# ቢኒያም ታደሰ እና ሳሙኤል ዲሚትሪ ተነጥለው ወደ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ተወሰዱ!
# ቀለብ ስዩም እና አስካል ደምሌ ከእስር ተለቀቁ!
ዛሬ የካቲት 26/2014 ዓ.ም የካራማራ የድል በዓልን ለማክበር በድላችን ሀውልት የተገኙት እና ለእስር የተዳረጉት የባልደራስ አባላት ምግብ እና ውሃ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ፡፡ አብዛኛዎቹ ጠዋት ቁርስ ያልበሉ ሲሆን፣ ከታሰሩ ጀምሮ ምግብና ውሃ ሊደርስላቸው አልቻሉም፡፡ ለምን እንደዚህ እንደሚያደርጉ የተጠየቁት ፖሊሶች፣ “ከላይ በመጣ ትዕዛዛ ነው” ብለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ቀለብ ስዩም እና አስካል ደምሌ ከእስር የተለቀቁ ሲሆን፣ ቀደም ብለው እስክንድር ነጋ እና ስንታየሁ ቸኮል በመለቀቃቸው፣ 37 የነበረው የታሳሪዎቹ ብዛት ወደ 33 ወርዷል፡፡ በሌላ በኩል፣ ቢኒያም ታደሰ እና ሳሙኤል ዲሚትሪ የሚባሉ የባልደራስ አባላት ከሌሎቹ እስረኞች ተነጥለው ጊዮርጊስ የሚገኘው አዲስ አበባ ፖሊስ ተወስዷል፡፡
ምንም አይነት የህግ ጥሰት ሳይፈጽሙ፣ ከህግ ውጭ የታሰሩት ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ነው፡-