May 31, 2023
3 mins read

በሥላሴ አንድነት ገዳም ከ200 በላይ በሚሆኑ መናኝ እናቶች ላይ በዛሬው ዕለት የተፈፀመውን የጦር ወንጀል የአማራ ህዝባዊ ግንባር በጥብቅ ያወግዛል

 

ሥላሴ ገደሞ የተላከ ክርሰቲያን 1 1 1
#image_title

ደብረኤልያስ ወረዳ በሚገኘው የሥላሴ አንድነት ገዳም ላይ 3 ሞርተሮችን ጨምሮ በተለያዩ ከባድና የቡድን መሳሪያዎች ጥቃት እየፈፀመ የሚገኘው የፌደራል መንግስቱ መከላከያ ኃይል፤በገዳሙ ግቢ ውስጥ ከ200 በላይ መናኝ እናቶች የሚገኙበትን ግቢ በሞርተር በመምታት ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ መነኮሳት አልቀዋል፤ሌሎችም ከፍተኛ ጉዳት አስተናግደዋል።በዚህም ገዥው የኦህዴድ ብልፅግና ስርዓት ከባድ የጦር ወንጀል ፈፅሟል።

ይህ የጦር ወንጀል በገዳሙ መናኝ እናቶች ላይ የተፈፀመው በአካባቢው የመደበኛ ስልክ ጥሪም ሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት በማቋረጥ ነው።

ይህ ድርጊት በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ህጎች ፍፁም የተከለከለ በመሆኑ፣ የዓለም አቀፍ ወንጀለኞች ፍ/ቤት(ICC) ጨምሮ የዓለም አቀፍ ማህበር ጉዳዩን በአጣዳፊ እንዲመለከተው እንጠይቃለን።

በጎጃም ደብረ ኤልያስ ጭፍጨፋ ሲፈፅም የቆየው የኦህዴድ ብልጽግና መከላከያ ሠራዊት  ዛሬ ሸበል በረንታ፣ ዲማ ጊዮርጊስ፣ የትኖራ ፣ወጀል ዓባይ ፣በመርጦ ለማሪያም፣ደብረዎርቅ እና እሁዲት-ኢናባራ አየሁ መከላከያ እንዲገባ ወስኖ ተጨማሪ የጦር ወንጀል እንዲፈፀም እያደረገ ነው።

በተመሳሳይ በሰሜን ሸዋ እንሳሮ፣ራሳ፣መርሃ ቤቴ እና ይፋት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሠራዊት በማሰማራት በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የጦር ወንጀል በኦህዴድ/ብልፅግና የሚመራው ገዢ ስርዓት እየፈፀመ ነው።

መላው የአማራ ህዝብ በሠራዊቱ እየተፈፀመበት ያለውን የጦር ወንጀል በጋራ በመሆን ሊመክት ይገባል።

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ሚዲያዎች፣የሲቪክ ማህበራት፣የሰብዓዊ መብት ተቋማት እና ሌሎችን የንፁሃን ጭፍጨፋን በአፅኖት ሊመለከቱት ይገባል።

የአማራ ህዝባዊ ግንባር
ግንቦት 23/2015 ዓ.ም

Amhara Popular front 4 1

 

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop