May 30, 2022
2 mins read

ባለሀብቶችን በማገት እና በማስፈራራት ብር በጠየቁ የሰራዊቱ አባላት ላይ ክስ ተመሠረተ

military
military
ባለሀብቶችን በመሰለል፣ በማገት እና በማስፈራራት 8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በጠየቁ እና በተቀበሉ አራት የመከላከያ ሚኒስቴር አባላት እና ግብረ-አበሮቻቸው ላይ ሥልጣንን አላግባብ በመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ስር ክስ መመሥረቱን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ክሱ የተመሠረተው የመከላከያ መኪና በመያዝ “ከጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሀብት ማስመለስ የመጣን ዐቃቤ ሕጎች ነን፤ ሕገ-ወጥ ዘይት፣ ስኳር እና የጦር መሣርያ ስለምትሸጡ በወንጀል ትፈለጋላችሁ” በማለት 8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በጠየቁ የመከላከያ ሚኒስቴር አባላት እና ግብረ-አበሮቻቸው ላይ ነው።
የተለያዩ የምርምራ ሂዶትችን ከፖሊስ ጋር ሲያከናውን ቆይቶ በግለሰቦች ላይ ክሱን የመሠረተው ደግሞ በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጄኔራል መሆኑ ተገልጿል።
ወንጀሉን ፈጽመዋል በሚል ክስ የተመሠረተባቸው በመከላከያ ሚኒስቴር በ93ኛ እና 94ኛ እግረኛ ክፍለ ጦር አባል የሆኑት 1ኛ) መቶ አለቃ ሀጂ ቱሉ߹ 2ኛ) ኦፊሰር መንግሥቱ በቀለ߹ 3ኛ) ሻምበል ካህሊ መላክ߹ 4ኛ) ሻለቃ ዱጉማ ዲምሳ እና በተለያዩ የንግድ ሥራዎች ውስጥ ተሰማርተው የሚገኙት ግብረ-አበሮቻቸው ከ5ኛ-8ኛ ስማቸው በክሱ የተጠቀሰው ተከሳሾች ሹምበዛ ፍቃዱ፣ አዲስ ዓለሙ፣ ተስፋዬ ለሚ እና አሸናፊ ወልደ ሰማያት መሆናቸውን ከፍትሕ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ችሎቱ በቁጥጥር ስር ያልዋሉትን 7ኛ እና 8ኛ ተከሳሽን ፖሊስ አፈላልጎ አንዲያቀርብ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን ተከሳሾች በተመሰረተባቸው ክስ ላይ የመጀመርያ የክስ መቃወሚያ እና ባልተያዙ ተከሳሾች ላይ የፖሊስን ምላሽ ለመጠባበቅ ለግንቦት 29/2014 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል።
ግንቦት 22/2014 (ዋልታ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Tefera Mano
Previous Story

ለጀነራል ተፈራ ማሞ ተጨማሪ የ10 ቀናት ቀጠሮ ተሰጠ

281879168 312962384358060 5362106728364363354 n
Next Story

“ፋኖ ማለት በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ የሚኖር የሀገር ባለውለታ ማለት ነው” ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop