አጭር ቅኝት: የኦሮሙማ አፈግፍጉ ሴራ እስከ ግማሽ ነጻ መውጣትና ለድርድር እስከ መሞዳሞድ ድረስ (እውነቱ ቢሆን)

በመጀመሪያ የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ደስ ያለህ፡፤

ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከአማራና አፋር ልዩ ሀይሎችና ከፋኖ ጋር ሆኖ በጦርነቱ እየተገኙ ላሉት ድሎች ታላቅ ክብርና ምስጋና ይገባዋል፡፡ ዱሮም ቢሆንኮ እንዳይሆን ሆን ተብሎ ሴራ ተሰርቶ ነው እንጅ ወያኔ ኮረምን አልፎ ሊመጣ ፈጽሞ አይችልም ነበር፡፡ የሆነው ሆነና ነገሩ በዚህ ደረጃ እያለ ገና ወልዳያና መርሳ ነጻ ወጡ ተብሎ “የአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ሙሉ በሙሉ ነጻ ወጣ” በማለት በመንግስት ኮሙኒኬሽን ሀላፊው መነገሩ (በዚህ ቪድዮ 4፡42 ደቂቃ ላይ ያገኙታል https://www.youtube.com/watch?v=PVE9tQs7F1k) ስህተት ብቻ  ሳይሆን ሆን ተብሎና ታስቦበት በአማራው ላይ እየተሰራ ያለው ደባና ተንኮል ቅጥያ ስለሆነ አንቀበለውም፡፡

ሲሆን ሲሆን መንግስት ተብየው የኦሮሙማ ስብስብ በፓርላማው “ሽብርተኛ” ተብሎ የተሰየመውንና የአገር አውዳሚ ጠላት የሆነውን ወያኔን ከምድረ ገጽ አጥፍቶ የትግራይንም ሆነ መላው የኢትዮጵያን ህዝብ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከወያኔ ስጋት መገላገል ሲገባው የትግራይ ህዝብ በወያኔ እንደታፈነና ይባስ ብሎም የተያዙ የአማራ መሬቶች ሙሉ በሙሉ ነጻ ሳይወጡ ከወያኔ ጋር ለድርድር መሞዳመድ እጅግ አሳፋሪና ዘላቂ ዉጤት የማያመጣ ወራዳ ተግባር ነው፡፡

ሰሜን ወሎ ማለት ወልዳያና መርሳ ቆቦ ብቻ ነውን? በዚያ መስመር በወረራው ስር ያሉት ቆቦ ሮቢት፣ ቆቦ፣ ዋጃ፣ አለማጣ፣ ኮረም ….ወዘተ የትግራይ መሬቶች ናቸው ለማለት ነውን? መንግስት ተብየው “ሰሜን ወሎ ሙሉ በሙሉ ነጻ ወጥቷል” የሚለው የቱና የቱ መሬትና ህዝብ ነው ነጻ የወጣው??  በቦታው ያለው ህዝብስ ምን ይል ይሆን? መንግስት አለኝ ይል ይሆን?? ኢትዮጵያዊ ነኝ ይል ይሆን?? እንዳው በሞቴ ህዝቡ ምን ይሰማው ይሆን?? መንግስትንስ ይህ ያዋጣዋልን?? የአብይ አህመድ ኦሮሙማ መንግስት አካሄድ ሽወዳ መሆኑ ቢገባንም እኛ አማራወች ይህ የግለሰቡ አይን ያወጣ ብልጣብልጥነት አይዋጥልንምና መሞዳሞዱ መዘዝ ክማምጣቱ በፊት ተገቢው እርማት ተደርጎበት የአማራ መሬቶች ሙሉ በሙሉ ከወረራሪው የወያኔ ጦር በአስተማማኝ ሁኔታ ነጻ እስከሚወጡ ድረስ ዉጊያው መቀጠል አለበት የሚል ጽኑ አቋም ይዘናል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይድረስ ለአገር ወዳድ ወገኖቼ በያላችሁበት- ምንድነው የተፈለገው? - ከአባዊርቱ!

ይህም ማለት በወረራው የተያዙ የአማራ መሬቶች ማለትም ወያኔ “ምእራብ ትግራይ” በሚል ስም ወደ ትግራይ ያካለላቸው የጠገዴ፣ ወልቃይት፣ ማይጠምሪ፣ አዲርቀይ፣ ዳንሻ፣ መተማ፣ ማይካድራ ሁመራና ጠለምት የአማራ መሬቶች እንደዚሁም ወያኔ “ደቡብ ትግራይ” ብሎ አካልሎ እስካሁን ድረስ በወረራ የያዛቸው ቆቦ ሮቢት፣ ቆቦ፣ ዋጃ፣ ራያ ዘቦ፣ ጨርጨር፣ ሰቆጣ ኮረም፣ አለማጣ፣ ዋግ፣ ኦፍላ ሙሉ በሙሉ ነጻ እስካልወጡ ድረስ ” ነጻ ወጥተዋል” ተብሎ መነገሩ ከአንድ አገር “መንግስት ነኝ” ከሚል ሀይል የማይጠበቅ አሳፋሪ ድርጊት ነው፡፡

የአማራ ጠላቶችም ወዳጆችም ማወቅ ያለባቸው አንድ እውነታ አለ፡፤ ይሄውም አማራ ነጻነቱንና መብቱን ተገፍፎ፤ ርስቱንና መሬቱን አስወርሮ ዝም ብሎ የሚቀመጥ ህዝብ አይደለም፡፤ ሁሉም ማንነቱን ፣ ጀግንነቱን፣ ታሪኩንና ነፍጠኛነቱን ጠንቅቀው ያውቁታልና የጊዜ ጉዳይ እንጅ ጠላቶቹን በሙሉ ድባቅ መትቶ ነጻነቱን ማስጠበቅ የሚችል ህዝብ ነው፡፤ ለዚህ ምስክሩ አለም ያወቀው ደማቅና የውጭ ወራሪወችን ድባቅ የመታበት(ከመሰል ወንድም የኢትዮጵያ ጀግኖች ጋር በጋራ) የጀግንነት ታሪኩ ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ወቅትም በአይን የሚታዩ ተግባራቱና የአርበኛነት ውሎወቹ በቂ ማረጋገጫወች ናቸው፡፤የወያኔ ምርኮኞችም እጃችንን ለመከላከያ ሰራዊቱ እንጅ ለአማራ ልዩ ሀይል ወይንም ለፋኖ አንሰጥም ማለታቸው የነፍጠኛ አማራን የየዉጊያ ውሎ ምን አይነት እንደሆነ ማንም ተራ ሰው ይረዳዋል፡፡ የመንግስት ተብየው ብልሹ አካሄድ በዚህ ከቀጠለ የአማራው ህዝብ ቀጣዩ ተጋድሎ ከየት ጀምሮ እንዴት መቀጠል እንዳለበት የአማራው ዝባዊ ሀይል  ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ከውስጡ ከበቀሉ ሆዳሞች ሌላ አማራው እስካሁን የተሸነፈው “ለኢትዮጵያ ሲባል፣ ለአገር አንዲነት ሲባል” የሚሉ ማታለያወችን በጠላቶቹ ሲጋት በመቆየቱ ብቻ ነበር፡፤ አሁን ላይ ግን ጠላቶቹ ይህንኑ ቅጥፈት ሊግቱት የማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፤ አማራው አሁን ላይ እንኳን የጠላቶቹን ቅጥፈት ለመጋት ቀርቶ ውሎ ለማደር እንዳይችል አሁን ላይ የደረሰበት የመጨረሻው የህልውና አደጋ ውስጥ ስለገባ ከወደቀበት ሰመመን ነቅቶ በጀግኖቹ  ልጆቹ ማለትም ፋኖወችና ልዩ ሀይሉየጎበዝ አለቃ እንዳው በጥቅሉ በአማራ ህዝባዊ ሀይል አማካይነት ህዝቡ ነቅንቆ በቁጣ በመነሳቱ ህልውናውን ለማረጋገጥ በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ከሁሉ አስቀድሞ  የመኖር ዋስትና የነሱትን ጠላቶቹን በቁርጠኝነት በመደምሰስ በቅድሚያ ራሱን ነጻ ካወጣ  በኋላ ቀጥሎም ለሚወዳት እናት አገሩ በኢትዮጵያ አንዲነትና ጠንካራ አገርነት ከሚያምኑ መሰል ሀይሎች ጋር ጠንክሮ በጋራ ለመቆም ቆርጦ ተነስቷል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሁለቱ ሰልፎች ወግ - ሰሎሞን ጌጡ ከኑረምበርግ

የአብይ አህመድ የኦሮሙማ ተረኛ መንግስት በሁለት እግሩ ያልቆመ መንግስት ነው፡፡ በዚሁ ላይ የሚሰራው ስራ ሁሉ አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ እንዲሆን እያደረገው ነው፡፡ አማራን ለመጉዳት ብሎ “በአፈግፍጉ ፖለቲካ” እስከደብረ በርሀን ድረስ አማራው እንዲደቅቅ ያስደረገው የአብይ አህመድ መንግስት ገና ተቆፍሮ የሚወጣ ብዙ ጉድ አለበት፡፤ አሁን ለጊዜውም ቢሆን መንግስት ቆሞ ያለው ሌላ በማንም ሳይሆን በሆዳም አማራወች ትከሻ ላይ ብቻ ነው፡፡ ከአማራው ህዝብ አብራክ ወጥተውና ለሆዳቸው ተሽጠው አብይን ተሸክመው በማገልገል ላይ ባሉት በእነደመቀ መኮንን ትከሻ በአንድ እግሩ ብቻ ተንጠጥሎ የሚገኘው የአብይ አህመድ ኦሮሙማ ስብስብ ቆም ብሎ ቢያስብና ወደ እውነታው ቢመለስ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ህይወቱን ማራዘም ይችል ይሆናል፡፡ አለበለዚያ የአማራ ህዝብን እንዲህ ሜዳ ላይ አስጥቶ የስልጣኑ መረማመጃ ለማድረግ በዚሁ ከቀጠለና በዚሁ መነሾም ይህችው አንድ እግሩ ካንዳለጠችው አለቀለት ማለት ነው፡፤ ከዚያ በኋላ መነሻም መፈወሻም መንገድ የለውም፡፡

 

4 Comments

  1. TPLF is a dangerous force that has a plan to completely eliminate the Amhara race as a race and to destroy Ethiopia. Then it aims building greater Tigray on the grave of Amhara. Therefore TPLF is a cancer that must be totally removed & buried deep down.
    OROMUMA on the other hand is also a dangerous force both to the Amhara race and as well to Ethiopia. The difference between these two evil forces is that TPLF will never rest until all the Amhara race is swipped off while OROMUMA or OLF- ሼኔ እነ አብይ ያወጡለት የዳቦ ስሙ ነው is a force that aims to rule the country by oromizing the entire nation.
    Probably if these line of thought is not stopped now early, OLF can be more dangerous to the entire nation than TPLF.The solution is to get rid of both these forces and create a federalist system based on individual right that acknowledges the unity & territorial integrity of the country. So there remains a lot to fight for!!!

  2. እውነቱ አልሆነም እንጂ እውነቱ ቢሆን እንዲህ ባልዘላበድክ።
    “የአማራ ጠላቶችም ወዳጆችም ማወቅ ያለባቸው አንድ እውነታ አለ፡፤ ይሄውም አማራ … አለም ያወቀው ደማቅና የውጭ ወራሪወችን ድባቅ የመታበት (ከመሰል ወንድም የኢትዮጵያ ጀግኖች ጋር በጋራ)” አባባልህ ያስቃል።
    አማራ ጀግና ሕዝብ ለመሆኑ መካድ አይቻልም፤ ወያኔ መካድ ሞክሮ አልሆነለትም። አማራ “ከመሰል ወንድሞቹ የኢትዮጵያ ጀግኖች ጋር” ያልካት ግን ውስልትናህን ገልጦብሃል። አማራ አንድ ወገን፣ ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሌላ ወገን አደረግኸውሳ!

  3. አለም የተባልከው/የተባልሽው አስተያዬት ሰጪ ሆይ፦
    የቅኝቱ ጸሀፊ …..“ከመሰል ወንድሞቹ የኢትዮጵያ ጀግኖች ጋር በጋራ’ የሚለውን”ውዳቂ” አስተያዬት ይመለከታል፡፡
    አስተያየት ሰጪው/ዋ አንድም ጸረ አማራ ተልእኮን ያነገበ አለበለዚያም በጉዳዩ የተነካ መሆን አለበት፡፡
    አስተያየቱም ‘አማራውን አንድ ወገን ሌላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ሌላ ወገን” አደረግከው …ይህም ውስልትናህን ገልጦብሀል፣”…ዘላበድክም “የሚል ስድብም ተጨምሮበት ቀርቧል፡፡
    በመሰረቱ በቅኝቱ ላይ የቀረበው ጽሁፍ የሚያሰድብም ወገን የለየ አገላለጽም በውስጡ የለውም፡፡ በተችት አቅራቢው/ዋ እንደተገለጸው የአገሪቱን የውጭ ጠላቶች አማራው በአንድ ወገን የተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ ሌላ ወገን ሆኖ ጠላት ተመክቶ ድል ተነሳ የሚል ስድነትን አልያዘም፡፡
    ስለዚህ ለመተቸት በቅድሚያ የሀሳብ ትክክለኛነትን ማወቅና እውነትን መያዝ ያስፈልጋልና እንዳሻን መዘባረቅም አይገባም፡፡ መሳደብ ደግሞ የባለጌነት መገለጫ ነው፡፤
    ገባህ/ገባሽ አለም?

  4. እውነቱ ቢሆን ለተባለው። ሀገሪቱ በውሥጥ በቀል ባንዳ ጠላቶች እየታመሰች በውጭ ጠላቶችም እንደቀደሙ በሁለተኛ የዓለም ጦርነት ወይም በጣሊያን ወረራ ጊዜ ኢትዮጵያን ለመበታተን ብሎም አፍሪካን የተዛውሪ ቅኝ ተገዢ ለማድረግ መሬት በሚምሱበት ሰማይንም ለመቧጠጥ እየተራኮቱ በአለበት ወቅት በሀገር ውስጥ እና በውጭው ዓለም ያሉ እትዮጵያውያን በኖ ሞረ ተቃውሞ አለምን እያናወጡ ወገናቸውንም አቅም በፈቀደው ከመንግሥት ጋር በመተባበር ደፋ ቀና በሚሉበት ወቀት የአቢይ አህመድ የኦሮሙማ ተረኛ መንግሥት ጨቋኝ የአማራው ህብረተሰብ ተጨቋኝ በማድረግ አስተያየት መጻፉ የባንዳ ተላላኪነትም ከማስመዝገብ ባሻገር የከረፋ እና የሻገተ የአይምሮ ደንቆሮነትህን ማብሰርህ ነው። ወጣም ወረደ ይህ አሁን የተከሰተውን ችግረን የወለደው የጡት አባትና እናትህ የውያኔው መለስ ዜናዊ አስተዳደር እንጂ የአቢይ አህመድ ኦሮሙማ ተረኛ መንግሥት ብልህ የምትጠራው አለመሆኑን ሳትረዳው ቀርተህ ሳይሆን እንደሚባለው ከሆነ በውጭው ዓለም የሚኖሩ እነተጋሩ በሚሳተፉበት ወልፌር በሚባል የልመና ኑሮ ከሚኖሩት ባንዳዎች መካከል አንዱ በመሆንህ እንጂ፤አቢይ አህመድማ ከዓለም ሃያላን መንግሥታትና ጦር ሜዳ እየታዋጋ ነው። የአንተ ውጊያ ደግሞ የወልፊር ካርድ ቆጠራ እንዳይቀር የመሸበት የዘር ቆጠራ መዘላበድ እና ልሃጭን ማዝረብዝብ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share