January 28, 2022
5 mins read

አቤቱታችንን ለሚመለከተው አድርሱልን?

https://youtu.be/xjTfumFPu0Y

ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዋና ጽሕፈት ቤት:

አዲስ አበባ

ጉዳዩ: ፍትህ ስለመጠየቅ:

እንደሚታወቀው በተማሪዎች የተጀመረው አብዮት በጉልበተኛ ወታደሮች ተቀልብሶ ሀገሪቱ በርካታ ወጣቶችን አታለች::

የሚያሳዝነውና የብዙዎቻችንን ልብ  እስከ አሁን ድረስ እያደማ ያለው ጉዳይ ደግሞ በሰፊው ሕዝብ ምሬትና ጥላቻ ምክንያት ደርግ በወደቀ ማግሥት በእስርና በጫካ ውስጥ ሲንገላቱ ቆይተው ለትግል ያቁዋረጡትን ትምህርት እንደ ገና ገብተው ከጨረሱና ተመርቀው ሕዝቡን በማገልገል ላይ የነበሩትን የኢሕአፓ አባላትን እነ ታምራት ላይኔና በረከት ስሞን ከመሪያቸው መለስ ጋር በመሆን ለድርጅትዋ ከነበራቸው ፍራቻ የተነሳ ከየቦታው በማደንና በማሳፈን በርካቶችን ዳብዛቸው እንዲጠፋ ያደረጉ ሲሆን እስከ አሁን ድረስ ቁርጡን የሚነግራቸው ጠፍቶ ቤተ ሰቦቻቸው እያለቀሱ የሚገኙ መሆኑን ይህ ከዚህ በላይ በሊንኩ ላይ ያለው ቃለ መጠየቅ በቂ መረጃ ይሆናል ብለን እናምናለን:: (please click the link to watch)

ከእነዚህም መካከል:

1) አበበ ዓይነኩሉ (የደ/ማ ልጅ)
2) አለሁበል (የባሶ ሊበን ልጅ)
3) ድሉ ገበየሁ (የደጀን ልጅ)
4) ጌታቸው አበበ (የይቦቅላ ቁይ ልጅ)
5) ተሾመ ቢምረው (ምናልባት የቢቸና)
6) ወዘተ

የተባሉት ወንድሞቻችን ከአዲስ አበባ! ከባህዳርና ከሚሠሩበት መ/ቤት ታፍነው በመወሰድ ይገደሉ ወይም ይታሰሩ እስከ እሁን ድረስ ባለመታወቁ ይሄው በቃለ ምልልሱ ላይ እንደምትሰሙት (ወንድም) ቤተ ሰብ ያለቅሳል::

የሚገርመው ግን ጋይም (የኢሕአሠ መሪ የነበረው) ሳሪስ አካባቢ በድንገት ሲገሉት አለሁበል ከአደጋው አምልጦ እንደነበረና ከዚያ በሁዋላ ኮተቤ አካባቢ ከሁለት ልጃገረዶች ጋር በዲኤክስ መኪና ውስጥ እንደነበረ እንዳፈኑትና ወደ ሰባተኛ ፖሊስ ጣቢያ ከሴቶቹ ጋር እንደወሰዱትና ወዲያውኑ ታምራት ላይኔ ተደንቆ በመምጣት እንዳየውና እንደዛተበት ሁለቱ ልጃገረዶች ሲፈቱ ተናግረዋል::

ጋይም ከሞተ በሁላ ግን (የሚጠሉት የአድዋ ልጅ ቢሆንም) በዘመዶቹ አሳሳቢነት አስከሬኑ አደዋ ተወስዶ በክብር በመቀበሩ ምክንያትዘመዶቹ እርማቸውን ያወጡ ሲሆን ከዚህ በላይ ስማቸው የተጠቀሱትና የሌሎች በርካታ የኢሕአፓ አባላት ነበሩ ተብለው የተጠረጠሩ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ቤተ ሰቦች እስከ አሁን ድረስ እያለቀሱ ይገኛሉ::

ስለዚህ የእነዚህን እና የሌሎች መሰል ወገኖቻችን አያያዝና የት እንደደረሱ! በማን እንደተያዙና የት ተወስደው እንደተገደሉ (ይኖራሉ ተብሎ ጭራሽ ስለማይገመት):-

ሀ) አቶ ታምራት ላይኔ
ለ) አቶ በረከት ስሞን
ሐ) አቶ ታደሰ ጥንቅሹ
መ) በወቅቱ በተያዙበት ክልልና በሀገር ደረጃ በዚያን ጊዜ ስልጣን ላይ የነበሩ ሰዎች ተጠይቀው ትክክለኛው መረጃ ለቤተሰቦቻቸው ተነግሮ ከልቅሶ እንዲያርፉ ይደረግ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን::

ግልባጭ:

ለሰላም ሚ/ርጽ/ቤት
ለሰባዊ ኮሚሽን ጽ/ቤት
ለኢሰመጉ ጽ/ቤት
ለኢሕአፓ ጽ/ቤት
አዲስ አበባ

ለአማራ ክልል አስተዳደር ጽ/ቤት
ባህርዳር

ጉዋደኞቻቸው ከእያለንበት

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop