February 15, 2021
2 mins read

አድዋ ይመስክር (ከአሁንገና ዓለማየሁ)

የጦር እምቢልታ ባድዋ ሲነፋ

በለው! ስትባል ወደ ፊት ግፋ!

ዳማው ፈረስህ እየደነፋ

ለዓለም ሊያውጅ ያፍሪካን ተስፋ

አንጸባረቀ የጋሻህ ጣፋ።

የጋሻህ ጣፋ ቢያጥበረብረው

ጠላት ወደቀ ራሱን አዞረው

ከፈረስ ወርደህ ገብተህ ጨበጣ

ጠላትክን ገድለህ ማርከህ ስትመጣ

የዳኘው አሽከር! ብለህ ስትፎክር

ያድዋ ተራራ ነበር ምስክር

ያድዋ ተራራ የሰሜኑ በር

የተኮፈሰው ርቆ ከድንበር

ታሪክ መዝግቧል ጠላት ሲሰበር

ጠላት ሲሰበር ሲበለሻሽ

እግሬ አውጭኝ ብሎ ነቅሎ ሲሸሽ

ማልዶ የወጣው ገና ሳይነጋ

ሽቅብ ቁልቁል ሲል ውሎ ሲዋጋ

ወገን ድል ቀንቶት ምርኮ ሲያንጋጋ

ሲሸልልና ደግሞም ሲፎክር

ያየው ተራራ አድዋ ይመስክር።

አድዋ ይመስክር ከየጠረፉ

የተጠሩና የተሰለፉ

የኢትዮጵያ ልጆች ልሳነ ብዙ

ጉንዳኖች መስለው እየተጓዙ

ባንድ ላይ ወድቀው እየተነሱ

የጠላትን ጦር እንደመለሱ።

ቅኝ ተገዝቶ እየማቀቀ

ባርነት ገብቶ ለተጨነቀ

የተስፋ ጮራ የፈነጠቀ

አድዋ ይመስክር ጀግናው ተራራ

የኢትዮጵያ አንድነት ምን እንደሠራ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የዘር ማጥፋት (Genocide) ዋነኛው መሳሪያ ዝምታና ወንጀሉን በስሙ አለመጥራት ነው!

Next Story

የሞራል ዝቅጠት እና የአድርባይነት ልክፍት ፡ ጣምራ ደዌዎቻችን! – ጠገናው ጐሹ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop