August 26, 2023
8 mins read

 ከአመድ አፋሽ ወደ ደም አፍሳሽ

Abiy apointed Amhara pesident 1 1

በኢትዮጵያ  የፖለቲካ  ንቅናቄ እና የለዉጥ ፍላጎት እና ጥያቄ ከጥንት አስካሁን የዓማራ ህዝብ ድርሻ ቀላል አለመሆኑን የታሪክ ድርሳናት እና ትዉልድ የሚዘክሩት ከመሆን በላይ ያላፉት ዘመናት በኢትዮጵያ የተስተዋሉት የፖለቲካ እና ስርዓት ለዉጦች ዓይነተኛ ማሳያወች ናቸዉ ፡፡

ከንጉሰ መገስቱ የዘዉድ ስርዓት ወደ አብዮት ለዉጥ እንቅስቃሴ ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ጋር በመሆን የግንባር ቀደም ተሳትፎ መኖሩን ዓለም የሚያዉቀዉ ፀሀይ የሞቀዉ ገሀድ ነዉ ፡፡

Abiy Ahmed warበግል እንኳን መጥቀስ ቢቻል ብዙዎች የዘዉድ ስርዓቱን እንደ ጣኦት በመያመልኩበት እና በሚፈሩበት ጊዜ የትግሉን ችቦ ያቀጣጠሉት እና የመሩት እነ ኮሎኔል አጥናፉ አባተ እና ጥግል ጓዶች ያለፈ ሥርዓት ናፋቂ ሳይሆኑ የህዝብን ፋላጎት እና የአገርን አንድነት መሰረት ያደረገ ብሄራዊ ለዉጥ እና ዕድገት ለማምጣት ነበር ፤ ነዉ ፡፡

ይሁን ዛሬም ላይ ላለፉት ሶስት አሰርተ ዓመታት በኢትዮጵያዊነት ላይ የሚደረገዉ የጥላቻ እና ዛቻ ቅስቀሳ ያለፈ ስርዓት ናፋቂ እና አድናቂ፣ አሀዳዊ፣ ብሄራዊ ፣ ኢትዮጵያዊነት….ሲባል ምን ያህል ከታሪክ እና ዕዉነት መራቃችንን የሚያሳይ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ፡፡

አዚህ ጋ ሳይጠቀስ የማይታለፈዉ የዓማራ ህዝብ ኢትዮጵያዊነት እና ብሄራዊነት ብዙዉን እና የረጂም ዘመናት የአገር ባለዉለታነት ትተን በ1966 ፣ በ1983፣ 2008   እና መጋቤት 2010 ዓ.ም. ብልጭ ብለዉ ድርግም ያሉት የለዉጥ ምልክት ፋና ወጊነት የዓማራ ህዝብ የጎላ ድርሻ ምስክር የሚያስፈልገዉ አይደለም ፡፡

ሳይጠቀስ የማያልፈዉ በአገሪቷ ለዓመታት ሲከናወን ከነበረዉ የህዝብ ጥያቄ እና የአግሪቷን የለዉጥ ፋላጎት ከኋላ ተነስተዉ ከፊቴ በመደንቀር የየጊዜዉን የታግድሎ ዋጋ የሚያሳንሱ አስመሳዮች እና አድር ባዮች በተለያየ ጊዜ ተከስተዋል ፡፡

ይህም ከረጂም ጊዜ አሁን አስከምንገኝበት ጊዜ እና ሁኔታ ሲቀጥል በዜጎች የህይወት እና የአካል ዋጋ በማሳጣት ለግል እና ቡድን ጥቅም መረማመጃ ማድረግ የማይረካዉ ብአዴን ዛሬም በለመደዉ መንገድ መጓዝ ቀጥሏል፡፡

