ዓለም አቀፍ ንጉስ – በ ተፈራ ድንበሩ

እንዴት ያለ ሥልጣን የዓለም ንጉስ
በሰላምታ ምክንያት አገር የሚወርስ፡፡
ፖሊስ የማይፈራ ዳኛ የማያቀው
የማይዳሰሰው የማይታየው
ስንቱን ባለሙያ በየቤቱ አስቀረው፡፡
ምርጡ ጥበበኛ ላገር መከታው
ከምድር እስከጠፈር ተመራማሪው
ዛሬስ እያቃዠ ጉንፋን ድል ነሣው፡፡
ቅጠል በጣሽና ቀማሚም ጠይቆ
ሁሉን ተመራምሮ ሌተቀን ተራቆ
ያዳም ልጅ ተረታ ፍጡር መሆኑ ታውቆ፤
የሰው ልጅ ተጨንቆ ሰላምን ለማግኘት
ሲበር በሰማይ ሲዳክር በመሬት
ሚሳየል አልሠራ ሮኬት ሆነ ጀት
በትንፋሽ ተረታ አወይ ሰውነት፡፡
ዳርዊንና ማልተስ እንደተነበዩት
እንግዲህ መፎከር የለም ማቅራራት፤
ኮሮና ነገሠ እስኪወርድ ምህረት
ወሸባ ወሸባ እንዲየው በርቀት፡፡
ሕዝበ አሕዛብ ሁሉ ወንዱም ሆነ ሴቱ
መዘመሩ ናፍቆት በየአውደምህረቱ
ፌስቡክና ቫይቨር ጠምዶ በየፊቱ
ድምፅና ምስልን ባጀው በየቤቱ፡፡
የእግር ኳሱ ቡድን ጋጋታ የለመደው
የቅርጫት ኳስ ቡድን ዋካታ የናፈቀው
የስፖርቱ ቤተሰብ ወጣት ሽማግሌው
በመስኮት ላይ ቀረ አጀብ እያማረው፡፡
ሰው ወዳጅ ዘመዱን ሲያገኝ እንዳያቅፈው
ከንፈር ጉንጭን አይቶ ቀርቦም እንዳይስመው
እግር ፓርክ ወስዶት እንዳያዝናናው
እጅ ሥራ ሠርቶ እንዳይኖር በምንዳው
ንጉሡ ኮሮና ሁሉን ከለከለው፡፡
ያዳም ልጅ የሔዋን አይሁድ ክርስትያን
ቡድሒስቱ እስላሙ አረማውያን
መድሐኒት መጥቶለት ሁሉን የሚያድን
በውሀ መታጠብ ጠፍቶት መቀደስን
ሁሉንም ለማግኘት ተማምኖ ገንዘብን
ልብ መግዛት አጥቶ የሚያዘልቀውን
ውሀን በመዘንጋት ተሠረቀ ነፍሱን፡፡
እንደአውድማ በሬ እሚታሠር አፉ
አንዱ በሌላው ሥር አለአግባብ ማለፉ
የፈጸመው ጥፋት ተቆጥሮበት ግፉ
ሰውም ተሸበበ አወይ ዘመን ክፉ፡፡
በቅንጦት የመጣ በአስረሽ ምቺው
ሕግ እየተሻረ አያስቆጣ ምነው፤
ግን በሌላው ስህተት ተጎዳ ብዙ ሰው፡፡
ዓለም ትልቅ መስላ የማይደርሱባት
ዛሬማ አየናት ትንሽ ጎጆ ናት
በመንካት በትንፋሽ የተዳረሱባት
እንግዲህ ሰው ባየው ምርምር ውጤት
ዓለምን የሚያድን በፈዋሽነት
እውነትን ላወቀ እሱስ ነው መድሐኒት፡፡
እንግዲህ ተረኛው ምንም አይታወቅ፣
መዘንጋቱ ቀርቶ ይሻላል መጠንቀቅ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሦስቱ የሰው ዓይነቶች በጥንታዊ የግሪክ ፈላስፋዎች አገላለፅ  (ትርጉም:ዘ-ጌርሣም)

1 Comment

  1. Mayor Takele Uma is such a disciplined Mayor , all
    of the Addis Ababa city residents are lucky to have him as their Mayor .

    The Addis Ababa residents should show their gratitude to Mayor Takele Uma every chance they get so he doesn’t leave Addis Ababa , because good Mayors are hard to find and keeping good Mayors in their office is a challenge too.

    After seeing what a good job Mayor Takele Uma is doing for Addis Ababa, it is highly likely cities in the Oromia region do want him to become their Mayor after the next election is held so Addis Ababa residents need to do whatever they can to keep Mayor Takele Uma in Addis Ababa to convince him to stay in Addis Ababa without him deciding to leave Addis Ababa for another city in Oromia.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share