ኢትዮጵያዊነት እና ህዝባዊነት ከወዴት ናቸዉ ?

ዕዉነት ለኢትዮጵያዊነት እና ብሄራዊ አንድነት መኖር እና ማበብ የሚያሳስበዉ ካለዉ የቀደመዉን የታሪክ ዉርስ እና የቀደሙትን ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነት እና ብሄራዊ ኩራት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉትን በህይወት የሚገኙትን ሆነ በመስዋዕትነት ያለፉትን ገድል እና ስራ ለማዉሳት እና ከታሪክ ለመማር እንሞክር፡፡

የዛሬዋን ኢትዮጵያ እና ዜጎች ሞት እና ዉርደት ላለማየት ከዘመናት አስቀድሞ ከፍተኛ መስዋዕት የከፈሉትን እያጥላላን ላለፉት  ግማሽ ክ/ዘመናት የፀረ ኅዝብ እና አንድነት ኃይሎችን  ዕኩይ እና ድብቅ ሴራቸዉን እያለባበስን  ያልሰሩትን ሰሩ የማለቱን  አድር ባይነት በቃ ማለት አለብን፡፡

ስለኢትዮጵያ  አንድነት እና የሕዝቦች ብሄራዊ ጥቅም እና ከብር በብርቱ የሰሩትን  ለምሳሌ እንደ ቀድሞዉ የኢትዮጵያ  መሪ ኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም በስልጣን ዘመናቸዉ  እንደ ነብይ የተናገሩት ዛሬ ከ40 ዓመት በፊት ከተናገሩት የጥፋት ኃይሎች ተልዕኮ ዕጥፍ  ጥፋት፣ ክህደት፣ ሞት፣ ስደት እና ዉርደት እያየን  ስለ ዕርሳቸዉ አርቆ አስተዋይነት፣ ብሄራዊ እና ህዝባዊ ስሜት  እዳንመሰክር ፤እንዳንናገር  በት.ህ.ነ.ግ.ኢህዴግ  ግዝት እና ባርነት አስተሳሰብ እንደተቀፈደድን ያሳያል፡፡

የኢትዮጵያን ዕዉነተኛ እና ታሪካዊ ጠላቶች  ለማወቅ እና ለአንዴ እና ለመጨረሻ ለመጠንቀቅ፣ ለመታጠቅ እና ለመጠበቅ  በህይወት ከሚገኙ የኢትዮጵያ መሪዎች ዉስጥ  ከኮ/ል መንግስት ኃ/ማርያም ዉጭ ማን ሊሆን ይችላል፡፡

አገር እና ህዝብ ክዶ ለዘመናት ለባዕድ እና ጠላት ህዘቡን ለባርነት እና ምድሯን፤ግዛቷን  ለግዞት አሳልፈዉ ለሰጡ የታሪክ  ዕንክረዳዶች  የግል ንብረት የሆነች አገር   ለሞቱላት  ጀግኖች የምትሆን አስከ መቸ ነዉ ፡፡

ዕኮ ዕዉነተኛ ኢትዮጵያዊነት እና ህዝባዊነት የሚሰማዉ ካለ ፡-

ት.ህ.ነ.ግ እና ግብረ አበሮች ለግማሽ ክ/ዘመናት ከትግል አስከ ዛሬ  ላደረሰዉ እና እያደረሰ ላለዉ

፩) የአገር ከህደት፣

፪) የአገር እና ህዝብ ሀብት በመዝረፍ፣

፫) በኢትዮጵያዊነት እና ማንነት መሰረት ያደረገ የአጥፍቶ ጠፊነት ተግባሩን በመረጃ በማስደገፍ ይህም በቀድሞዉ የኢትዮጵያ መንግስት  አመራር ( ኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም) …….)፣የፅሁፍ ሠነዶች፣ የምስል ማስረጃዎችን…..በማጠናከር ፡-

  • በዘር ፍጅት እና በአገር ክህደት ወንጀል (ላለፉት 50 ዓመታት) እንዲጠየቁ፣
  • የአንድ አገር ህዝብን ጠላት እና ወዳጂ  አድርጎ በመፈረጂ አንድን ህዝብ በማንነት፣ በዕምነት እና  በዕዉነት ላይ ዘመቻ በማድረግ በፖለቲካ፣ በባህል፣ በሀብት ማፍራት/ኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የጥላቻ ዘመቻ ማድረግ፣
  • የኢትዮጵያን አንድነት ለማናጋት  እና በዚህም ጠላት አዲስ አገር ምስረታ የሚሆን የመስፋፋት እና የማጥፋት ዘመቻ እና ተጠቅሶ ተጠያቂ እንዲሆን፣
  • ባለፉት የሞት እና የጥፋት ዘመናት (፳፯+፫) ከአጥፍቶ ጠፊዎች ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለተባበሩት እና ላስተባበሩት ሁሉ በግልም ሆነ በቡድን የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ እንዲይቁ፣
  • ለ ፴ ዓመት በኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም በአማራ ህብረተሰብ  ላይ ለደረሰ  ሞት ፣ፍጅት፣ ዘረፋ ፣ ስደት….. ካሳ  እንዲጠየቅ እና እንዲከፈል፣
  • ለ ፴ ዓመት በዓማራ ህዝብ ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ግዛቶች እና አስተዳደሮች  ለደረሰዉ ሠባዊ እና ቁሳዊ በደል እና መግደል ፤ማስገደል ፣በሰዉ ልጅ ላይ በማንነት እና አመለካከት ለይቶ የማጥፋት ዕልቂት (holocaust)…….የተደራጀ እና የተቀናጀ  የዓመታት  ሴራ  ሰማዕት  መታሰቢያ በብሄራዊ ደረጃ እንዲደረግ ማድረግ  ይገባል፡፡

ከዚህ ጋር በአሁኑ ጊዜ የብሄራዊ አንድነት እና የህዝብ ህልዉና ለመከላከል፣ለመጠበቅ እና ለማስጠበቅ የሚደረገዉ ታሪካዊ ተጋድሎ  የፊት ለፊት ትግል በተጨማሪ የአገር አፍራሽ  ጠላት እና የጠላት መሳሪያዎች የጥፋት ጉልበት የገንዘብ እና የቁሳቁስ ምንጭ የሆኑትን (በመንግስት ሆነ በግል ድርጅት ስም) መለየት እና መንጭነታቸዉን ማንጠፍ ያስፈልጋል፡፡

ከዚህም በላይ በኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ላይ ለዘመናት ዘመቻ ጥፋት ላካሄዱ እና ለሚያካሂዱ የሀብት እና ንብረት ምንጭ ከሆኑት ድርጅቶች ምርት ላይ በማንኛዉም መንገድ ማዕቀብ ( አለመጠቀም፣ አለመግዛት፣ አለማበረታት……) የዕዉነተኛ ኢትዮጵያዊነት አንዱ እና ዋነኛዉ የጠላት ማክሰሚያ ስልት መሆኑን መገንዘብ እና መተግበር ያስፈልጋል፡፡

በኢትዮጵያ ላለፉት ፳፯ ዓመታት  ከሰደማይ በታች በኢትዮጵያ እና በመላዉ ዓለም በኢትዮጵያ ህዝብ ስም የነበሩ እና ያሉ የእርሻ፣የንግድ፣ የአገልግሎት ፣የፖለቲካ፣ የመንግስት መዋቅር፣ የዕምነት እና ኃይማኖት ተቋማት ሳይቀሩ  ሳር ቅጠሉ በት፤ህ.ነ.ግ. እና የኢትዮጵያዊነት ጥላቻ ያዛመዳቸዉ ተባባሪ አጥፍቶ ጠፊዎች ዕዝ ስር የነበሩ እና ያሉ እንደመሆናቸዉ ያለምንም ማመንታት ወደ ህዝብ ( ብሄራዊ ) ሀብት ማዛወር ያስፈልጋል፡፡

ዕዉነተኛ ኢትዮጵያዊነት እና ህዝባዊነት የሚመጣበት ቁርጠኛ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት እንዲኖር  ለማድረግ ህዝባዊነት የሚሰማዉ አመራር እና ትዉልድ የሚመጣበትን ጊዜ መናፈቅ እና መጠየቅ  የኢትዮጵያዊነት እና ሠባዊነት ወቅታዊ  መገለጫዎች ናቸዉ ፡፡

 ይህን ዕዉነተኛ ሁነት እና ድርጊት ዛሬ ላይ ሆኖ አለመመስከር እና አለመመስከር  የምንለዉ  ዕዉነተኛ ኢትዮጵያዊነት እና ታላቅነት ከአፍ የማያልፍ ዕዉነት እና ታሪክ የማዘነፍ  ታሪካዊ ስህተት መደጋገም ነዉ ፡፡

“  አንድነት ኃይል ነዉ ”

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ ያለምንም ማስረጃ መታሰራቸውን የፖሊስ የምርመራ ሒደት እንደሚያሳይ ጠበቃቸው አሳወቁ

ማላጂ

1 Comment

  1. የገንጣይ አስገንጣዪችን ትርክት ጠንቅቀው ከተረድት መሪዎች መካከል ቀዳሚው ኮ/ መንግስቱ ሃይለማርያም ናቸው። በውስጣቸው በተሰገሰጉ የወያኔና የሻቢያ የውስጥ መስመር ታጋዪች ነገሮች እንዳልሆኑ ሆነዋል። ከጅምሩ ሻቢያና ወያኔ ቀዳሚ ጠላታቸው በማድረግ ለህዝባቸው ውሸት የጋቷቸው ” አማራ ጠላትህ ነው” በማለት ነው። ከመራራነታቸው የተነሳ የሚያውቁትን የአማርኝ ቋንቋ አናውቅም በማለት በስህተት በዚሁ ቋንቋ ሊያናግራቸው የሞክረውን የውጭና የሃገር ሰው ሁሉ ስድብና ግልምጫ ለእግዜሩ ሰላምታ የሚሰጡት ምላሽ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው። ወያኔ በአዲስ አበባ ሻቢያ በአስመራ የሃገር አለቆች ከሆኑ በህዋላ የተከተለውን ሽርክና እና መልሶ የእቃ እቃ ጫወታ ፊልሚያ ያየነውና አሁንም የምናየው ጉዳይ በመሆኑ አላወሳውም። የክፋት ጆንያው የማይነጥፍበት ወያኔ በ 27 ዓመት የአገዛዝ ዘመኑ በአማራ ላይ የፈጸመው በደል ናዚ ጀርመኒ በዘመኑ ከፈጸመው ጋር ይነጻጸራል። ይህ ዝም ብሎ በስማ በለው ወይም በወሬ የተያዘ ነገር ሳይሆን በመረጃ ያለ ጉዳይ ነው። ወያኔ ከሰው ዘር ያልተፈጠረ የድር አውሬ ነው። አሁን እንሆ በአራት ኪሎ በተፈጠረ ፍትጊያ ከስልጣን ተባሮ መቀሌ ሲመሽግ ይሆነኛል የሚለውን ሃብትና ንብረት እንዲሁም የጦር መሳሪያ ሁሉ በ27 ዓመት ግዛቱ አጠራቅሞና በጉራ ተሞልቶ ነበር። የህግ ማስከበር የተባለው ውጊያ ራሱን ሲጨፈልቀው ለውጭና ለሃገር ውስጥ ኡኡታ ያሰማው ወያኔ ሳይታሰብ ትግራይን ጥሎ የወጣውን የኢትዪጵያ ሰራዊት አባረን እንደመስሳለን በማለት የአፋርና የአማራ ህዝቦችን ለሰቆቃ እንደዳረጋቸው የዓይን ምስርክሮች ነው። በወሎና በጎንደር በአማራው ላይ የፈጸመው ግፍ ትውልድ የማይረሳው ድርቡሻዊ ድርጊት ነው። በጥይት ተደብድበው የወደቁ የቀን ከብቶችን ላየ እነዚህ አራዊቶች በፍጽም ከሰው ባህሪ ምንም ያልቀረላቸው አረመኔዎች መሆናቸውን አስረግጦ ያሳያል። እድገታችን በገጠር የሆንን ሰዎች ምን ያህል የቀንድ ከብቶችም ሆነ ሌሎች ላይ መጨከን ሆዳችን እንደማይቆርጥ ይታወቃል። ከትግራይ መሬት የወጡት እነዚህ አረመኔዎች ግን የጥፋት ተልኮ ብቻ የተቀበሉ በመሆናቸው ማውደውም ሙሉ ስራቸው በመሆኑ የጭካኔያቸውን ልክ ማወቅ ያስቸግራል። ህዝቡ እንዲራብ፤ እንዲሞት፤ እንዲበተን ሆን ተብሎ ታቅዶ የተደረገ ወረራ በመሆኑ የወያኔን ሰው በላነት ለተረዳ ጉድ ላያሰኝ ይችላል። ግን በሰውኛ ባህሪ ለቆመ ሰው አውጣኝ፤ አታድርስ፤ እግዚኦ ያስብላል።
    በቅርብ ቀን ጌታቸው ረዳ በፈረደበት በትግራይ ቲቪ ቀርቦ የሰጠውን ቃለ መጠየቅ አይደለም ዲስኩር እንጂ ላዳመጠ ወዬው አለሙ ሁሉ አብዷል ያስብላል። ነጮቹ እንደዚህ ያለውን ባህሪ “Certifiable” ይሉታል። አሁንና በፊት የሰነዘራቸውን ሃሳቦችን ረጋ ብሎ ላዳመጠና ለመዘነ ጭርቁን የጣለ እብድ እንኳን በዙሪያው ያለውን ዓለም እያየ በራሱ ይስቃል እንጂ እንደ ጌታቸው ረዳ በውሸት ተጠምቆ አይበሰብስም። የሚገርመኝ የወያኔ ቱልቱላዎች ታጋይ ጌታቸው እያሉ ሲያንቆለጳጵሱት ማንበብ እብደቱ ተላላፊ መሆኑ ያሳየናል። ህዝባዊነት፤ ኢትዮጵያዊነት ገለ መሌ የሚባለው ሁሉ ዝም ብሎ የክተት ጥሩንባ ለማይሰማ የሚነፋ እንጂ ፍሬ ነገር የለውም። ለሃገራቸው ለወገናቸው የተዋደቁት ሳይሆን ገንጣይና አስገንጣይ ነው ዛሬ በሃገሪቱ ውስጥ ጮቤ የሚረግጠው። ለዚያም ነው አበው ኢትዮጵያ ሃገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ ያሉን። ገና ድሮ ሴራውን ደርሰውበታል።
    እኔ ነብይ ወይም የነብይ ልጅ አይደለሁም። የሃገራችን ነብያቶችንም (ሴትና ወንድ) ድብ እየመታ ከሚጠነቁል የቡና ፍንጃል እንጥፍጣፊ ያንኑ አይቶ “ሩቅ መንገድ ትሄዳለህ” ከሚለው የማይሻሉ የወስላታ ጥርቅም ናቸው። ግን ወያኔ በጦር ሜዳ ሲሸነፍ አሁን ከሚሰራው የማሸበር ተግባሩ በተለዬ መንገድ፤ የእነ አልሸባብንና የአልካዲያን እንዲሁም አሁን በአፍጋኒስታን የሻሪያን ህግ ለማስፈን ከሚታገለውና ከሌሎች መሰሎች ጋር በማበር የምድሪቱን መከራ ቀጣይ እንደሚያረገው ከአሁኑ መገመት ይቻላል። የወያኔ ሪዎ ለፍርድ እስካልቀረቡ ድረስ በምንም ሂሳብ የትግራይ ህዝብም ሆነ ጎረቤቶቿ በተለይም የአማራ ህዝብ ሰላም አይኖረውም። ኢትዮጵያዊነትና ህዝባዊነት መቃብር የገቡት ወታደራዊውም መንግስት ንጉሱን ገልብጦ ሜዳውን ሁሉ እንክርዳድ ከዘራበት በህዋላ ነው። የብሄር ነጻነት ፈላጊዎቹ ይህኑ ጉዳይ ተደግፈው በአረብና በነጭ እየተደገፉ በሃገሪቱ ላይ የመከራ ዶፍ አውርደዋል ዛሬም አላባራም። ግን ልብ ላለው ቆም ብለን ብናስብ ለእነዚህ የብሄር ነጻነት ፈላጊዎች እና ባርነት አምጪዎች ድጋፍ ሲሰጡ የነበሩ ሃገራት ዛሬ ያሉበትን ሁኔታ አይቶ መፍረድ ይቻላል። ወያኔና ሻቢያን ሲረድ ከነበሩት ብዙ ሃገራት መካክል። ሱዳን፤ ግብጽ፤ ሊቢያ፤ ኢራቅ፤ ሶሪያ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሳውዲ አረቢያ እንዲሁም ነጩ አለም በአሜሪካ መሪነት እንደሆነ ታሪክ ያሳየናል። ሊቢያ፤ ኢራቅ፤ ሶሪያ ሃገር መሆናቸው ቀርቶ ተፍረክርከዋል። ሱዳን ደቡብ ሱዳን ተገንጥላባት አሁን በዳርፉር ጉዳይ ተወጥራ ተይዛለች። ባነደድት እሳት ራሳቸውም ተለብልበዋል ገናም ይለበለባሉ። የእሳቱ ቆስቋሽና ተቆስቋሽ ጊዜ ቢዘገይ እንጂ ሁሉ የእሳት ራት ይሆናሉ። በወልቃይት ህዝብ ላይ ወያኔ የፈጸመው በደል ጣሊያኖች በአምስት አመት ቆይታቸው ያልፈጸሙት ግፍ ነው። ጭራሽ ከወያኔ ጋር አብሮ መኖር አይቻልም። ወደ መልካምነት የሚለውጥ የሰውነት ክፍል የላቸውም። የሰሜን እዝ ያረድ አውሬዎች በምንም ሂሳብ ምህረት ሊደረግላቸው አይገባም። አሁን በአፋርና በአማራው ክልል ያሳዪት ጭካኔና ክፋት ከዚሁ የክፋት ጆኒያቸው የተዘገነ ነው። አማራው ራሱን ለማዳን በዘላቂ ሁኔታ ራሱን ካላዘጋጀ ማንም የውጭም ሆነ የፌዴራል ሃይል አያድነውም። ሁሉም የፓለቲካ ቁማር ተጫወች ነው። በደፋሩ ጌትነት ሽለላ ላብቃ። የሚሰማ ጀሮ ያለው ይስማ። ራስህን አድን! በቃኝ!
    ሲገሉን ስንበዛ፤ስንበዛ ሲገሉን
    ዘመን ተቆጠረ
    በጁንታው ላይ ጁንታ እየተደመረ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share