ይህም በአምስት ምዕራፍ ሲታይ ፡-

  • የዓማራ ህዝብ የቀድሞዉን መንግስት ስርዓት ለማስወገድ ከፍተኛዉን ድርሻ የተወጣዉ እና ለኢህአዴግ መፈጠርም ሆነ መኖር መሰረት የሆነ ህዝብ ከኢህዴግ መስረታ(1982 ዓ.ም) ማግስት ክህደት እንዲፈፀም ብአዴን የኢህአዴግ ባለዉለታ ለኢትዮጵያ እና ዓማራ ህዝብ ጠላትነቱን አሳይቷል፣
  • ኢህአዴግን ዕጁን ይዞ ለስልጣን ያስገበዉን የዓማራ ህዝብ እና ምርጥ ልጆች በመካድ ማሳደድ ሲጀመር ብአዴን ለዚህ ተባባሪ መሆን፣
  • በኢትዮ -ኤርትራ ጦርነት አገርም ፤ህዝብም እና አህአዴግም በዓማራ ህዝብ ሲሆን ከጦርነት በኋላ የተካደ እና የተሳደደ ህዝብ ፣
  • በምርጫ የተካደ ፣
  • በትህነግ ወረራ እና ምዝበራ የተነሳዉ ጦርነት ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ፤ የዓማራን ህዝብ ከምደርረ ገፅ ለመደምሰስ  ጦርነት ሲታወጂበት በጦርነት የጠዋደቀዉም ሆነ የተወረረዉ ህዝብ ዓማራ ሆኖ ዓማራ ሲከሰስ ብአዴን ከሳሽ ኆኗል ፣
  • የዓማራ ህዝብ በላቡ እና በደሙ የያዘዉን መሳሪያ ለሁለተኛ ጊዜ እንዲፈታ (1ኛዉ ፡ ኢህአዴግ ሲገባ ትጥቅ አይደለም ዜግነቱን እንዲያጣ ሆኗል) በዚህ በምንገኝበት ዘመን ተገዷል ፤
  • በቀለላል እና በጥበብ ሊታረቅ  የሚችልን ቅራኔ እና የህዝብ ታሪካዊ እና ወቅታዊ የማንነት እና የህለዉና ስጋት ” በጥቁር ጠበንጃ ” ሰበብ “ጥቁር የጥላቻ ታሪክ ሙጃ ” ተዘርቶ አንዲስፋፋ የመሀል ተመልካች ሆኗል ፣

ከዚህም በላይ ሰሞኑን አንድ አገር ፣ አንድ ህዝብ  እና የጋራ ማንነት የሉዓላዊት አገር መገለጫ እንደመሆኑ መጠን ይህ ለዘመናት አስካሁን እንደ ጥፋት እየተቆጠረ ተወቃሽ  ወቃሽ ሲሆን የብአዴን አድር ባይነት እና አይቶ ማለፍ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የዓማራ ህዝብ እና የኢትዮጵያ የግዛት አንድነት መደፈር እና መወነካከር ለሆነዉ ተደጋጋሚ  ክህደት እና ለሚደርሰዉ ጥፋት ኃላፊነት ያለበት በስሙ ለሚገለገልበት የዓማራ ህዝብ ለደረሰበት መጠነ ሰፊ ግፍ እና በደል ተጠያቂ ያደርገዋል ፡፡

በአዴን ለእናት ፣ አዉራ ወይም እህት ድርጂቱ ባለዉለታነቱ ከላይ በተጠቀሱት እና በሌሎች ባልተጠቀሱት  ሁነቶች  ከፍ ያለ ሲሆን በተቀራኒዉ ለህዝብ ባላናጣነቱ በዚኅ ልክ መደጋገሙ  ደረጃዉን ከአመድ አፋሽነት ደም አፋሳሽነት ማሳደጉ ባለፉት ጥቂት ዓመታት አረጋግጧል፡፡

የብአዴን በድንነት በታረክም በትዉልድም በይቅርታ እና ህዝብን በማገልገል ሳይታደስ በዚህ ደረጃ መድረስ በዕዉነት ለአገር እና ለህዝብ ከማገልገል ይልቅ ለአላፊ እና ጠፊ ነገር ክፉ ስም ይዞ ማለፍ ምን እንደሚያስደስት ራሱ ዕመረዋለሁ ከሚለዉ ህዝብ አልፎ ዲያብሎስን ያስናቀ ክፋቱ እና  ጥፋቱ ዓለምን ግራ አጋብቷል ፡፡

በቃ…….ዉርደት ፤

በቃ …ስደት፣

አይበቃም ወይ  …እየሞቱ መሞት ፡፡

 

አንድነት ኃይል ነዉ !

 

Allen!

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop