“የአሸባሪው ታጣቂዎች ትግራይ የኢትዮጵያ አይደለችም የሚሉ ጽሁፎችን በየግድግዳው ጽፈው ሄደዋል

” - ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ ጥላሁን በሰሜን ምእራብ እዝ የኮር አንድ አዛዥ

ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ ጥላሁን
ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ ጥላሁን

በጋይንት በኩል የማጥቃት እርምጃ የተወሰደባቸው የአሸባሪው ኃይሎች “ትግራይ የኢትዮጵያ አይደለችም” የሚል ጽሁፎችን በየግድግዳው ጽፈው መፈርጠጣቸውን ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ ጥላሁን ገለጹ፡፡ አሸባሪው የህዝቡን ሀብት ጨምሮ በርካታ መሠረተ ልማቶችን እንዳወደመም አስታወቁ፡፡

በሰሜን ምእራብ እዝ የኮር አንድ አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ ጥላሁን ትላንት በነፋስ መውጫ ጨጨሆ ግምባር ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ አሸባሪው በሰሜን ጎንደር በተለይም በጋይንት በኩል አድርጎ ወደ ደብረ ታቦር ለመግባት ያደረገው ሙከራ ከሽፎበት የማጥቃት እርምጃ ተወስዶበታል፡፡
ቡድኑ ባለፈባቸው አካባቢዎች ሁሉ “ትግራይ የኢትዮጵያ አይደለችም”፤ “ኢትዮጵያ የኛ አይደለችም” የሚሉ የጽሁፍ መልዕክቶችን በየግድግዳው ላይ ጽፎ መሄዱን ያስታወቁት ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ፤ ይህ ምን ያህል አገር ጠል መሆኑን ያመላከተ ነው ሲሉ አስታውቀዋል።
እንደ ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ ገለጻ፤ አሸባሪው ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች ኢትዮጵያ ጠል መሆኑን በግልጽ አሳይቷል፡፡ኢትዮጵያ የኛ አይደለችም ከሚለው መልዕክቱ ባሻገር፤ በጋሳኝ፣ በክምር ድንጋይና ነፋስ መውጫ፤ የግለሰብ ንብረት ዘርፏል፡፡የህዝቡን ሀብት ጨምሮ በርካታ መሠረተ ልማቶችን አውድሟል፡፡ ዓላማውም ማውደም ስለሆነ ጸረ መንግሥት መሆን ብቻ ሳይሆን ጸረ አገርና ጸረ ህዝብ መሆኑንም አሳይቷል፡፡
በዚህ መሠረት ሱቆችንና ድሆች የሚጠቀሙበት እለታዊ ፍጆታቸውን ሳይቀር በመዝረፍ ሰብዓዊ ቀውስ ማድረሱን የገለጹት ብርጋዴር ጀኔራል ብርሀኑ ፤ ለዚህ ምላሽ ሠራዊቱ አሸባሪውን እየቀጣ በአሁኑ ወቅትም በነፋስ መውጫ ጨጨሆ ግምባር ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡
(ኢ ፕ ድ )
ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ክልል ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ላቀ አያለው እና ባልደረቦቻቸው የተናገሩት

1 Comment

  1. No surprise guys! If the people of Ethiopia cannot create and develop a real sense of self- consciousness , take collective action and be able to move forward in a timely fashion and deal with the very propaganda of TPLF and fight a good political fight against the other faction or junta of EPRDF which controlling the Arat Kilo Palace ; all our political rhetoric and propaganda will remain just a very lousy wishful thinking !
    Yes, unless we are willing and able to critically see our own very lousy or stupid way of political thinking and make necessary corrections , blaming and condemning only TPLF or any other criminal entities such as OLF does not make any sense at all!
    We have to be patriotic enough to ask the question : who is or are controlling the palace politics ? Are they not the carriers of the deadly political virus of TPLF/EPRDF’s political system ? Are they not OLF/Oromumma ‘s guys who have already declared that they will either bring all the country under their absolute domination or have an independent Oromia ?
    It is better to try hard to get out from this very lousy if not stupid type of political mentality before it is too late !

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share