብሂል የዘነጋው ወይም የማያውቀው ይስመስልበታል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አዲስ ጉዳይ መጽሔት፡ ማኅበራዊ ሚዲያ ፕሬሱን እየተካ ይሆን?

ዶክተር አክሎግ ቢራራ “ለ50 ዓምታት ለኢትዮጵያ ተሟሙቻለሁ” በማለት ራሱን በራሱ ከፍ እያደረገ፣ በወያኔ መንግሥት ከፍተኛ በደል የደረሰበትን፣ ባሁኑ የሞት ሽረት ወቅት ላማራ ሕዝብ ሕልውና በከፍተኛ ደረጃ እየተሟሟተ ያለውን ፋኖውን አቶ ሐብታሙ አያሌውን “የቀደመውን የህውሃት ሴራውን ስኬታማ ለማድረግ” በማለት በወያኔ ተላላኪነት ሊፈርጀው ሞክሯል።  ይህ ፍረጃ የሚጠቅመው ደግሞ ጀግናው ሐብታሙ አያሌው በፅኑ እየታገላቸው ያለውን፣ ያማራ ሕዝብ የሕልውና ጠላቶች የሆኑትን ወያኔና ኦነግን እንደሆነ ለዶክተር አክሎግ መንገር አያስፈልግም።

ስለዚህም ዋናው ጥያቄ ዶክተር አክሎግ ቢራራ ለምን ተተቸሁ በሚል ሰበብ ለጀግናው ለሐብታሙ አያሌው ያለ ስሙ ስም መስጠት ለምን አስፈለገው የሚለው ነው፣ በተለይም ደግሞ ላማራ ሕዝብ ወሳኝ በሆነው ባሁኑ የሞት ሽረት ወቅት

ያልተገራ ምላስ የሚያስብለው ዶክተር አክሎግ ቢራራ አቶ ሐብታሙ አያሌውን በወያኔነት ለመፈረጅ መሞከሩ እንጅ፣ አቶ ሐብታሙ አያሌው ከጭራቅ አሕመድ ጋር መዋጋት እንጅ መወያየት አያስፈልግም በማለት ዶክተር አክሎግን መተቸቱ አይደለም።  ያማራን ሕዝብ የሕልውና ትግል እጅጉን የሚጎዳው እንደ ሐብታሙ ያሉትን ያማራ ሕዝብ ጀግኖች ስም ለማጥፋት መሞከር እንጅ፣ እነ ዶክተር አክሎግ ቢራራን መተቸት አይደለም።  ዶክተር አክሎግ ቢራራ ግን “አትንኩኝ የሹም ዶሮ ነኝ” እያለን ነው።  የየትኛው ሹም?

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 

 

6 Comments

  1. ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ተደናብረዋል፡፡ እኔ መቸም እያወቁ የአባይ ግድብ ከአማራ ህዝብ ይበልጣል የሚሉ አይመስለኝም፡፡ ያችን ቀን አቶ “”ዋቄ ፈታ”” ተጠናውቷቸው የነበረ ይመስለኛል፡፡ በይፋ ይቅርታ ቢጠይቁ ይሻላል፡፡ በነገራችን ላይ እኔ “”ዋቄ ፈታ”” ስል አካባቢየን ዘወር ዘወር ብዬ አይቼ ነው፡፡
    ስለትንታጉ ሀብታሙ አያሌው እንኳን እርሳቸው ትክክለኛው ባለ ድግሪ አጨናባሪው ባለድግሪ አቶ አብይ አህመድም ራሱ ሲያስባንነው የሚያድርበት መጋኛው ሆኖበታል፡፡ ለዕኛ ለሚሊዮኖች አገር ወዳዶች ኢትዮጵያዊያን ደግሞ ሀብትሽ ቆራጡ ልጃችን ስለሆነ ዶር አክሎግ “”አፉ”” ይበሉ!!!

  2. መስፍንም ሆንክ ዶር አክሎግ ላማራው ምን ያህል እንደደከማችሁ እናውቃለን ፕሮፌሰር መስፍን ረጋ ባለ ሁኔታ ኑገሩ የሚለዝብበትን እንጅ ተደርበህ ሽብልቅ ባትከት መልካም ነበር በውነቱ ዶር አክሎግን ያለ ስማቸው ስም መስጠት ዩአማራውን ትግል ከመሰንጠቅ አልፎ ምሁራንም ተደባለቀው አስተዋጽዋቸውን እንዳያበረክቱ ስለሚያደርግ ጥንቃቄ መልካም ይመስለኛል። ጽሁፋቸውንም ከአውድ አውጥቶ የራስን ትርጉም ሰጥቶ ሌላውን መቀጥቀጥ ምን ይሉታል? ገና ብዙ መጓዝ ይጠይቃል አላለቀም አትዘናጉ። ከትግሬም ተማሩ ዶር አክሎግ ስፍር ቁጥር የሌለው ጠላት ተጋሩና ቄሮ ስላላቸው መመከቱ ቢቀር ባንደረብባቸው መልካም ነው ካጠፋን ይቅርታ።

  3. Well, if our intellectuals like including Dr Aklog are not well determined to sincerely regret for their terrible failure of dancing a very dirty tail waging dance with a very good puppets of the criminal political system , let them go ahead and face not only the degrading their own intellect and intellectual personalities but also self/ dehumanization !!!
    Yes, any ordinary person with his or her right mind can understand the very clear and bitter political situation in our country let alone people such as Dr Aklog who claim themselves senior intellectuals .
    Let’s call a spade a spade if we are really in need of a real sense of freedom and justice for all citizens , not the other way round !!!

  4. ይህ ሰውዬ ከስድብ እና ስም ከማጥፋት ውጭ ቁም ነገር ያለው
    ፅሁፍ ፅፎ አይቸ አላውቅም እባክህ ተረጋጋ ::

  5. ዶ/ር አክሎግ የተናገሩት ከሀብታሙ አልፎ ትግሉን የሚጉዳ ባይሆንም በዚህ ወቅት ከሳቸው የሚጠበቅ አይደለም። ሆኖም እርሳቸው አሁንም በመንግስት መሪዎች አሰራር ተስፋ ያልቆረጡ መሆኑን እና በኢትዮዽያ ላይ የተጋረጠውን አደጋ በመዘንገት እና ኢጎቸውን መግታት ተስኗቸው ስለሆነ እንለፋቸው፥ ሀብታሙም ብትሆን ከዋናው ኢላማህ ውጭ እነከሌ የፋኖን ትግል መሪ መን አሉ ፥ የፋኖ ወኪል ነን ብለው መጡ እስከሸሁን የት ነበሩ እያልክ ግዜ አታባክን። ወደዚህ ጉዳይ የሚመራህ በየቀኑ ያለበቂ አዲስ ጠቃሚ መተጃ አየር ላይ መውጣት ስለሆነ ይኸን ነጥብ ብትይዘው። ግለሰብ ላይ አታተኩር።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share