ከአመድ አፋሽ ወደ ደም አፍሳሽ

በኢትዮጵያ  የፖለቲካ  ንቅናቄ እና የለዉጥ ፍላጎት እና ጥያቄ ከጥንት አስካሁን የዓማራ ህዝብ ድርሻ ቀላል አለመሆኑን የታሪክ ድርሳናት እና ትዉልድ የሚዘክሩት ከመሆን በላይ ያላፉት ዘመናት በኢትዮጵያ የተስተዋሉት የፖለቲካ እና ስርዓት ለዉጦች ዓይነተኛ ማሳያወች ናቸዉ ፡፡

ከንጉሰ መገስቱ የዘዉድ ስርዓት ወደ አብዮት ለዉጥ እንቅስቃሴ ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ጋር በመሆን የግንባር ቀደም ተሳትፎ መኖሩን ዓለም የሚያዉቀዉ ፀሀይ የሞቀዉ ገሀድ ነዉ ፡፡

በግል እንኳን መጥቀስ ቢቻል ብዙዎች የዘዉድ ስርዓቱን እንደ ጣኦት በመያመልኩበት እና በሚፈሩበት ጊዜ የትግሉን ችቦ ያቀጣጠሉት እና የመሩት እነ ኮሎኔል አጥናፉ አባተ እና ጥግል ጓዶች ያለፈ ሥርዓት ናፋቂ ሳይሆኑ የህዝብን ፋላጎት እና የአገርን አንድነት መሰረት ያደረገ ብሄራዊ ለዉጥ እና ዕድገት ለማምጣት ነበር ፤ ነዉ ፡፡

ይሁን ዛሬም ላይ ላለፉት ሶስት አሰርተ ዓመታት በኢትዮጵያዊነት ላይ የሚደረገዉ የጥላቻ እና ዛቻ ቅስቀሳ ያለፈ ስርዓት ናፋቂ እና አድናቂ፣ አሀዳዊ፣ ብሄራዊ ፣ ኢትዮጵያዊነት….ሲባል ምን ያህል ከታሪክ እና ዕዉነት መራቃችንን የሚያሳይ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ፡፡

አዚህ ጋ ሳይጠቀስ የማይታለፈዉ የዓማራ ህዝብ ኢትዮጵያዊነት እና ብሄራዊነት ብዙዉን እና የረጂም ዘመናት የአገር ባለዉለታነት ትተን በ1966 ፣ በ1983፣ 2008   እና መጋቤት 2010 ዓ.ም. ብልጭ ብለዉ ድርግም ያሉት የለዉጥ ምልክት ፋና ወጊነት የዓማራ ህዝብ የጎላ ድርሻ ምስክር የሚያስፈልገዉ አይደለም ፡፡

ሳይጠቀስ የማያልፈዉ በአገሪቷ ለዓመታት ሲከናወን ከነበረዉ የህዝብ ጥያቄ እና የአግሪቷን የለዉጥ ፋላጎት ከኋላ ተነስተዉ ከፊቴ በመደንቀር የየጊዜዉን የታግድሎ ዋጋ የሚያሳንሱ አስመሳዮች እና አድር ባዮች በተለያየ ጊዜ ተከስተዋል ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከልማት መጋረጃው በስተጀርባ

ይህም ከረጂም ጊዜ አሁን አስከምንገኝበት ጊዜ እና ሁኔታ ሲቀጥል በዜጎች የህይወት እና የአካል ዋጋ በማሳጣት ለግል እና ቡድን ጥቅም መረማመጃ ማድረግ የማይረካዉ ብአዴን ዛሬም በለመደዉ መንገድ መጓዝ ቀጥሏል፡፡

ይህም በአምስት ምዕራፍ ሲታይ ፡-

  • የዓማራ ህዝብ የቀድሞዉን መንግስት ስርዓት ለማስወገድ ከፍተኛዉን ድርሻ የተወጣዉ እና ለኢህአዴግ መፈጠርም ሆነ መኖር መሰረት የሆነ ህዝብ ከኢህዴግ መስረታ(1982 ዓ.ም) ማግስት ክህደት እንዲፈፀም ብአዴን የኢህአዴግ ባለዉለታ ለኢትዮጵያ እና ዓማራ ህዝብ ጠላትነቱን አሳይቷል፣
  • ኢህአዴግን ዕጁን ይዞ ለስልጣን ያስገበዉን የዓማራ ህዝብ እና ምርጥ ልጆች በመካድ ማሳደድ ሲጀመር ብአዴን ለዚህ ተባባሪ መሆን፣
  • በኢትዮ -ኤርትራ ጦርነት አገርም ፤ህዝብም እና አህአዴግም በዓማራ ህዝብ ሲሆን ከጦርነት በኋላ የተካደ እና የተሳደደ ህዝብ ፣
  • በምርጫ የተካደ ፣
  • በትህነግ ወረራ እና ምዝበራ የተነሳዉ ጦርነት ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ፤ የዓማራን ህዝብ ከምደርረ ገፅ ለመደምሰስ  ጦርነት ሲታወጂበት በጦርነት የጠዋደቀዉም ሆነ የተወረረዉ ህዝብ ዓማራ ሆኖ ዓማራ ሲከሰስ ብአዴን ከሳሽ ኆኗል ፣
  • የዓማራ ህዝብ በላቡ እና በደሙ የያዘዉን መሳሪያ ለሁለተኛ ጊዜ እንዲፈታ (1ኛዉ ፡ ኢህአዴግ ሲገባ ትጥቅ አይደለም ዜግነቱን እንዲያጣ ሆኗል) በዚህ በምንገኝበት ዘመን ተገዷል ፤
  • በቀለላል እና በጥበብ ሊታረቅ  የሚችልን ቅራኔ እና የህዝብ ታሪካዊ እና ወቅታዊ የማንነት እና የህለዉና ስጋት ” በጥቁር ጠበንጃ ” ሰበብ “ጥቁር የጥላቻ ታሪክ ሙጃ ” ተዘርቶ አንዲስፋፋ የመሀል ተመልካች ሆኗል ፣

ከዚህም በላይ ሰሞኑን አንድ አገር ፣ አንድ ህዝብ  እና የጋራ ማንነት የሉዓላዊት አገር መገለጫ እንደመሆኑ መጠን ይህ ለዘመናት አስካሁን እንደ ጥፋት እየተቆጠረ ተወቃሽ  ወቃሽ ሲሆን የብአዴን አድር ባይነት እና አይቶ ማለፍ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የዓማራ ህዝብ እና የኢትዮጵያ የግዛት አንድነት መደፈር እና መወነካከር ለሆነዉ ተደጋጋሚ  ክህደት እና ለሚደርሰዉ ጥፋት ኃላፊነት ያለበት በስሙ ለሚገለገልበት የዓማራ ህዝብ ለደረሰበት መጠነ ሰፊ ግፍ እና በደል ተጠያቂ ያደርገዋል ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  አብይ አህመድ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኛ ወይንስ የኦነግ ምርኮኛ? ......ከጥሩነህ

በአዴን ለእናት ፣ አዉራ ወይም እህት ድርጂቱ ባለዉለታነቱ ከላይ በተጠቀሱት እና በሌሎች ባልተጠቀሱት  ሁነቶች  ከፍ ያለ ሲሆን በተቀራኒዉ ለህዝብ ባላናጣነቱ በዚኅ ልክ መደጋገሙ  ደረጃዉን ከአመድ አፋሽነት ደም አፋሳሽነት ማሳደጉ ባለፉት ጥቂት ዓመታት አረጋግጧል፡፡

የብአዴን በድንነት በታረክም በትዉልድም በይቅርታ እና ህዝብን በማገልገል ሳይታደስ በዚህ ደረጃ መድረስ በዕዉነት ለአገር እና ለህዝብ ከማገልገል ይልቅ ለአላፊ እና ጠፊ ነገር ክፉ ስም ይዞ ማለፍ ምን እንደሚያስደስት ራሱ ዕመረዋለሁ ከሚለዉ ህዝብ አልፎ ዲያብሎስን ያስናቀ ክፋቱ እና  ጥፋቱ ዓለምን ግራ አጋብቷል ፡፡

በቃ…….ዉርደት ፤

በቃ …ስደት፣

አይበቃም ወይ  …እየሞቱ መሞት ፡፡

 

አንድነት ኃይል ነዉ !

 

Allen!

 

1 Comment

  1. እኛ ስለ ብአዴንና ብርሀኑ ነጋ ተሸማቅቀን አለቅን እነሱ ደግሞ ውርደትን ተለማመዱት

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share