May 31, 2023
2 mins read

ተዋናይት ሜላት ዳዊት ከእስር እንድትፍታ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ቢሰጥም ፖሊስ ይግባኝ ጠየቀ ! ( ይድነቃቸው ከበደ )

347419155 647743003457819 8163470114537388733 n 1 2

የፊልም ዳይሬክተር እና ተዋናይት ሜላት ዳዊት ፤ በዛሬው ዕለት ግንቦት 22 ቀን 2015 ዓ.ም. አስሯት የሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ፣ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት እንድትቀርብ አድርጓል ።

ፖሊስ ለባለፉት 7 ቀናት ፍርድ ቤት በሰጠው የምርመራ ቀናት ፣ ከዚህ ቀደም ይቀሩኛል የሚለውን የምርመራ ሂደት አጠናቆ እንዲቀርብ ጊዜ የተሰጠው ቢሆንም ፣ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ 14 የምርምር ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል ።

melat 1 Copy 1

ሆኖም ግን ፤ ፍርድ ቤቱ ከዚህ ቀደም ለፖሊስ የተሰጠው የምርመራ ቀናት በቂ በመሆኑ ፣ እንዲሁም ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው ጊዜ የተለየ የምርመራ ሥራ አልተሰራም በማለት ፤ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ፣የፊልም ዳይሬክተር እና ተዋናይት ሜላት ዳዊት በ5 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና ጉዳዩን ከእስር ተፈታ እንድትከታተል ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል ።
ጠዋት በዋለው ችሎት ፤ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፤ ተዋናይት ሜላት ዳዊት በ5 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንድትለቀቅ የሰጠውን ትዕዛዝ በመቃወም ፤ ፖሊስ ለከፍተኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሰዓት በዋለው ችሎት ይግባኝ ጠይቋል ።

Melat

ይግባኙን የተመለከው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ፤ በታችኛው ፍ/ቤት የተሰጠውን ትዕዛዝ መርምሬ ” ውሳኔ የምሰጠው ፤ ነገ ግንቦት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ 8 ፡00 ሰዓት ነው ” ብሏል ።

All reactions:

259

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop