የኢትዮጵያ ጂዲፒ ስድስት ትሪሊዮን ሁለት መቶ ሃያ ሁለት ቢሊዮን ብር ተመነደገ!!! (122 ቢሊዮን ዶላር!!!) የመደመር ኢኮኖሚክስ!!! ‹‹ምን ቢታለብ በገሌ!

ኢት-ኢኮኖሚ /ET-ECONOMY
(ክፍል 1)  ሚሊዮን ዘአማኑኤልና ፂዮን ዘማርያም  (ኢት-ኢኮኖሚ

ድመቷ ጥቁር ወይ ነጭ ሆነች አልሆነች ግድ የለም፣ ዓይጥ እስከያዘች ድረስ! ‹‹It doesn’t matter if a cat is black or white, so long as it catches mice.››Deng Xiaoping Quotes

የኢትዩጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፅፀም ዳሰሳ 

ዶክተር አብይ አህመድ የብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አፈፅፀምን  በተመለከተ ባቀረቡት ሪፖርት
•       የውጭ ንግድ ኤክስፖርት 4.12 (አራት ነጥብ አስራሁለት)  ቢሊዮን ዶላር
•       የአገልግሎት ወጭ ንግድ 6.3 (ስድስት ነጥብ ሦስት ቢሊዮን ዶላር  )
•       የውጭ ንግድ ኤክስፖርትና የአገልግሎት ወጭ ንግድ  በመደመር  ቲዬሪው  ተጠቅሞ 10.3 (አስር ነጥብ ሦስት) ቢሊዮን ዶላር  አደረስው በመቀጠልም ከዲያስፖራዎች ለቤተሰብ የሚላክ ሃዋላ (Remittance)  እና ቀጥተኛ የውጭ መዋለ-ንዋይ (Foreign Direct Investment)  ሲደመሩ 20 (ሃያ) ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ የመደመር  ፍልስፍናቸውን  ኢኮኖሚክሱን እንደማያውቁ  አስመስክረዋል፡፡   የአገልግሎት ወጭ ንግድ 6.3 ቢሊዮን ዶላር  ውስጥ የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ 4.75 ቢሊዮን ዶላር  ያልተጣራ ገቢ ያስገኘ ሲሆን ቀሪው  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ኢትዮቴሌ ወዘተ የተገኘ ያልተጣራ ገቢ ነው፡፡ዶክተር አብይ አህመድ የውጭ ንግድ፣የአገልግሎት ወጭ ንግድ፣ ሃዋላና ኤፍዲአይን ገቢዎች በአንድ ላይ በመደመር ለማምታታት የተጠቀሙበት ማጭበርበር  ትውልድ ያሳስታል፡፡ዶክተር አብይ ወተቱም፣ እርጎውም፣ ቅቤውም  ኬኛ በማለት ‹‹ድመቷ ጥቁር ወይ ነጭ ሆነች አልሆነች ግድ የለም፣ ዓይጥ እስከያዘች ድረስ!››ብለውናል፡፡

 

{1} የኢትዮጵያ ብሄራዊ  አማካይ  ጠቅላላ  አመታዊ  ምርት (GDP)

በ1991እኤአ (1983ዓ/ም) ብሄራዊ አማካይ ጠቅላላ አመታዊ ምርት (GDP) 10,535 ቢሊዩን ብር የነበረ ሲሆን በግዜው (አንድ ዶላር በ2.07 ብር እኩሌታ ይመነዘር ነበር) በ2015 እኤአ (2008 አ/ም) ብሄራዊ አማካይ ጠቅላላ አመታዊ ምርት 1,300,000,000 (አንድ ትሪሊየን ሦስት መቶ ቢሊዮን) ብር ሲሆን (አንድ ዶላር በ21.83 ብር እኩሌታ ይመነዘር ነበር) የሃገሪቱ ጂዲፒ እድገቱ በ123 እጅ ማለትም አስራ ሁለት ዕጥፍ እንዲደርስ አንዳደረገው ይስተዋላል፡፡ (አንድ ዶላር በ2.07 ብር እኩሌታ ወደ 21.83 ማደግ በ9.5 በመቶ አምስት እጥፍ በላይ የውጪ ምንዛሪው በማደጉ የብሄራዊ አማካይ ጠቅላላ አመታዊ ምርት ስሌት እንዲጨምር አደረገው፡፡)

ተጨማሪ ያንብቡ:  በፊች የደረጃ ምደባ፣ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ደረጃ ሲሲሲ ኔጌቲቭ አሽቆለቆለ! የቆሎ ተማሪ እዳ፣ የዕለት እንጀራችንን ስጠን!

የብር መንዛሪ መርከስ ሁኔታ ማለትም በዓለም አቀፍ ንግድ ገበያ የኢትዩጵያ ብር የመሸጥና የመግዛት አቅም እንደተሸመደመደ ያሳያል፡፡ አገሪቱ በውጪ ንግድ የምትልካቸው ምርቶች ዋጋ መቀነስን አስመዝግቦል፡፡ እንዲሁም አገሪቱ በገቢ ንግድ የምታስገባቸው ካፒታል ጉድስ እቃዎች ዋጋ በመጨመሩ የዶላር  የመግዛት አቅም በ9.5 በመቶ ማለትም አምስት እጥፍ በላይ በመጨመሩ ሃገሪቱ በገቢ ንግድ ተጎጂ ሆናለች ማለት ነው፡፡ በመሆኑም የብሄራዊ አማካይ ጠቅላላ አመታዊ ምርት (GDP) ከቢሊዩን ብር ወደ ትሪሊዩን ብር እምርታ ማሳየቱ የኢኮኖሚ እድገትን አያመላክትም፣ የብር መርከስንና የመግዛት አቅም መቀነስን ነው የሚያሳየው፡፡

በ2022እኤአ ብሄራዊ አማካይ ጠቅላላ አመታዊ ምርት (GDP) 112,000,000,000 (መቶ አስራ ሁለት) ቢሊዩን ዶለር ሲሆን በኢትዮጵያ ብር 6,222,000,000,000 (ስድስት ትሪሊዮን ሁለት መቶ ሃያ ሁለት ቢሊዮን ) ብር መድረሱ የኢትዮጵያ የብር ምንዛሪ በመርከሱ የተነሳ የመጣ የቁጥር ግዝፈት (አንድ ዶላር በሃምሳ አንድ ብር) በመመንዘሩ የተገኘ ስሌት ሲሆን ‹‹ወጣ ወጣና እንደ ሸንበቆ ተንከባለለ እንደ ሙቀጫ!!!›› ተብሎለታል፡፡

Ethiopia GDP The Gross Domestic Product (GDP) in Ethiopia was worth 111.27 billion US dollars in 2021, according to official data from the World Bank. The GDP value of Ethiopia represents 0.01 percent of the world economy. source: World Bank

GDP in Ethiopia is expected to reach 112.00 USD Billion by the end of 2022, according to Trading Economics global macro models and analysts expectations. In the long-term, the Ethiopia GDP is projected to trend around 115.00 USD Billion in 2023, according to our econometric models.

የውጭ ምንዛሪ ተመን የአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን ከአመት ወደ አመት እየረከሰ መሄድ ማለትም፣ የአንድ ዶላር የብር ተመን በ1991 እኤአ 2.05 ብር የነበረ ሲሆን፣ ከ1992 እስከ 1994 እኤአ ወደ 5 ብር፣ ከ1995 እስከ 1999 እኤአ 5.88 ብር፣ ከ2000 እስከ 2004 እኤአ 8.15ብር፣ ከ2005 እስከ 2008 እኤአ 8.65 እስከ 9.67 ብር አንድ አሃዝ እየረከሰ ሄድ፡፡  ከ2009 እስከ 2015 እኤአ የአንድ ዶላር የብር ተመን ወደ ሁለት አሃዝ እየረከሰ ከ12.39 ብር ወደ 21.83 ብር፣ ከ2016 እስከ 2022 እኤአ የአንድ ዶላር የብር ተመን ወደ ሁለት አሃዝ እየረከሰ ከ22.39 ብር ወደ 51.00 ብር  የብራችን የመርከስና የብር የመግዛት አቅም መውደቅ ዋና ምክንት የተደላደለና የረጋ የውጭ ምንዛሪ ተመን አለመኖሩን በቀላሉ ለመረዳት ይቻላል፡፡ በጥቁር ገበያ አንድ ዶላር ከ82 እስከ 84 ብር ይመነዘራል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ቀውስና የአይኤምኤፍና የዓለም ባንክ  ፕራይቬታይዜሽን ሴራ!! - (ክፍል 3)  

የብሄራዊ አማካይ ጠቅላላ አመታዊ ምርት (GDP) እድገት መገለጫዎች በሃገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች፣በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች መረጋገጥ አለበት፡፡የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በግብርና ዘርፍ ላይ ጥገኛ ነው፡፡ ግብርና ዘርፍ አማካይ የሃገር ውስጥ ምርት (GDP) 40 በመቶ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ ግብርና 80 በመቶ ወደ ውጭ የሚላክ ምርቶች ገቢ በማስገኘት የውጭ ምንዛሪ ያስገኛል፡፡ ግብርና ዘርፍ 75 በመቶ የሰው ኃይል ይሸፍናል፡፡

 

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፅፀም ሁሉን የኢኮኖሚ ዘርፍ የመደመር ቅዥት 

{1} የግብርናው ዘርፍ ምርቶች የእህል፣የሰብል፣ካሽ ክሮፕስ፣ብና፣ሰሊጥ፣የቅባት እህሎች፣ አትክልታና ጥራጥሬ፣ የአበባ ምርት  የመሳሰሉትን ያካትታል፡፡ የአንድ ዶለር በ51 ብር እየረከሰ በመሄዱ የግብርና ምርት በተለይ ቡና፣ በርካሽ ተቸብችቦል፣ ቡና አንድ ቢሊዮን ዶላር ሊሸጥ ችሎል፡፡

{2} የኢንዱስትሪው ዘርፍ ምርትና ሸቀጦች የማዕድን ምርቶች፣(ወርቅ፣ ታንታለም፣ ብረት፣) የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች (ልብስና አልባሳቶች)፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ የስካር፣ የዘይት፣ የዱቄት፣ የወተት፣ የሲሚንቶ ምርቶች፣ አምራች ፋብሪካዎችን ምርቶች ያካትታል፡፡ በ2013 እና 2014ዓ/ም በኢትዮጵያ ውስጥ 404 (አራት መቶ አራት) ፋብሪካዎች ተዘግተዋል፡፡ ዋና ምክንያቱም በውጭ ምንዛሪ እጦት የተነሳ የፋብሪካዎቹ ግብአት አለማግኘት፣ የስፔር ፓርት (መለዋወጭ) እጦት፣ ወዘተ ናቸው፡፡ የብሔራዊ ማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ስለዚህ ጉዳይ ትንፍሽም አላለ፡፡  ማዕድን ሚኒስቴር ተከለ ዑማ የ900 (ዘጠኝ መቶ) ማዕድን  ላኪዎችን በመሠረዝ ማዕድን ሚኒስቴር ተዘግቶል ማለት ይቻላል፡፡ የአጉዋ ጉዳይ ተከድኖ ይብሰል፡፡ አዲዬስ ኢኮኖሚ!!! …..አልታይህ አለኝ ያገሬ ሠማይ፣

 

{3} የአገልግሎት ዘርፍ የአየር፣የየብስና ባህር ትራንስፖርት አገልግሎቶች፣ የቱሪዝምና ሆቴሎች፣ የቴሌኮም፣ የኤሌትሪክ ኃይል አገልግሎቶች ሽያጭ በየአመቱ በምን ያህል አደገ? ምን ያህል የውጭ መንዛሪ አስገኙ?

  • 1‹‹ኤክስፖርት ኦፍ ስርቪስ›› የአገልግሎት ዘርፍ ሲሆን በውስጡ የሚካተቱት (1ኛ) ቱሪዝም (2ኛ) የኢትዩጵያ አየር መንገድ   (3ኛ) የኢትዩጵያ ንግድ መርከብ (4ኛ) የኢትዩጵያ ቴሌኮም (5ኛ) የኢትዩጵያ ኤሌትሪክ ኃይል ወዘተ የአገልግሎትዘርፍ ውስጥ የሚካተቱ ናቸው፡፡
  • 2 የቱሪዝምና ሆቴሎች፣ አገልግሎቶች ይካተታሉ
    3.3 ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት፣ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት ቀጥተኛ የውጭ  መዋለ-ንዋይ ፍሰት የሃገሪቱን መሠረተ ልማቶች እድገት በማሳለጥ፣ ምርታማነትን በመጨመር፣ እና የሰው ኃይል ልማትን በማሳደግ አዲስ ሥራ በመፍጠር ኢኮኖሚውን ያሳድጋል፡፡ በተጨማሪም አዲስ ቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግርና ክህሎት  በማዘመን የውጭ ምንዛሪ ኃብት ያስገኛል፡፡‹‹Foreign direct investment (FDI) is critical to a country’s economic development. The entry of foreign cash has allowed Ethiopia to improve its infrastructure, increase productivity, and increase employment. FDI also serves as a vehicle for acquiring sophisticated technology and mobilizing foreign exchange reserves.Jun 18, 2022››
  • 4  ብድር
  • 5 ዕርዳታ በሰለጠኑትዓለም ያሉ ሌሎች የአገልግሎት ዘርፍ ውስጥ (1ኛ) ሴክስ ቱሪዝም (2ኛ) የህክምና አገልግሎት (3ኛ) የትምህርት አገልግሎት (4ኛ) የፊልም ኢንዱስትሪ (5ኛ) የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ምርት ሽያጭ (6ኛ) ጌምና ልዩ ልዩ ሶፍት ዌሮች ምርቶች ሽያጭ (7ኛ) የመጽኃፍትና የኤሌክትሮኒክስ መፅሃፍት ሽያጭ (8ኛ) የኢንተርኔት ኢኮኖሚ አገልግሎት (9ኛ) የጠፈር ቱሪዝም (ለአንድ ሰው በመንኮራኩር ወደ ጠፈር ጉብኝት ለማድረግ 20 ሚሊዩን ዶላር በማስከፈል አገልግሎት ይሰጣል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ቀውስና የአይኤምኤፍና የዓለም ባንክ ፕራይቬታይዜሽን ሴራ!!! የብሔራዊ የጋራ ኃብታችን በኦሮሙማ ውርስና ስልቀጣ?

 

ምንጭ

(1) Ethiopia Imports, percent of GDP – data, chart | TheGlobalEconomy.com

(2) Ethiopia External debt – data, chart | TheGlobalEconomy.com

(3) Ethiopia Remittances – data, chart | TheGlobalEconomy.com

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

3 Comments

  1. አቶ ሚሊዮን ዘአማኑኤል ፦
    በኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብትላይና በተረኞቹ ኦሮሙማወች የተጨመላለለቀ (ሆን ተብሎ ) የኢኮኖሚ አመራር ላይ የምታቀርባቸውን የበሰሉ ጽሁፎችህን እንከታተላለን፡፡ በዘርፉ ስለእውቀትህና አሰልቺ ስለሆነው የኦሮሙማን ሌብነትና ዘረፋን ማጋለጥህን ስለመቀጠልህ አድናቆት አለን፡፡
    ይህንኑ አስተሳስብህን ያጠናክርልህ ዘንድ የኢኮኖሚ ፕሮፌሰሩና የኦሮሞው ተወላጅ የሆኑት ፕሮፊሰር በፈቃዱ ደግፌ “ዱሮና ዘንድሮ” በሚለው የዱሮ ታዋቂ ሰወችን የሚያወያየው የኢሳት ፕሮግራም ላይ ፕሮፌሰሩ ቀርበው “አብይ የሚመራው የአሁኑ ኢኮኖሚ አመራር ስህተት ነው”” ሲሉ ተችተውታል፡፡ ገበያ መር ወይንም መንግስት መር የሚባል የኢኮኖሚ አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ ያለው በወረቀት ላይ ብቻ እንጅ መሬት ላይ በተግባር አይሰራም፡፡ አልሰራምም ሲሉ አስረድተዋል፡፡ የሁለቱ ጥምረት በትክክለኛ አሥተዳደር ሲጣመር ብቻ ነው ስምረትና ውዑጤት የሚኖረው ሲሉም በስፋት ዘርዝረው አስረድተዋል፡፡
    ሳያውቁት ቀርተው ሳይሆን ሽማግሌ ስለሆኑ ይመስለኛል ኦርሙማ “”በተረኝነትና ዘረኝነት ተወጥሮ”” የሚሰራው ሌብነትና ዝርፊያ ግዲያና ጭፍጨፋ ላይ ምንም አላሉም፡፡ ተማሪያቸው ስለነበርኩ አሁንም ስለሙያቸው አድንቂያቸው ነኝ!!!
    የበሻሻው ጩልሌ አብይ አህመድ አሊ በወፍዘራሽነት መጥቶ በጥራዝነጠቅነት የሚያደናግረው ጥቂት ለሆዳቸው ያደሩ ትርፍ አንጀትቶቹን የአማራ ሹመኞችን ምርኩዝ አድርጎና ተረኞቹን የኦሮሙማ ጅቦች መደላድል አድርጎ እንጅ ችሎታ ኖሮት ወይንም ህዝባዊነት ተሰምቶት አይደለም፡፤ ጊዜው የእንብላው ጊዜ ስለሆነ እየተጠቀመበት ነው፡፤
    እንደ ጅብ አንበሳና ነብር በጋራ ለአደን ተሰማርተው እንደተፈጸመው ተረት ሆነ ነገሩ፡፡ ተረቱ በአጭሩ እንደዚህ ነው፡፡ የጅብን “እንብላው” አስረግጦ የሚያሳይ ነው፡፡ ሶስቱም እንሰሳት አደን ላይ ቆይተውና አድነው በልተው ሆዳቸው ስለሞላ የተረፉትን ያደኗቸውን እንሰሳት ስጋ በሚመለከት ይህንን አሁን ሆዳችን ስለሞላ ለነገ ይደርልን ብለው አንበሳና ነብር ይነጋገራሉ፡፡ ጅብ ሆየ ይህንን ይሰማና የሚከተለውን ሀሳብ ያቀርባል፡፡ እንብላው ካላችሁ እንብላው፤ አንብላው ካላችሁም እንብላው ብሎ እርፍ አለ አያ ጅቦ፡፡
    የኦሮሙማ ጅብነት በታሪክ ወደር የለውም፡፤ ወያኔን ማረኝ ያስብላል፡፡
    ስለቅሌታሙ አብይ አህምመድ ከራሱ አንደበት በቅርቡ የሰማሁትን ትዝብትን ላጋራችሁ፡፡ መቼም አብይን ትዝብት አይታክተውም መጥኔ!! እስኪ ይታያችሁ ትክክለኛውን የእስልምና ጉባኤ አስገልብጦ ለኦህደድ የሚመችአ በአክራሪወች የሚመራ አዲስ ዪትዮጵያ እስልማን ኡላማወችን ሲያስመርጥ የተናገረውን እናስታውስ፡፤ ድርጊቱ ዉጉዝ ነው፡፡ ሀራም ነው፡፡ የኢትዮጵያ እስላሞች አይቀበሉትም ብቻ ሳይሆን አምርረው ይዋጉታል፡፡
    ወራዳው አብይ በዚያ ስብሰባ ላይ ያለውን ልጥቀሰ፦ <>>
    እምዬ ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት መሽረፊቱ አብይ አህመድ እርሱ ራሱ ከንቲባ፣ እርሱ ራኡ ጠ/ሚ/ር፣ እርሱ ራሱ የከተማ ልማት ሰራተኛ፣እርሱ ራሱ ቀያሽ፣ እርሱ ራሱ ህግ፣ እርሱ ራሱ አዋጅና እርሱ ራሱ አስክሬን በዘር ቆጣሪ የሆነባት አገር ሆናለች፡፡
    አቶ ሚሊዮን ዘአማኑኤል፦
    በርታ!! ተረኛውን ኦሮሙማ ማጋለጥህን ቀጥልበት፡፤ ፍሪውን ወደፊት ታየዋለህና፡፡ እንንደ ዜጋም አገርህን በሙያህ ህዝብህን በማንቃት እያገለገልክ ስለሆነ ምስጋና ይገባሀል፡፡

  2. አቶ ሚሊዮን ዘአማኑኤል ፦
    በኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ላይና በተረኞቹ ኦሮሙማወች የተጨመላለለቀ (ሆን ተብሎ ) የኢኮኖሚ አመራር ላይ የምታቀርባቸውን የበሰሉ ጽሁፎችህን እንከታተላለን፡፡ በዘርፉ ስለ እውቀትህና አሰልቺ ስለሆነው የኦሮሙማን ሌብነትና ዘረፋን ማጋለጥህን ስለመቀጠልህ አድናቆት አለን፡፡
    ይህንኑ አስተሳስብህን ያጠናክርልህ ዘንድ የኢኮኖሚ ፕሮፌሰሩና የኦሮሞው ተወላጅ የሆኑት ፕሮፊሰር በፈቃዱ ደግፌ “ዱሮና ዘንድሮ” በሚለው የዱሮ ታዋቂ ሰወችን የሚያወያየው የኢሳት ፕሮግራም ላይ ፕሮፌሰሩ ቀርበው “አብይ የሚመራው የአሁኑ ኢኮኖሚ አመራር ስህተት ነው”” ሲሉ ተችተውታል፡፡ ገበያ መር ወይንም መንግስት መር የሚባል የኢኮኖሚ አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ ያለው በወረቀት ላይ ብቻ እንጅ መሬት ላይ በተግባር አይሰራም፡፡ አልሰራምም ሲሉ አስረድተዋል፡፡ የሁለቱ ጥምረት በትክክለኛ አሥተዳደር ሲጣመር ብቻ ነው ስምረትና ውዑጤት የሚኖረው ሲሉም በስፋት ዘርዝረው አስረድተዋል፡፡ ሳያውቁት ቀርተው ሳይሆን ሽማግሌ ስለሆኑ ይመስለኛል ኦርሙማ “”በተረኝነትና ዘረኝነት ተወጥሮ”” በሚሰራው ሌብነትና ዝርፊያ ግዲያና ጭፍጨፋ ላይ ምንም አላሉም፡፡ ተማሪያቸው ስለነበርኩ አሁንም ስለሙያቸው አድንቂያቸው ነኝ!!!
    የበሻሻው ጩልሌ አብይ አህመድ አሊ በወፍዘራሽነት መጥቶ በጥራዝነጠቅነት የሚያደናግረው ጥቂት ለሆዳቸው ያደሩ ትርፍ አንጀትቶቹን የአማራ ሹመኞችን ምርኩዝ አድርጎና ተረኞቹን የኦሮሙማ ጅቦች መደላድል አድርጎ እንጅ ችሎታ ኖሮት ወይንም ህዝባዊነት ተሰምቶት አይደለም፡፤ ጊዜው የእንብላው ጊዜ ስለሆነ እየተጠቀመበት ነው፡፤
    እንደ ጅብ ፣አንበሳና ነብር በጋራ ለአደን ተሰማርተው እንደተፈጸመው ተረት ሆነ ነገሩ፡፡ ተረቱ በአጭሩ እንደዚህ ነው፡፡ የጅብን “እንብላው” አስረግጦ የሚያሳይ ነው፡፡ ሶስቱም እንሰሳት አደን ላይ ቆይተውና አድነው በልተው ሆዳቸው ስለሞላ የተረፉትን ያደኗቸውን እንሰሳት ስጋ በሚመለከት ይህንን አሁን ሆዳችን ስለሞላ ለነገ ይደርልን ብለው አንበሳና ነብር ይነጋገራሉ፡፡ ጅብ ሆየ ይህንን ይሰማና የሚከተለውን ሀሳብ ያቀርባል፡፡ እንብላው ካላችሁ እንብላው፤ አንብላው ካላችሁም እንብላው ብሎ እርፍ አለ አያ ጅቦ፡፡
    የኦሮሙማ ጅብነት በታሪክ ወደር የለውም፡፤ ወያኔን ማረኝ ያስብላል፡፡ ስለቅሌታሙ አብይ አህምመድ ከራሱ አንደበት በቅርቡ የሰማሁትን ትዝብትን ላጋራችሁ፡፡ መቼም አብይን ትዝብት አይታክተውም መጥኔ!! እስኪ ይታያችሁ ትክክለኛውን የእስልምና ጉባኤ አስገልብጦ ለኦህደድ የሚመችአ በአክራሪወች የሚመራ አዲስ የኢትዮጵያ እስልምና ኡላማወችን ሲያስመርጥ የተናገረውን እናስታውስ፡፡ድርጊቱ ዉጉዝ ነው፡፡ ሀራም ነው፡፡ የኢትዮጵያ እስላሞች አይቀበሉትም ብቻ ሳይሆን አምርረው ይዋጉታል፡፡
    በዚያ አሳፋሪ የወራዶች ስብስበአ ላይ አብይ በራሱ አንደበት የተናገረው እንደዚህ ብሎ ነበር፡፡
    <> ብሏል፡፡
    እምዬ ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት መሽረፊቱ አብይ አህመድ እርሱ ራሱ ከንቲባ፣ እርሱ ራኡ ጠ/ሚ/ር፣ እርሱ ራሱ የከተማ ልማት ሰራተኛ፣እርሱ ራሱ ቀያሽ፣ እርሱ ራሱ ህግ፣ እርሱ ራሱ አዋጅና እርሱ ራሱ አስክሬን በዘር ቆጣሪ የሆነባት አገር ሆናለች፡፡ አቶ ሚሊዮን ዘአማኑኤል፦ በርታ!! ተረኛውን ኦሮሙማ ማጋለጥህን ቀጥልበት፡፤ ፍሪውን ወደፊት ታየዋለህና፡፡ እንንደ ዜጋም አገርህን በሙያህ ህዝብህን በማንቃት እያገለገልክ ስለሆነ ምስጋና ይገባሀል፡፡

  3. ከይቅርታ ጋር እውነቱ ቢሆን ነኝ –
    ከላይ ባስቀመጥኩት አስተያየቴ ላይ አብይ አህመድ ሸራተን ሆቴል ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች ኡላማ መሪነት በራሱ ቀጭን ትእዛዝ የኦህዴዱን ካድሬ ኦቦ ኢብራሂም ቱፋን አስመርጦ ካበቃ በኋላ ተሿሚውም ነባሩም (ትክክለኛው የሙስሊሞች መሪ የነበሩት ሸህ እዲሪስ ) ባሉበት ስብሰባ ላይ ራሱን ከነገሩ ነጻ የሆነ ለማስመሰል የተናገረውን ለመግለጽ አሳፋሪ ንግግሩን በዚህ ምልክት ውስጥ አስገብቼ አቅርቤው ነበር፡፡ ነገር ግን ምልክቱ ብቻ ወጣ እንጅ በውስጡ ያስቀመጥኩት የአብይ አህመድ የተናገረው ጽሁፉ ስላልወጣ ጽሁፉን ሰንካላ አድርጎታል፡፡ ደግሜም ሞከርኩት”” አሁንም አልወጣም፡፡ የሆነ ጽሁፍ በዚህ ምልክት ውስጥ ከሆነእንደማይወጣ ገባኝ፡፡ ስለዚህ ከይቅርታ ጋር አሁን በዚህች አጭር ማስተካከያ ለተሰብሳቢወቹ አብይ ምን ብሎ እንደተመጻደቀ መልእክቱን ከምልክቱ ውጭ አውጥቼ አቅርቤዋለሁ፡፡
    …….. አቡበከርን ይዤ ራሴ መኪና እያሽከረከርኩ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለመስጊድ መስሪያ የሚሆን ቦታ ፍለጋ ወጣሁ፡፡ መጨረሻም የአፍሪካ ህብረት አጠገብ አንድ ቦታ አገኘሁና መስጊዱን እዚህ ላይ ስሩት አልኩት፡፡ ……

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share