May 31, 2023
4 mins read

በሐዋሳ ተፈፅሟል ስለተባለው ዘመናዊዉ የጠለፋ ድርጊት መረጃ

347236771 5943482499112068 5537150762318974338 n 1 1

ጉዳዩ በሐዋሳ ከተማ ከተከሰተ ሳምንት ያስቆጠረው የአንድ እንስት በከተማዋ ከንቲባ ጠባቂ ( ጋርድ) መጠለፏን እና በዚህም ቤተሰቦች ከፍተኛ ጨንቀት ዉስጥ መግባታቸውን ሰምቻለሁ።

የቅርብ ሰዎች

ድርጊቱን ፈፅሟል የተባለው ግለሰብ በሁለት በመንግሥት ተሽከርካሪ መኪና ከስራ ገበታዋ ስትወጣ ጠልፈዋት ይዘዋት ከአከባቢው ተሰዉረዋል ፤ በምስዕሉ ላይ የተምትመለከቱት የባለስልጣኑ ጠባቂ ወደ ትዉልድ ቀዬው ሲያቀና “የጀግና አቀባበል ተደርጎለታል”!

ዛሬ ነገ ድምጿን እንሰማለን በሚል በተሰፋ ሲጠባበቁ የነበሩት ቤተሰብ ከአጋች አንድ የስልክ ጥሪ ይደርሳቸዋል ” ልጃችሁ እኔዉ ጋር ነች በቅርቡ ሽማግሌ እልካለሁ በግዴታ ትቀበላላችሁ ” የሚል እንደነበር በግሌ ባደረጉት ማጣራት ለማወቅ ችያለሁ ።

ጉዳዩ በዚህ አያበቃም ፖሊስም ምላሽ ሰጥቷል።

እንደ ፖሊስ መረጃ ከሆነ ድርጊቱን የፈፀመውን ግለሰብ በማፈላለግ ላይ እንደሚገኙ እንዲሁም ከሐዋሳ አቅራቢያ ወደ ምትገኘዉ ሐገረ ሰላም ማቅናቱን አረጋግጠዋል ። ነገር ግን ከዉስጥ ለባለስልጣኑ ጠባቂ መረጃ ቀድሞ እየደረሰዉ በመሆኑ ፖሊስ ይገኝበታል ብሎ ያሰበበት ስፍራ ቢሰማራም ቦታ መቀየሩን ተናግሯል ። ይህም ስራዉን አክብዶብኛል ብሏል።

እንዲህ አይነት ድርጊት እንዴት ሊፈፀም ቻለ?

የልጅቱ መጥፋት ተደማምሮ በርካታ የሚዲያ ሽፋን በማግኘቱ ትኩረት ተደርጎበታል ነገር ግን ከየገጠር ወረዳዎች ይህ ነገር አሁንም ድረስ መኖሩ ለስራ አጋጣሚ ወደ ክልሉ ፖሊስ የሴቶችና ህፃናት ክፍል ባመራሁበት ወቅት አረጋግጫለሁ ።

የግል ጠባቂው ከዚህ ቀደም በልጅቷ ላይ የተለያዩ ማስፈራሪያ ዛቻዎችን የሚፈፅም ቢሆኑም እንዲህ ያደርጋል ብሎ የጠበቀ ማንም አልነበረም ይልቁኑ በቅርብ ልትሞሸር ሽር ጉድ እያለች ትገኝ ነበር።

ከመሬት ተሰነስቶ ሊያዉም በከተማው ፈፅሞ ሊደርግ የማይችል ድርጊት ሊፈፀም የቻለዉ እና በግልፅ ማንም ሲናገር ያልሰማሁት መረጃ ላካፍላችሁ ይህንንም ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈቀደ ግለሰብ ነዉ ቃል በቃል እንዲህ ብሎኛል …”ሁለቱም ትዉዉቅ አላቸዉ በግልፅ እንዲህ ነዉ የምለዉ ነገር ባይኖረኝም ከስራዋ ጋር የተያያዘ ነዉ፤ እሱ እንደሚወዳት በተደጋጋሚ ነግሯታል በስልክም ያወሩ ነበር ” ሲል ለጉዳዩ ቅርበት ያለዉ ሰዉ መረጃዉን አድርሶኛል።

አሁን ግን ቤተሰቦቿ በእጅጉ ተጨንቀዋል ይህ የከተማዋን ገፅታ ማበላሸት ነዉ የሚባለዉ ትርክት አይገባኝም ይሄ የሰዉነት ጉዳይ ነዉ.. ዛሬ በዚህች ልጅ የተፈጠረው ነገ በእኔ እህት እንደማየሰከሰት ማረጋገጫ የለኝም።

እንደሚሰማዉ ፖሊስ ከአቅሙ በላይ ሆኖበታል … ቀድሞ መረጃ እየደረሰዉ በመሆኑ ጠባቂዉን ለማግኘት አዳጋች አድርጎታል … ይሄ ፊልም የመሰለው ድርጊት ዝምታ ተመርጦ እስካሁን ምላሽ አለመሰጠቱ እርስበርሳቸው መፈራራት እንዳለባቸው ያሳብባል።

Eyasu Zekarias ከስፍራው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop