June 12, 2022
3 mins read

ዛሬም ባለጊዜው ኦነግ ብልግና

በፈቃዱ ሀይሉ

ባለፈው ጎበዜ ሲሳይ፣ አሁን ደግሞ ሜሮን ታደለ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ነን ባሉ አካላት ታፍነው ተለቅቀዋል። እንዲህ ዓይነቱ አፈና እና እስር በአገራችን ነባር ነው። በደርግ ጊዜ ታፍነው የተወሰዱ ሰዎች የሚሰቃዩበት ድብቅ እስር ቤት “ቤርሙዳ” ይባል ነበር። በኢሕአዴግ ጊዜም የድምፃችን ይሰማ ሰዎች፣ የመጀመሪያው ዙር የማስተር ፕላኑ ተቃውሞ ጊዜ የታሰሩ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በኢሕአዴጉ ቤርሙዳ ውስጥ አልፈዋል። የሜሮን ታደለን ቃለ ምልልስ ስሰማም ድርጊቱ ልክ የኢሕአዴጉ ቤርሙዳ ውስጥ የገቡ ሰዎች የተደረገባቸውን ዓይነት የነገሩኝን ይመስላል። ልዩነቱ አካላዊ ማሰቃየቱ መቅረቱ ነው። ጎበዜም፣ ሜሮንም የብልፅግና ቤርሙዳ ውስጥ ገብተው ወጥተዋል። ነገርዬው ሁሉ ወለፈንዴ የሚሆንባችሁ ይህ ድርጊት የሕግ ማስከበር ዘመቻው አካል መሆኑን ስትሰሙ ነው (ያው መንግሥት አላፈንኳቸውም ብሎ አልካደም፤ ቢክድም አፋኙን አካል ለሕግ የማቅረብ ዕዳ አለበት።)
ሕጋዊ ስርዓት እና የሕግ የበላይነት ዜጎች በወንጀል ድርጊት ተጠረጠሩ ስለሚባልበት ሁኔታ፣ የተጠረጠሩ ሰዎች በሕግ ቁጥጥር ሥር እንዲቆዩ የሚወሰንበት እና ከተወሰነ በኋላም የሚያዙበት እና የሚቆዩበት፣ አንፃራዊ ፍትሕ ሊገኝ የሚችልበት ሥነ ስርዓት አለ። የወንጀል ሥነ ስርዓቱ የተበጀው እንዲህ ዓይነቱ የማን አለብኝነት ሥራ እንዳይሠራ ነው። ገዢዎቻችን ግን ካለፉት አገዛዞች ስህተት መማር የሚፈልጉ አይመስሉም። የሜሮን አፈና ከቃለ ምልልሱ እንደገመትኩት ከሆነ ሰው ጋር ይኖራት ይሆናል ብለው የጠረጠሩትን ግንኙነት ማጣራት ላይ ያተኮረ ይመስላል። የኢንተሊጀንሱን ስንፍና ነው እንግዲህ በሕገወጥ ተግባር ለመሸፈን እየተሞከረ ያለው። ይኼ የፖለቲካ ተቃናቃኞችን የማፈንና የማሰቃየት ባሕል የሆነ ቦታ ሊቆም ይገባል። አለበለዚያ ጠንቁ ለአገርም፣ ለገዢዎቹም ይተርፋል።

https://youtu.be/V1ZH9l6Zlds

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop