በሥላሴ አንድነት ገዳም ከ200 በላይ በሚሆኑ መናኝ እናቶች ላይ በዛሬው ዕለት የተፈፀመውን የጦር ወንጀል የአማራ ህዝባዊ ግንባር በጥብቅ ያወግዛል

 

#image_title

ደብረኤልያስ ወረዳ በሚገኘው የሥላሴ አንድነት ገዳም ላይ 3 ሞርተሮችን ጨምሮ በተለያዩ ከባድና የቡድን መሳሪያዎች ጥቃት እየፈፀመ የሚገኘው የፌደራል መንግስቱ መከላከያ ኃይል፤በገዳሙ ግቢ ውስጥ ከ200 በላይ መናኝ እናቶች የሚገኙበትን ግቢ በሞርተር በመምታት ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ መነኮሳት አልቀዋል፤ሌሎችም ከፍተኛ ጉዳት አስተናግደዋል።በዚህም ገዥው የኦህዴድ ብልፅግና ስርዓት ከባድ የጦር ወንጀል ፈፅሟል።

ይህ የጦር ወንጀል በገዳሙ መናኝ እናቶች ላይ የተፈፀመው በአካባቢው የመደበኛ ስልክ ጥሪም ሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት በማቋረጥ ነው።

ይህ ድርጊት በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ህጎች ፍፁም የተከለከለ በመሆኑ፣ የዓለም አቀፍ ወንጀለኞች ፍ/ቤት(ICC) ጨምሮ የዓለም አቀፍ ማህበር ጉዳዩን በአጣዳፊ እንዲመለከተው እንጠይቃለን።

በጎጃም ደብረ ኤልያስ ጭፍጨፋ ሲፈፅም የቆየው የኦህዴድ ብልጽግና መከላከያ ሠራዊት  ዛሬ ሸበል በረንታ፣ ዲማ ጊዮርጊስ፣ የትኖራ ፣ወጀል ዓባይ ፣በመርጦ ለማሪያም፣ደብረዎርቅ እና እሁዲት-ኢናባራ አየሁ መከላከያ እንዲገባ ወስኖ ተጨማሪ የጦር ወንጀል እንዲፈፀም እያደረገ ነው።

በተመሳሳይ በሰሜን ሸዋ እንሳሮ፣ራሳ፣መርሃ ቤቴ እና ይፋት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሠራዊት በማሰማራት በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የጦር ወንጀል በኦህዴድ/ብልፅግና የሚመራው ገዢ ስርዓት እየፈፀመ ነው።

መላው የአማራ ህዝብ በሠራዊቱ እየተፈፀመበት ያለውን የጦር ወንጀል በጋራ በመሆን ሊመክት ይገባል።

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ሚዲያዎች፣የሲቪክ ማህበራት፣የሰብዓዊ መብት ተቋማት እና ሌሎችን የንፁሃን ጭፍጨፋን በአፅኖት ሊመለከቱት ይገባል።

የአማራ ህዝባዊ ግንባር
ግንቦት 23/2015 ዓ.ም

 

 

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ትግላችን የኢትዮጵያን ህዝብ ማዕከል ያደረገ በኢትዮጵያ ህዝብ የታጀበና በኢትዮጵያውያን ላይ የሚተማመን ሊሆን ይገባል

2 Comments

  1. ዛሬ አደገኛው ጭራቅ ኦናግ ና ብልጽግና በወያኔ የተጀመረውን ኢትዮጵያን እንደ ሶማሊያ መበተን እንደ ሩዋንዳ እርስ በርስ ጦርነት እንዲሁም እስልምና ክርስቲያን ሃይማኖት አጥፍተው በጴንጤ ለመተካት ሥልጣኑን ለማጠናከር አማራን ከትግራይ አጋጭቶ ዛሬ አማራን በማጥፋት የቤት ሥራ ጀምረዋል ና የኢትዮጵያ ሕዝብ ነቅቶ እነዚህን ጠባብ ዘረኞችን በአንድነት መጥፋት አለበት ።
    በውጭ ሀገር የሚኖሩ ዲያስፖራ ባንኮች በኩል የምላክ ሀዋላ ገንዘብ አቁሞ በግልሠቦች በኩል መላክ ።
    የጭራቆችን መከላከያን ለማዳከም ሽምቅና ደፈጣ ውጊያን የነሱን ባንዳዎችን በሁሉም ቦታ መግደል ።
    ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ በዘር በሃይማኖት ሳይከፉፈል በአንድነት በጣልያን ፋሺሽት ጣሊያኒን ላይ ያስመዘገበው ታሪክ ዛሬም በዘረኞች ጭራቆች መድገም አለበት

  2. ዛሬ አደገኛው ጭራቅ ኦናግ ና ብልጽግና በወያኔ የተጀመረውን ኢትዮጵያን እንደ ሶማሊያ መበተን እንደ ሩዋንዳ እርስ በርስ ጦርነት እንዲሁም እስልምና ክርስቲያን ሃይማኖት አጥፍተው በጴንጤ ለመተካት ሥልጣኑን ለማጠናከር አማራን ከትግራይ አጋጭቶ ዛሬ አማራን በማጥፋት የቤት ሥራ ጀምረዋል ና የኢትዮጵያ ሕዝብ ነቅቶ እነዚህን ጠባብ ዘረኞችን በአንድነት መጥፋት አለበት ።
    በውጭ ሀገር የሚኖሩ ዲያስፖራ ባንኮች በኩል የምላክ ሀዋላ ገንዘብ አቁሞ በግልሠቦች በኩል መላክ ።
    የጭራቆችን መከላከያን ለማዳከም ሽምቅና ደፈጣ ውጊያን የነሱን ባንዳዎችን በሁሉም ቦታ መግደል ።
    ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ በዘር በሃይማኖት ሳይከፉፈል በአንድነት በጣልያን ፋሺሽት ጣሊያኒን ላይ ያስመዘገበው ታሪክ ዛሬም በዘረኞች ጭራቆች መድገም አለበት …………………….

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share