June 3, 2023
4 mins read

ሕዝብ ሆይ! – በላይነህ አባተ

Abiy Ahme Killer 1 1
#image_title

ሕዝብ ሆይ!

ጅቡ ሲመጣ አፍጦ በአውሬ ባህሪው ሊገምጥህ፣
እንደ አምናው ተዛሬ ነገ ሰውን ይሆናል ብለህ ተጠበክ፣
እንደ ታች አምናው ዘንድሮም ዳግም ቂል ተሆንክ፣
የራስህ አጥፊው ጅብ ሳይሆን አንተው ራስህ ሕዝብ ነህ!

ሕዝብ ሆይ!

ከተቀደሰው ቤተክርስትያን ከምትሰግድበት መስጊድህ፣
እርኩስ ጅብ ገብቶ እየጎመደ ሲበላህ ሲያረክስህ፣
ያላዬ መስለህ ተተኛህ እጅህን አጣጥፈህ ቁጭ ታልክ፣
እንኳንስ ይህ ከንቱ ምድር እግዜር ያለበት ሰማይም አይረዳህ፡፡

ሕዝብ ሆይ!

እርዳኝ እረድሃለሁ ያለውን ትእዛዙን ሕጎቹን ቦጫጭቀህ፣
ጅብ ተቤተ መቅደስ ደም ሲያፈስና ሲጠጣ ዝም ታልክ፣
በአምሳሌ ሰርቸዋለሁ ያለውን ፍጥረቱን መቼ ሆንክ?

ሕዝብ ሆይ!

አሞት አልቦ ጅብ ግራ እግር ጎርሶ ሲውጥህ እያየህ፣
“ቀኜን እንዳይደግም ዝም በል” የሚል ጡርቂ አመል ታሳየህ፣
ልብ አድርግ ለቀብር የሚሆን እራፊ ገላም አይተርፍህ፡፡

ሕዝብ ሆይ!

ጅብና ውሻ ፈሪ እንደማይለቅ እያወክ፣
ወግድ ክላልኝ የሚልን እንደማይነካ ዘንግተህ፣
ፊትለፊት እንደመጋጠም ለመሸሽ ከተፈተለክ፣
እንኳንስ የአንተ የልጅ ልጅህም ታፋው አይተርፍህ፡፡

ሕዝብ ሆይ!

ጅብ ተጠራርቶ ሊጎርስህ በሁሉ አቅጣጫ ሲከብህ፣
አካሎችህን አንድ አርገህ በጥኑ ወኔ መፋለም ሲገባህ፣
የግራ የቀኝ እጅህን አጋጭተህ ክንድ ማስለሉን ተቀጠልክ፣
እንኳን ቀን የሰጠው ጅብ ጆፌ አሞራውም አይምርህ፡፡

ሕዝብ ሆይ!

እንደ ቅደም አያቶችህ አንድ ላይ ሆነህ መፋለም ሲገባህ፣
በጎጥ በመንደር እየጮህክ እርስ በራስህ መናከስ ተጀመርክ፣
ማለቅህን እወቅ በጅቦች የከረፋ አፍ ተራ በተራ ተውጠህ፡፡

ሕዝብ ሆይ!

የቀን ጅብ ተዱሩ ወጥቶ ሊውጥህ አምቧትሮ ሳለ፣
ቀኝ እግርህ ግራውን በተንኮል ጠልፎ ተጣለ፣
ለራስህ የከፋ ጠላት ያለ አንተው ሌላ ማን አለ?

ሕዝብ ሆይ!

ቀኑ የጅቦች መሆኑን በእዝነ ልቡናህ አጥንተህ፣
ቀኝ ክንድን በጡንቻህ ተግራው ጋራ አጣምረህ፣
ግራ እግርን ተቀኙ እንደ ብረት ከንች አምቧትረህ፣
ህልውናህን አረጋግጥ እንደ ታሪክህ በትግልህ፡፡

ሕዝብ ሆይ!

ዘመኑ የጅቦች መሆኑን በአይምሮ ልብህ አጢነህ፣
የአያትን ክብሮች አስጠብቅ ክንድ መንፈስክን አንድ አርገህ፡፡

በላይነህ አባተ ([email protected])
ግንቦት ሁለት ሺ አስራ አራት ዓ.ም.

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

Go toTop