የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ሰብሳቢ የሆኑት መስፍን አርአያ (ፕሮፌሰር ) መንግስት በኮሚሽኑ አሰራር ውስጥ ጣልቃ የሚገባ ከሆነ ከኃላፊነታቸው እንደሚለቁ አሳሰቡ

ዋና ሰብሳቢው መስፍን አርአያ የግል ማሳሳቢያቸውን የተናገሩት ሀገራዊ ምክክሩን ለሚመራው ኮሚሽን ሰሞኑን የተሾሙት ኮሚሽነሮች ዛሬ የካቲት 16 ቀን 2014 ዓም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመጀመሪያ የስራ ትውውቅ ፕሮግራም ባደረጉበት ወቅት እንደሆነ ምክር ቤቱ በማህበራዊ ድረ ገጹ ካሰራጨው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።

ይህንን ኃላፊነት የሰጣቸው የኢትዮጵያ ህዞብ በመሆኑ ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው በኃላፊነት መንፈስ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን የተናገሩት የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ፤ ከሚዲያውና ሌሎች አካላት ጋር በጋራ እንደሚሰሩ መናገራቸውንም ዘገባው አስረድቷል፡፡

አክለው ባደረጉት ንግግርም የአስፈፃሚው አካል ወይም የመንግሥት ጣልቃ-ገብነት እንደማይኖር እምነታቸው መሆኑን ጠቁመዋል።

ነገር ግን በኮሚሽኑ አሰራር ውስጥ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት የሚኖር ከሆነ ኃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው እንደሚለቁ ማሳሰባቸውን ምክር ቤቱ ያወጣው መረጃ ይገልጻል።

በስራ ትውውቅ ፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ኮሚሽኑ ሥራውን በገለልተኝነት በመሥራት የተሰጠውን ህዝባዊ ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ተመሳሳይ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

ፖለቲካ ከአገር በላይ ስላልሆነ ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረት የተሰጠውን ኃላፊነት ገለልተኛ በመሆን ታሪካዊ ሥራ ሰርቶ ማለፍ እንደሚገባው አፈ ጉባኤ ታገሰ ማስገንዘባቸውን መረጃው አመላክቷል።

በሀገራዊ ምክክሩ የሚሳተፉት የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደ አንድ አካል መሆናቸውን ጠቁመው፤ የምክክሩ ባለቤት ህዝቡ ስለሆነ ትክክለኛ ውሳኔ የሚጠበቀው ከህዝቡ መሆኑን አፈ ጉባኤው እንደገለጹ መረጃው ይገልጻል።

በተጨማሪም ኮሚሽኑ እቅድ አውጥቶ ወደ ሥራ እንዲገባ አስፈላጊው የሰው ኃይል፣ ቢሮ እና ግብኣቶች ሊሟሉለት ስለሚገባ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር አስፈለጊው በጀት እንደሚመደብ አፈጉባኤው ተናግረዋል።

ኮሚሽኑ ለሚያከናውነው ሀገራዊ ምክክር ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ተሞክሮዎችን በማካተት እና በሕዝቡ መካከል ብዙ የባህል ትስስሮች ስላሉ እድሉን ለሕዝቡ በመስጠት እንዲሁም በማወያየት በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ የኮሚሽኑ አባላት አበክረው እንደሚሰሩ በትውውቅ ፕሮግራሙ ወቅት መናገራቸውን የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በሲዳማ 146 ከፍተኛ አመራሮች ከሃላፊነት ተነሱ

#ሪፖርተር

2 Comments

  1. Big lie!

    He said they were elected by the Ethiopian people. When did the Ethiopian people vote to elect you? O my Gash?

    So, should we expect anything good form this kind of liar?

  2. The parliament was elected by the ethiopian people
    The same parliament selected commissioners. Therefore he was correct but your wrong. First check your facts

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share