አማራ ሆይ በድርድር ስም እዳትሸወድ!! – ተዘራ አሰጉ

ድርድር ፣ ሽምግልና ፣ ሰላማዊ ውይይት ፣ ከተቀናቃኞች ፣ ከተፋላሚዎች ፣ ከተቀያየሙ ከዚያም አልፎ ደም ከተቃቡ ባለአንጣዎች ፣ ቡድኖችና ግለሰቦች ጋር ማከናወን የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊያን ቀደምት ባህላዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ሃይማኖታዊ ፣ ቤተሰባዊና በሕግ ማዕቅፍ ተካቶ የሚካሄድ የተቀደሰ  ነባራዊ ኩነት ነው።

ኢትዮጵያዊያን የቤተሰብ ሽምግልና ፣ አውጫጭኝ፣ አፍርሳታ ፣ ጉማ ፣ የዕርቅ ኮሚቴ ወዘተ እያሉ የተለያየ ስያሜ ቢሰጡትም ዞሮ ዞሮ ኢትዮጵያ ዕምቅ የሆነ የድርድርና የዕርቅ መቸቶች እንዳሏት ልብ ሊባል ይገባል።

“ልጅ ለእናቷ ምጥ አስተማረች” እንዲሉ ሆነና ሃገረ ኢትዮጵያ  በኮንጎ ፣ በቲሪፖሊ ሊቢያ፣ በኮሪያ ፣ በሱዳን ፣ በሩዋንዳ ወዘተ ሰላም አስከባሪ ፣ የመጀመርያዋ የተባበሩት መንግስታት League of Nations” የአፍሪካ ብቸኛ ተወካይ ፣ አደራዳሪ ፣ አስታራቂና ችግር ፈች ሃገር እንዳልነበረች “ የጉድ ጉዶችና አዋራጆች” ተፈጠሩና ከነበረችበት ማማ እያወረዷት ይገኛሉ።

“ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል “ እንዲሉ ነፃነታቸውን በደማችን ያስከበርንላቸው ፣ የአፍሪካ አንድነትን (OAU)ን አቋቁመን “ በክብርና በነፃነት ኑሩ” ብለን ጀባ ያልናቸው አፍሪካዊያን እኛኑ ኢትዮጵያውያን የታሪክ ባለቤትና ኩሩ ሕዝቦችን ፣”ኑ – እናስታርቃችሁ” እያሉን ነው ፣ ዘይገርም ነው።

ጊዜ ያመጣውን ጊዜ እስኪመልሰው “ “ይሁን” ከማለት ውጭ ምን ማድረግ ይቻላል ጎበዝ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በታላቁ ኢትዮጵያዊ ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴና በአጋር ጥቂት አፍሪካዊያን በሳል የዘመኑ መሪዎች የተቋቋመው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት /OAU/ የህውሃትን ከግማሽ ምዕተ ዓመታት በላይ የገነገነ ተንኮል ፣ ስግብግብነት ፣ ተስፋፊነት ፣ የመሬት ነጣቂነት ፣ ዘራፊነት ወዘተ በጥልቅ ሳይገነዘቡና ሳይብራራላቸው በደረቁ ይህን ስር የሰደደ ችግር ሊፈቱት ይቻላቸዋል ወይ? የሚለው ጥያቄ በአፅንኦት መልስ ሊያገኝ የሚገባው ጉዳይ ነው እንላለን።

ግፍ ፣ በደል ፣ ሞትና መፈናቀል ለደረሰበትና ለዓመታት ከህውሃት ጋር ፍልሚያ ላይ ለነበረ የአማራ ሕዝብ “ ከህውሃት ጋር መደራደር ጉም እንደ መዝገን” ና “ ውሃ ቅዳ ፣ ውሃ መልስ” መሆኑን አስረግጠን እንናገራለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የእስረኛው ‹‹ጋዜጠኝነት›› ሌላ ፈተና

በድርድር ስም እነ ኢዲዮን ፣ ኢሕአፓን ፣ እራሱን ደርግን ፣ ኢሰፖ ተብየውንና መሪዎቻቸውን ሁሉ ቅርጥም አርጎ የበላ ብልጣብልጥና መሠሪ ቡድን ልብ ገዝቶ ይደራደራል ማለት ዘበት ነው። ለማዘናጋት ፣ ትንፋሽ ለማግኝትና ጊዜ ለመውሰድ ካልሆነ በቀር ።

“ግራ ነፈሰ ቀኝ” ግን አሀን ባለው ተጨባጭ ሀኔታ  የድርድር ህሳቤው በራሱ ለህውሃት “ሠርግና ምላሽ” ሲሆን ለሰላም ፈላጊው ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና በተለይ ለአማራው ሕዝብ “መርዶ ተነግሮት ሃዘን ላይ ቁጭ የሚባልበት” ክስተት ነው እንላለን ። ምክንያቱም ቢሉ ህወሃት እንደ ኢሰፓ ፣ ኢሕአፓ ፣ መሄሶን፣ ኢዲዮ ወዘተ ታሪክ ሁኖ ካልከሰመ በቀር ኢትዮጵያ የሰላም እንቅልፍ ትተኛለች ብሎ ማሰብ ዘበት ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአፍሪካ አንድነት /OAU/ የተወሰኑ በግጦሽ መሬት መገፋፋት ፣ በብሄሮች መካከል በሚነሳ ግጭት ፣ በዘር ማጥፋት ወዘተና በመሳሰሉ ምክንያቶች የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ሞክሯል ፣ የተሳካለት ሁኗል ለማለት ግን ፍፁም አይቻልም።

ነገር ግን በአፍሪካ ሆነ በዓለም ታይቶ የማያውቅ በአንድ ሃገር ውስጥ እየተኖረ ለም መሬት በመፈለግ ብቻ የወልቃይትና የራያን ምድር በማናለብኝነት ነጠቆ ታላቂቷን ትግራይ የመመሥረት እኩይ ዓላማ ይዞ የተነሳው ቡድን ይህ ተንከሲስ ዓላማው ለአደራዳሪዎች በጥናት ተደግፎ በግልፅ እስካልተነገራቸው ድረስ እንዲሁም ለክፋትና ለመሰሬ አላማው ባፀደቀው ሕገ-መንግስትና ለሰላሳ ዓመታት ወልቃይት ፣ ጠገዴና ራያ በትግራይ ስር ያለአግባብ አካቶ በመኖሩ ይህን መሰሬ ኩነትና አካሄድ ተከትሎ ያለፈና የነበረው ሕገ ወጥ እካሄዱ /status quo ante/ ይጠብቅ የሚለውን  የቅዥት : ጉንጭ አልፊ የዘወትር ልፈፋውን በማንሳት ይቀጥልልኝ ስለሚል ይህንንም ድብቅ ዓላማውን አወያዮቹ አፍሪካዊያን በግልፅ ሊያውቁትና “አይሆንም  “ይህ አጉራ ዘለል ህሳቤ ለድርድር አይቀርብም” ሊባል ይገባዋል እንላለን።

“የድርድሩም ቅድመ ሁኔታ በዚህ መሰረተ ሃሳብ ታንፆ ሊጀመር የግድ እንደሆነ” እኛ መላ ኢትዮጵያዊያንና የአማራ ሕዝቦች እናሳስባለን ፣ እናስጠነቅቃለን ።

ቀደምት የኢትዮጵያ ፣ የአማራና የትግራይ ታሪካዊ ፣ ባሕላዊና ጆግራፊያዊ አቀማመጥን በተመለከተ  አደራዳሪዎች አፍሪካውያን በግልፅ ሊያውቁ ፣ ሊብራራላቸውና ግንዛቤ ሊኖራቸው የግድ የሚል ይሆናል እንላለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአገር ወዳድነት ስሜት በጠፋበትና ክህደት በበዛበት አገር ጠንካራ ኢኮኖሚና ማህበረሰብ መገንባት አይቻልም!

አይበለውና ድርድሩ ከተካሄደ ከዚህ በፊት እንደተገለፀው ድርድሩ አካታች (Inclusive)ና የተዋጣለት ይሆን ዘንድ የአማራ በተለይም የጎንደር ወልቃይት ጠገዴ ፣ የወሎ ራያ የሃገር ሽማግሌዎች ፣ የአፋር አባቶች ፣ የታሪክ አዋቂዎች ፣ ሙሁራንና የሚመለከታቸው ተቋማት ሁሉ ሊሳተፉ የግድ ይላል።

ከዚህ ጋር አያይዞ እንደአለመታደል ሆኖ አፍሪካዊያን ፣ የአፍሪካ አንድነት ድርጅትና መሪዎች /OAU/ አደራዳሪ በሆኑበት ወቅት ያጋጠመውንና በዚህ ድርድር ሊያጋጥመው የሚችለውን መሰናክሎች  ችግሮችና እፀፆች መዳሰሱ ከወዲሁ ሊከሰት የሚችሉ ሰንኮችን ለመገንዘብ ይረዳ ዘንድ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሕዝብ ፣ ተደራዳሪዎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ግንዛቤ ይኖራቸው ዘንድ እንደሚከተለው እናቀርበዋለን።

አፍሪካ አንድነት ድርጅት /OAU/ በቡርንዲ፣ በሱማሊያ ፣ በሊቢያ፣ በኮንጎ ፣ በኮትዲቪያር ፣ በደቡብ ሱዳንና መሰል የአፍሪካ ሃገሮች ግጭቶችን ለማብረድ የድርድርና የውይይት መድረኮችን አዘጋጅቶ ነበር።

አፍሪካ አንድነት ድርጅት /OAU/ መሰል ድርድሮች ሲያካሂድ ያጋጠመው ዋነኛው ችግር ድርድሩን ለማከናወን የስራ ማስኬጃ ገንዘብ እጥረትና በግጭት ለተጎዱ አካባቢዎች የምግብና የመልሶ ማቋቋም ድጋፎች የማድረግ አቅም ማነስ ዋናው ማነቆው እንደነበር የጥናት ዳሰሳዎች ያስረዳሉ።

ሌላው ተደራዳሪዎችን አስመልክቶ እውነተኛ፣ የተሟላ ፣ ወጥና ሙሉ መረጃ አደራዳሪዎች ማግኘት አለመቻል ትልቁ ክፍተትና ፈተና ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት /OAU/ እንደሆነበት የምርምር ዳፋዎች ያሳያሉ።

ከዚህ ባሻገር አደራዳሪዎች በሙስና እንደሚዘፈቁ ፣ ለወዳጅ ቡድኖች የማድላትና የመወገን ብሃሪና አካሄድ እንደሚታይባቸው የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች ይተነትናሉ።

በዚህም ምክንያት በአፍሪካ አንድነት (OAU) የሚከናወኑ ድርድሮች አሰልች ፣ የተራዘመ ጊዜ የሚወስድ ፣ የይስሙላና እጃቸው በረዘመው ምዕራባውያን ሃገሮች የሚዘወር የመሆን ምልክቶችን እንዳሉ ሳይታለም የተፈታ እውነታ ነው።

በዚህም የተነሳ “ ከድጡ ወደ ማጡ” እንዲሉ ታላቋን የአፍሪካ ቅምጥል ሃገር ሊቢያን መቀመቅ እድትገባ ምክንያት የሆነ ፣ ሱማሊያ በእርስ በርስ ግጭት እድትታመስ፣ በተፈጥሮ ሃብት ተወዳዳሪ የለላትን የኮንጎን ምድር የምድር ሲኦል እድትሆን መንስሄ የሆነው በአንድ እግሩ ያልቆመው፣ እንደ ፈረስ ተጋላቢውና አሻጉሊቱ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት /OAU/ መሆኑን የሃገሬ ህዝብ ሊያውቅ ይጋባዋል እንላለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  “በጨለማዋ አህጉር” ዋሻ ጭላንጭል ብርሃን ይታያልን?

የኢትዮጵያን መንግስት ወክለው በመምራት የሚደራደሩት የአማራው ብልፅግና መሬ የሆኑት የተከበሩ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ሆይ “ እንግዲህ ፈረሱም  ሜዳውም ይሄው” እንዲሉ ፣ እንደዚህ በፊቱ ተጋድሎዎትና ቆራጥ አቋምዎት ወያኔ -ህውሃት የኢትዮጵያን ድንበር ለሱዳን ታልፎ ይሰጥ ዘንድ ፊርማዎን ያስቀምጡ ሲባሉ “ የኢትዮጵያ መሬትን አሳልፌ ለሱዳን መስጠት አይዋጥልኝም ፣ አሻፋረኝ” እንዳሉት ሁሉ ፣ አሁንም “ ወልቃይት ፣ ጠገዴ ፣ ሰቲት ሁመራና ራያ  “ የአማራ እንጂ የትግራይ ሆኖ ፣ አያውቅም ፣ ሉድርድርም አይቀርብም “ በማለት ለሃገርና ከማህፀኗ ለውጡበት የአማራ ሕዝብ ዘብ እንደሚቆሙና የታሪክ አሻራዎን በድጋሜ ያድሳሉ ብለን   እንጠብቃለን ፣ “አደራ በምድር ፣ አደራ በሰማይ”  እኛ ኢትዮጵያዊያንና የአማራ ወገኖችዎ ከልብ በመነጨ እሳቦት  እናሳስበዎታለን።

በመጨረሻም የአማራ ሕዝብ ሆይ በድርድር ስም የተዘጋጀልህን ወጥመድ እድታውቅ ፣ እድትረዳና ጉዳዩን በአፅንኦት እድትከታታል በአደራ ስም እናሳስባለን ።

አምስት ሚሊዮን የማይሞላ አማፂ ፣ ዘራፊና ስግብግብ ህወሃት የተባለ ቡድን ለድርድር ሲጠራ ከአምሳ ሚሊዮን በላይ የሆንከው የአማራ ሕዝብ እንዲህም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የዚህ ሰው ሰራሽ ግጭት ገፈት ቀማሽ የሆንከው ትሁቱ የአፋር ሕዝብ በድርድሩ ያልተካታታችሁበትን መንስሄና የጀርባ ውጥን ሴራን ልትመረምሩ የግድ ይላል እንላችኋለን።

በመጨረሻም “ጀሮ ያለው ይስማ” እንዲሉ የህውሃት የአራት ኪሎ የሚኒልክ ቤተመንግስት ህልም እንደ ጉም ቢትንም ፣ የወልቃይትና የራያን ጉዳይ ለድርድር ማቅረቡ አይቀሬ ስለሚመስል ፣ አራት ኪሎ የከተሙት የዘመኑ ሹመኞች ሥልጣናቸውን የሚቀናቀን እስከሌለ ድረስ የወልይቃት ፣ ጠገዴና የራያን ጉዳይ ለድርድር ቢቀርብ ጉዳያቸው እንደማይሆን ህሳቤ ስላለ የአማራ ሕዝብ ሆይ “  በድርድር ስም እዳትሸወድ” ጥንቃቄ አድርግ ብለን እንመክራለን።

ተዘራ አሰጉ

ከምድረ እንግሊዝ

4 Comments

  1. ያለው መንግስት ትንሽ ስለ ክብሩ አያስብም? ወይም አፍ አውጥቶ ተሸንፊያለሁ ማስተባበር አልቻልኩም ብሎ እጅ አይሰጥም? አገርን ግጦ የበላ፤ዜጎችን ያራቆት ፤በወንጀል የተጨማለቀ፤በፓርላማ የተወገዘና የኢትዮጵያ ጠላትነቱ የተረጋገጠን ጠላት ምን ብለህ ነው የምትደራደረው በህግ ትገትረዋለህ እንጂ፡፡ አሜሪካ ስላዘዘ የአንድ ሃገር ሉዋላዊነት አይጣስም፡፡ ኢሳይያስ አፈወርቅ የማስፈራሪያን የማስጠንቀቂያ ብዛት ሲወርድበት እንደ ሰሜን ኮሪያው ገዥ ሲያላግጥባቸው እዚህ ደርሷል ኦሮሙማ ምን አርበደበደው ዞር በሉ ማለት ምን ከበደው? 140 ሚሊዮን ህዝብ ይዟል አሜሪካ ትግሬዎችን እረዳለሁ ካለ ለኢትዮጵያ ራሺያ ቱርክ አሉ ኢትዮጵያን እንጅ ከትግሬ አተርፋለሁ የሚል የውጭ ሃይል አይኖርም ቢኖርም ከዚህ ወንጀለኛ ድርጅት ጋር ቃልን አጥፎ መቀመጥ አግባብነት የለውም፡፡ስለ ደመቀ መኮንን የተናገርከው ሃቅህን አስተካክል ደመቀ መኮንን፤አገኘሁ ተሻገር የአማራውን መከራ ያበዙ ክህወአት ያላነሱ ግለሰቦች ናቸው የአማራ ጠላቶች በመምቻ ብትርነት ነው የሚጠቀሙባቸው፡፡ አማራ በማንኛውም መንገድ ይህን ድርድር በቀላሉ ሊያይ አይገባውም፡፡ ድርድሩ ላይ ሊቀመጡ የሚገባቸው ፋኖ፤የአማራ ማህበራት እውቅ የአማራ ምሁራን (አቻምየለህ ታምሩ፤ፕሮፌሰር መስፍን አረጋ፤ዮሃንስ ቧያለው፤ፕሮፌሰር ሃብታሙ መንገስቴ ተገኘ፤የወልቃይት ኮሚቴ ፤ ኮለኔል ደነቀ ፤ሃስን ከረሙ፤ የአፋር ኮሚቴ፤የራያ ኮሚቴ፤ፋኖን የመሳሰሉ ድርጅቶች መሆን ሲገባቸው ከሁናቴው ጋር ተያይዥነት የሌላቸው ግለሰቦች በተዘዋዋሪ እነ ሽመልስ አብዲሳ ጁዋር መሃመድ ይህን ድርድር እንዲሳተፉ ማድረግ ውጤቱ በጣም የከፋ እንደሚሆን ግልጽ ነው፡፡ አማራ ሰዶ ማሳደድ እንዳይሆንብህ ባለህበት ሁሉ እዚህ ነገር ላይ አይንህን ሳትከድን መቃወም ይኖርብሃል፡፡ የምን ድርድር ነው ህወአት የሚለው የሰው ንብረት ስጡኝ ነው፤ መልሼ ደም ካልመጠጥኩ ነው፡፡ ምን አይነት ለራሱ ክብር የሌለው መንግስት ነው ኢትዮጵያን የሚያስተዳድረው፡፤

  2. ወንድሜ “አሳን መብላት በብልሃት” እንዲሉ ስንራመድ እንቅፋት እንዳይመታን ዳፋውን በትኩረት ፣ በብልሃት ፣ በማስተዋልና በሚያዋጣ መልኩ መውጣት አለብን። ሃሳብህ መልካም ነው ግን እንዴት ተግባራዊ ይሁን የሚለው በሰከነ መልኩ ሊኬድበት የግድ ይላል።

  3. Demeke Mekonen and his other Amhara colleagues have a historical moment to right their numerous wrongs. If they stand up for Amhara interests in respect of Wolkait-Tegede, Humera, Raya etc the Amhara people will forgive them the wrongs they made in the last 30 years. Would they stand in the right side of Amhara History by securing the ancestral lands of Amhara which had been repossessed with the sacrifice of tens of thousands of Amharas and the Ethiopian Armed Forces?.That we will see in the future. TPLF will never ever cease to claim the above lands while it is alive. Its demise only guarantees the stoppage of these illegitimate and unfounded claims. All Amharas for One Amhara, One Amhara for All Amharas.

  4. Yelemchen I very much doubt, a bad actor is always bad, this people were purposely selected from their dead careers and gave them material privilege which they haven’t thought about it. They prefer to die rather than changing their course of action in line with principle, loyalty and other human measures. Abyi choosing deadly Amhara’s enemies like Alemhewu Mekonen and Shiferawu Shigutea in his new post. Follow him and deduce where these things take us.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share