የህወሃት አሸባሪ ቡድን በሰሜን ወሎ ዞን ነዋሪዎችን ምንነቱ ያልታወቀ መርፌ ወግቷል

236391101 3010149952560797 3086562156685106336 n
236391101 3010149952560797 3086562156685106336 n

የህወሃት አሸባሪ ቡድን በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ ነዋሪዎችን ምንነቱ ያልታወቀ መርፌ ሲወጋ ማየቱን አንድ የአይን እማኝ ገለጸ።

በሀብሩ ወረዳ ቀበሌ 020 የሚኖረው ወጣት መሀመድ አንሷር እንዳለው የህወሃት አሸባሪ ቡድን በአካባቢው ሰርጎ ከገባ በኋላ የተለያዩ የግልና የህዝብ ንብረቶችን ዘርፏል።
በየደረሱባቸው አካባቢዎች ሁሉ ዘርፎ የሚፈልገውን ያክል ከጫነ በኋላ ሌላውን በማቃጠል ሲያወድም ተመለክተናል ብሏል።
ከዚህ ባለፈም “የኮቪድ 19 መከላከያ ነው” በሚል አሸባሪው ቡድን የተለያዩ ሰዎችን መርፌ ሲወጋ ተመልክቻለሁ ብሏል መሀመድ።
አሸባሪ ቡድኑ ሰዎችን የሚወጋው መርፌ እስካሁን ምን እንደሆነና ለምን ዓላማ እንደሆነ ባይታወቅም “መርፌ የተወጋ እርዳታ ያገኛል” በሚል በርካታ ሰዎችን ወግቷል ነው ያለው።
በተመሳሳይ በአፋር ክልል መርፌ ተወግቶ የእርዳታ አህል ያገኘ ጓደኛዬ አለ ሲልም መሃመድ ተናግሯል።
የአሸባሪው ህወሃት ዘራፊዎች በገቡባቸው አካባቢዎች ሁሉ ቤት ሲያቃጥሉ ንጹሃንን ሲገድሉ ማየቱንም ተናግሯል።
የአሸባሪው ቡድን ዘራፊዎች ለሰው ልጅ ምንም አይነት ርህራሄ የሌላቸው ጨካኞች መሆናቸውን በሚፈፅሟቸው ግዲያዎች ተመልክተናል ብሏል መሀመድ።
በተለያዩ አካባቢዎች የአርሶ አደሮችን ቤት በማቃጠልም በጭካኔ ንብረቶችን ሲያወድሙ ተመልክቻለሁ ሲል እማኝነቱን ገልጿል።
የአርሶ አደሮችን የቤት እንስሳቶች እየዘረፉ በማሸሽና ከባድ በደል በመፈፀም ላይ ይገኛሉም ነው ያለው።
ለትግራይ ክልል ነዋሪዎች የጥሞና ጊዜ ለመስጠት መንግስት የተናጠል ተኩስ አቁም ቢያደርግም የህወሃት አሸባሪ ቡድን ሰርጎ ገቦች በአማራ እና አፋር ክልሎች ከፍተኛ ማህበራዊ ቀውስና ውድመት እያስከተሉ ይገኛሉ።
ነሐሴ 17/2013(ኢዜአ
ተጨማሪ ያንብቡ:  መስከረም 19 ቀን 206 ዓ.ም አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በጠራው ሕዝባዊ ሠላማዊ ሠልፍ በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የተደረገ ንግግር

3 Comments

  1. ብዙ እንሰማለን። ብዙ ይወራል። ያለ መረጃ ግን ሁሉ ነገር ከንቱ ነው። ወያኔ ሰዎችን መርፌ እንደሚወጋ ከበፊትም ይታወቃል። የአማራ ሴቶች እንዲመክኑ ይህ ተደርጓል። አሁን በስዊዲን የሚኖር የወያኔ ካድሬ እስር ቤት በነበረበት ጊዜ መርፌ የተወጉ ጓደኞቹ ሲሞቱ አይቷል። ይህም በቃለ መጠይቅ በዚያው ለሚሰራጭ የአማርኛና የትግርኛ ሬዲዮ ጣቢያ የሰጠውን መረጃ መመልከት ይቻላል። አሁን እንሆ የሰርጎ ገቡ የወያኔ አሸባሪ ቡድን መርፌ ወጋቸው የተባሉ ሰዎችን በመፈለግ ደም እንዲሰጡና በላቮራቶሪ ቶሎ እንዲታይ ማረግ፤ መርፌ መወጋቱ በተፈጸመበት ስፍራ በመሄድ የተጣሉ ስሪንጆችን ወይም ሌላ ባዶም ሆኑ ፈሳሽ ያላቸው ብልቃጦችንና ሌሎችንም ነገሮች በመሰብሰብ በመረጃ መያዝ። ተወጉ የተባሉበትን ትክክለኛ ቀንና ሰአት ለይቶ ማወቅ። ከተወጉ በህዋላ በተወጊዎቹ ላይ የታዪ ምልክቶችን መዝግቦ መያዝ ተገቢ በሆነ ነበር። ግን ይህ አልሆነም። የኮሮና ክትባት ወያኔ ለአማራ ህዝብን ማታለያ እንጂ ለራሱ የሚሆንም የለውም። ግን ሁሉም ጋዜጠኛ በሆነበት በዚህ አስረሽ ምችው አለም እውነቱን ከሃሰት አንጓሎ ማቅረብ እየከበደ መቷል፡፤
    ወያኔ እኮ የራሱን ታጋዪች መርዝ አብልቶ የሚገል ድርጅት ነው። እንዴት ባለ ስሌት ነው የአማራን ህዝብ ሂሳብ አወራርዳለሁ እያለ የቫይረስ መከላከያ የሚወጋው። የማይሆን ነገር ለሚስትህ አትንገር ነው። ለወያኔ እጅን የሰጠ የአማራ ወጣት፤ ያለ ልቡ የእነርሱ መሳሪያ ይሆናል እንጂ በራሱ አስቦ እንዲኖር አይፈቀድለትም። እንደሚፈልጉ ከተገለገሉብህ በህዋላ ደግሞ እንደ እንስሳ ሜዳ ላይ በጥይት ደብድበው ይጥሉሃል። ወያኔ ሽንክ ነው። በቤ/ክርስቲያንና በመስጊድ ግቢ ውስጥ ሰው ሞቶ ልንቀበር ነው በማለት ጉድጓድ ቆፍሮ ስንት ጥይትና ጠበንጃ ቀብሮ ነው አሁን አፋር ድረስ ለመግባት የበቃው። ጅሎቹ የእኛ ሰዎች ናቸው፡፤ ወያኔን ማመን ጭራሽ አይቻልም። ሲኖ ትራክ በወታደሩ ላይ የነዳውን ወያኔን፤ ራት ጋብዞ ፌሮ እጃቸው ላይ ያስገባባቸው የወታደር መሪዎች፤ በወያኔ ተረሽነውና ራቁታቸውን ሆነው የተጨፈረባቸው ወታደሮችን ያየና የሰማ እንዴት ነው ወያኔ ይምረኛል ብሎ ከእነርሱ ጋ የሚጠጋው? አሁን ራሱ የተማረኩት ከፍተኛና ጄሌ የወያኔ ወታደሮች ራሱ አይ ምንም አናውቅም ነው የሚሉት። አይናገሩም። ያው አለቆቻችን ነው የሚያውቁት ይሉናል የሃይል መሪ ሆኖ እንኳን ምንም አላውቅም ነው የሚለን ያለ። ተንኮላቸው አጥንታቸውን ዘልቆ ገብቷል። አንዴ ወያኔ የለከፈው ሰው አይድንም። ለዛ ነው አዲስ አበባ ላይ ተቀምጠው ኢትዮጵያዊ አይደለንም በማለት የኢትዮጵያን ባንዲራ በመርገጥና በማቃጠል በውስኪ የሚራጩት። በዘረፉት ሃብት! የሴራቸው ሰንሰለት አለም አቀፋዊ ነው። ከራሳቸው በስተቀር ለሌላ ለማንም ደንታ አይሰጣቸውም። በሃገርም ሆነ በውጭ ሃገር ከቻሉ ራሳቸው፤ ካልሆነ ከፍለው ነው የሚያስገድሉት። አሁንና በፊት በአሸባሪው ኦነግና ኦነግ ሸኔ በጅምላ የተጨፈጨፉት ወገኖቻችን ሁሉ በወያኔ ስፓንሰርነት ነው። የሻሸመኔ ውድመት ከዚሁ ሃይል ጋር ተናቦ የተፈጸመ ነው።
    ባጭሩ መረጃ ማሰባሰብ ለአሁን እና ሊመጣ ላለው ትውልድ የወያኔን ሴራ ለማሳየት ይረዳል። እውነትን ተመርኩዞ፤ በፎቶ፤ በቪዲዪ፤ ከሞት የተረፉ፤ በውጊያ ላይ የነበሩ፤ መርፌ የተወጉ፤ መርዝ ያበሏቸውን፤ የተጨፈጨፉ ከብቶችን፤ የነደድ ቤቶችንና የእህል ክምሮችንና የሃይልና የመንገድ ሥራ ውድመቶችን ዶኮሜንት ማረጉ እጅግ አስፈላጊ ነው። ለምሳሌ በጋይንት አካባቢ የወያኔን ባንዲራ የተቀባ ታንክ ፎቶ አይቻለሁ። ይህ ራሱ ትልቅ መረጃ ነው። ወያኔ ራሱን እንደመንግስት ቆጥሮ በራሱ ባንዲራና ሰንደቅ እየተዋጋ እንደሆነ ያሳያል። ይህ በውጭ በተለይም በአውሮፓ፤ በአሜሪካ የሚንጫጫውን የወያኔ ደጋፊ ሃይል እውነትን በተመረኮዘ መረጃ ማሳፈር ይቻላል፡፤ ለዚያ ነው ከሱዳን ጋር ያለውን አለመግባባት ከሱዳን መሪዎች ጋር ለመፍታት ከመላፋት ይልቅ ለህዝቡ ቀጥተኛ መልዕክት ማስተላለፍ ተገቢ የሚሆነው። ህዝቡ እየተገደለም ቢሆን በመሪዎቹ ላይ ጫና ይፈጥራልና! ሱዳን በራሷ አስባ ለመኖር አይፈቀድላትም። ግብጽና አሜሪካ እያማሰሏት ያለች ሃገር ናት። እንንቃ። የጠላትን አመጣጥ እንወቅ። ስናይፕር ከያዘ ወያኔ ጋር እያቅራሩ ክላሽን ይዞ መግባት ራስን ለሞት መዳረግ ነው። የወያኔ የፓለቲካ ግቡ ይግባን። ሃገር ማፍረስ ነው። በቃኝ!

  2. TESFA,
    በጸረ ወያኔ የጥላቻና የነቀፌታ አቋምህ ልክ በአብይ አህመድ ኦሮሙማ አደገኛ ሀይል ላይ ምንም ትችት ስታቀርብ አትታይም፡፡ ቢገባህ በአሁኑ ወቅት ማለትም በዚህች ሰአት በአማራነቱ ብቻ እየተለየ ለሚጨፈጨፈው አማራም ሆነ ብሎም ለኢትዮጵያ ከወያኔ የባሰ አደገኛው ሀይል አብይ እያታለለና ስም እየቀያየረ የሚያሽሞነሙነው ተረኛው ኦነግ/ኦሮሙማ/ ነው፡፡ ወያኔንስ አንዴዉኑ ህዝቡ አንቅሮ ተፍቶታል፡፡
    ስለዚህ ተነቅቶብሀል፡፡ ህዝቡ በማይናወጥ አቋሙ ወያኔን በጠላበት ልክ አብይ አህመድ የምሚመራውን የጅቦችና አክራሪ ኦሮሙማውች ስብስብም አጥብቆ ይጠላል፡፡ ይዋጋቸዋልም፡፤ ልክ በወያኔ ላይ እንዳደረገው ሁሉ አብይ አህመድንም ከነግሳንግሱ ነቃቅሎ ይጥለዋል፡፡ ለማየት ያብቃህ፡፡
    አንተ ያን ጊዜ ምን ትል ይሆን?? ወይንስ እስካሁን ከአብይ ካምፕ የተከፈልህን ቆጥበህ ይዘሀል??

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share