1. አጠቃላይ መስፈርቶች
1.1. የኢፊዴሪ ሀገ – መንግስትን የተቀበሉ ፣
1.2. በህዝቦች ሉአላዊነትና አንድነት የሚያምኑ እና በፅናት ለማገልገል
ሙሉ ፍቃደኝነት ያላቸው ፣
1.3. ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነፃ የሆኑ ፣
1.4. በወንጀል ይሁን በፍታብሄር ተከሶ የፍርድ ቤት ክርክር የሌለባቸው፣
1.5. መከላከያ የሚያሰማራቸው የጦር ክፍሎች ሁሉ ተዘዋውረው
ለመስራት ሙሉ ፍቃደኛ የሆኑና የአካል ብቃት ያላቸው ፣
1.6. ለእግረኛ አዋጊ መኮንኖች ፣ ሻለቃ አመራርና ከዚያ በላይ ሃላፊነት
የነበራቸው፣
1.7. በየትኛውም የማዕረግ ደረጃ ላይ በየማሰልጠኛ ማዕከላት አሰልጣኝ
የነበሩ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፣
1.8. የሜካናይዝድ እና የቡድን መሳሪያ አመራርና ምድብተኛ የነበሩ ፣
1.9. የጤንነት ሁኔታን በተመለከተ
የአይን ፣ የአፍንጫ ፣ የጆሮ ፣ የጥርስ ፣ የከንፈር ፣ ችግር የሌለባቸው ፣
ከቲቢ ፣ ከሚጥል በሽታ ፣ ከስኳር ፣ ከደም ግፊት ፣ ከኪንታሮት ፣
ከእንቅርት በሽታዎች ነፃ የሆኑ እና ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የሆነ
አካላዊ ችግር የሌለባቸው ( የማያነክስ ) ፣
1.10. የትምህርት ሁኔታ ማቀድ ፣ ማሠልጠን ፣ የስልጠና ዶክሜንት
ማዘጋጀት የሚያስችል የትምህርት ዝግጅት ያለው ፣
1.11. በሚመለመልበት አካባቢ ከቀበሌ ፣ ከመስተዳድር እና ከፖሊስ
ከወንጀል ነፃ ስለመሆናቸው የፅሁፍ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፣
1.12. የቀድሞ ጦር ሠራዊት አባል ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ
የሚችሉ ፡፡
2. ዕድሜን በተመለከተ፡-
2.1. ከወታደር እስከ ከፍተኛ የበታች ሹም ያሉ ከ55 ዓመት
ያልበለጡ ፣
2.2. መስመራዊ መኮንኖች ከ60 አመት ያልበለጡ ፣
2.3. ከሻለቃ በላይ ያሉ ከፍተኛ መኮንኖች ከ64 ዓመት ያልበለጡ
መሆን አለባቸው፡፡
3. የምልመላ ቦታና ጊዜ ፡-
ለአዲስ አበባ ተመዝጋቢዎች በየክፍለ ከተማቸው ሲሆን
ለክልል ተመዝጋቢዎች በየአካባቢያችሁ ባሉ የቀበሌ ፣ የወረዳ
አስተዳደርና የፀጥታ ወይም ሚሊሻ ፅ/ቤት በአካል በመቅረብ
መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ፣
የምዝገባ ጊዜው ከህዳር 01 ቀን 2014 ዓ/ም እስከ ህዳር 15 ቀን 2014 ዓ/
ም ድረስ ይሆናል፡፡
በሁሉም የምዝገባ ጣቢያዎች ዝርዝር መስፈርቶች ተለጥፎ የሚገኙ
መሆኑን እንገልፃለን፡፡