የማይካድራ ጥቃት – ከ740 በላይ ሰዎች ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ተጨፍጭፈው የተገደሉበት

በዓለም አቀፍና አገር አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ መሰረት በማይካድራ 740 በላይ ሰዎች ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ተጨፍጭፈው የተገደሉበት ዛሬ 90ኛ ቀኑ ነው። በዚች ከተማ በአብዛኛው የአማራ ተወላጆች ላይ ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም. ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ገደማ የተጀመረው ጥቃት እስከ ሌሊት ድረስ ቀጥሎ እንደነበር የዓይን እማኞችን ጠቅሰው የሰብዓዊ መብት ድርጅቶቹ ቀደም ብለው ባወጧቸው ሪፖርቶች ይፋ አድርገዋል። የዚህን ሪፖርት ጫፍ ተከትሎ ከዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ወደ 950 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደምትገኘው ማይካድራ የተጓዘው የአሜሪካ ድምፅ የሐዋሳ ዘጋቢ ዮናታን ዘብዲዮስ ተከታዩን የቪዲዮ ዘገባ አሰናድቷል።  /VOA

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአርባምንጩን የእነ እስክንድር ነጋ'ን እስር ባሰብኩ ጊዜ! ወደየት እያመራን ነን? ብለን ደግመን ደጋግሜን መጠየቅ አለብን - ዳንኤል ሽበሽ

3 Comments

  1. ኢዜማ ለምርጫው ከ140 ሚሊየን ብር በላይ በጀት መድቧል:: አቶ ይልቃል ጌትነት ከእስር ከስድስት ወራት በፊት ቢፈቱም የባንክ አካውንታቸውን መንግስት ስላገደባችው ኢዜማን ለመቀላቀል እንደሚያስቡ ተሰማ።

  2. ሩዋንዳዊ ጥንስስ
    ወልቃይት ጠገዴ ዳንሻና ሁመራ
    አርሲ ሻሸመኔ መተከል ማይካድራ
    የክልል እርግማን የአፓርታይድ አሻራ

  3. እውቁ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን እሳት ወይ አበባ በሚለው የግጥም መጽሃፉ ላይ እንዲህ ብሎ ነበር።
    እዳችን የሚያስፎክረን
    ግፋችን የሚያስከብረን
    ቅንነት የሚያሳፍረን፤ ቂማችን የሚያስደስተን
    እረ ምንድንነን|2|
    አሜኬላ እሚያብብብን፤ ፍግ እሚለመልምብን። (እሳት ወይ አበባ 1966 ገጽ 206) የሚያስገርመው ሰው ከመደንዘዙ የተነሳ ሰውን እንደ ከብት አርዶ ሰው መስሎ ለመኖር እንጀራ መቁረሱ ነው። ዛሬ በዓለም ዙሪያ የጥቁሮችን መከራ ያባባሰው ይኸው እኛው በእኛ ላይ የምናደርሰውን ጭካኔ ሌሎችም ስለሚመለከቱ ነው። ሲጀመር የሰውን ደም ያፈሰሰ ይዘገይ ይሆናል እንጂ ደሙ መፍሰሱ አይቀሬ ነው። ተንበርክኮ ለነብሱ የሚለምነውን ሰው ያለምንም ጥፋቱ አንገቱን የሚቀላ ጉድ የፈላባት የሃበሻ ምድር ከትላንት ዛሬ ይሻላል ስንል ገጣሚው ከላይ እንደሚለን በፍግ ላይ አሜኬላ የሚበቅልባት ምድር ሆናለች። የእብደታችን ልክ መለኪያ እንደሌለው ማሳያው የወያኔ በሰሜን እዝ ላይ ያደረሰው ጥቃትና ጭካኔአቸው ነው። አይ ይህማ አይነገር፤ ይቀፋል አለኝ አንድ በወያኔ ታግቶ ያየውን ለምን ሚዲያ ላይ አትናገርም ስለው። ሰው ከሴት ተወልዶ እንዲህ ያደርጋል ብለህ አታስብም ሲለኝ ብስጭት አልኩና 27 ዓመት ሙሉ አንተ የት ነበርክ? በጥይት መትተው የጣሉትን ሰው ሊያነሳ የሄደን አይደል እንዴ እዚያው ተኩሰው ይገድሉ የነበሩት? እስቲ በየሥርቻውና በየእስር ቤቱ የተሰራውን ግፍ መርምረህ ድረስበትና አየሁ ከምትለው ጋር አወዳድረው ያው ልክ ያጣ ግፍ ነው ያኔም አሁንም ያረጉት። እና በእውነት ላይ ተመርኩዞ ሁሉን ማጋለጥ አስፈላጊ ይመስለኛል ስለው አይ ለራሴም እፈራለሁ አለኝና አረፈው። በማይካድራ የተፈጸመው ድርጊት በሌሎች የሃገሪቱ ክፍል በተለይም (በኦሮሚያ ክልል) ከተፈጸመው በደል ጋር ተመሳሳይ ነው። ስንቶች ምንም በማያውቁት ጉዳይ ታርደዋል፤ ቤታቸው በእሳት ጋይቷል፤ ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው ፊታቸው ላይ ተደፍረዋል። የሚያሳዝነው የሚሻል ቀን ይመጣል ስንል የከፋ መተካቱ ነው። አሁን በመተከልና በዙሪያዋ የተፈናቀለው ህዝብ ትግራይ ውስጥ ተፈናቀለ ከሚባለው በቁጥርም ሆነ እርዳታ በመሻት ይልቃል። ግን ስለዚያ የሚያላዝን የለም። ወያኔ በገዛቸውና ከፍሎ ባሰማራቸው ደጋፊዎቹ የሚነገረን የትግራይ ሴቶች ተደፈሩ፤ ህዝቡ ተራበ፤ መድሃኒት ጠፋ፤ ወዘተ የሚሉ ነገሮች ናቸው። እውነት ነው ህዝቡ አይቸገርም ሴቶች አይደፈሩም ማለት አይቻልም። ግን ለምንድነው ሌላው ወገናችን ላይ ትኩረት ያልተሰጠው። በደቡብ/በምዕራብና በምስራቅ በግፍ ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ ከወደቁ ወራታት አልፏል። ይህ ለአንድ ከልብ አልቅሶ ለሌላው የአዞ እንባ ማፍሰስ ነው ሃገራችን አሁን ላለችበት ትርምስ የከተታት።
    የማይካድራን ጭፍጨፋ የመሩት፤ የገደሉት፤ ያቀናበሩት በአመዛኙ የሚገኙት በሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ነው። በልባቸው አውሮፓና አሜሪካ ገቢ ናቸው። የማያውቁት ግን ወያኔ ከሱዳን ጋር በመመሳጠር አሰልጥኖ አስታጥቆ እንደገና ወደ እሳት እንደሚከታቸው ነው። በእርዳታ ስም ለትግራይ ህዝብ የተቆረቆረ መስሎ የገባው የነጭና የአረብ መንጋም ተልዕኮው ሌላ ነው። ግማሹ ሰላይ ነው፤ ሌላው በህክምና ስም የመድሃኒት ጥናትና መሞከሪያ ሰው ፍለጋ ነው፤ ሌላው በትግራይ ህዝብ ስም እየለመነ የራሱን ኑሮ የሚያመቻች ቀሪው ደግሞ እርስ በእርሳችን የማያቋርጥ ግጭት ውስጥ እንድንገባ ነዳጅና እሳት የሚያቀብሉ ናቸው። ይህ የተፈተነ እውነት ነው። ለትግራይ ህዝብ ምንም አይገዳቸውም። ታዲያ እኛው በእኛው ላይ ስንደነፋ፤ ለዚህ አጭር እድሜ በወንድምና በእህታችን ደም ስንታጠብ ያው እኛ እናንቀላፋለን። እንደዚያ አይደል እንዴ አቶ አባይ ጸሃዬና አቶ መስፍን ስዪም የሆኑት። ምን ነበረ በእርጅና አርፈው ቢቀመጡ? ግን በእጅ ላይ ግፍና የሰው ደም ያለበት እረፍት የለውም። ያ በመሆኑ ነው እንደ መንፈቅ ልጅ የማይታሰብ ነገር ሞክረው የሮም አወዳደቅ የወደቁት። ግን መቼ ነው አማራ፤ ትግሬ ኦሮሞ ገለመሌ ሳንል አፍሪቃዊና አለም አቀፋዊ እይታ ኑሮን ሰው ሆነን የምንሰለፈው? አይበቃም መገዳደል? የማይካድራ ጭፍጨፋ 45 ዓመት ሙሉ ሲፈስ የኖረው የወያኔ ግፍ የመጨረሻ ማሳያ አድርገው የሚወስድ ሁሉ ሞኞች ናቸው። ወያኔ አገግሞ እንደገና ለብቀላ መነሳቱ አይቀሬ ነው፡፡ ፎክረን ስናፋክር ገድለን ስንገደል አልቅሰን ስናስለቅስ ትውልድ አልፎ ትውልድ ይተካል። ባለህበት ሂድ ይሉሃል እንዲህ ነው። የትም የማያደርስ እንቅስቃሴ። ይቅር ይበላችሁ እናንተ የዘር ፓለቲከኞች። አይሰለቻችሁም በዘራችሁ ዙሪያ እንደ ቁራ ሁሌ መጮህ? በቃኝ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share