March 26, 2020
15 mins read

ይድረስ ለመላዉ ለኦሮሞ ነገድ – ሰመረ አለሙ

Oromo
Ethiopian women dressed in traditional Oromo costumes take part in the Irreecha celebration, the Oromo People thanksgiving ceremony in Addis Ababa, Ethiopia. October 5, 2019.REUTERS/Tiksa Negeri

ሰመረ አለሙ(semere.alemu@yahoo.com)

ወደ አንተ ወደ ወገናቸዉ ይጠብቀናል፤ ይንከባበከበናል፤ከክፉ ነገር ይከላከለናል፤ ይመግበናል ብለዉ ለትምህርት የሄዱ የኢትዮጵያ ልጆች አንተዉ ክልል እንደወጡ ቀርተዋል ክልልህንም ንጹሃንን አግቶ ቁጭ ብሏል። ቤተሰብም  ሌት ተቀን በልቅሶ ነሮዉን ይገፋል። ብታዉቀዉ ኑሮ  እነዚህ ወጣቶች ያንተ እንግዶች ነበሩ ቤተሰባቸዉን ጥለዉ አንተን አምነዉ ሲመጡ ከዚህ እምነት ጀርባ ብዙ ነገሮችን ያካተተ ነበር። የኦሮሞ ታሪክ ነዉ ብለዉ እንደሚነገሩን ቤተሰብ ላጡ አባትና እናት እንደሆንክ ነዉ የምንሰማዉ ዛሬ ግን ያየነዉ ከዛ የተለየ ነዉ። እንግዲህ ታሪክ ብለዉ የነገሩንን እንመን ወይስ ያየነዉን? በእርግጥ ላንተ አስብልሀለሁ ያሉ ዉክልና ያልሰጠኸቸዉ ባንተ ስም የሚነግዱትን እናዉቃለን አንተንም ከሌሎች ወንድሞች እሀቶችህ ለይተዉ በተለየ መንገድ እንድታታይ በረቀቀ ስልት ከህዝብ እያራቁህ እንደሆነም ይገባናል። የዚህ ሁሉ ጠንሳሾች ሁለቱ ትግሬዎችና አረቦች ቢሆኑም ይህን እንዲያስፈጽሙላቸዉ ካንተ አካባቢ በተገኙ ግለሰቦች አማካይነት የጥፋት ፐሮጀክቱን በሚገባ እየተገበሩ ነዉ። አገር ይተራመሳል፤ ሰርቶ አዳሪ አገርህ አይደለም እየተባለ ይባረራል፤ይገደላል፤ይሰቀላል፤ይደበደባል፤ይቀማል፤ይሳቀቃል ሌላም ሌላም።

እነዚህ ተንኮለኞች ታሪክ ብለዉ የሚነግሩህ እዉነት አይደለም ወንዝም አያሻግርም። እንደ እዉነቱ ከሆነ ታሪክህ ታሪካችን፤ ኑሮህ ነሯችን፤ በደልህ በደላችን ነበር፡ የተባለዉን ትርክት ተንቆ በመተዉና  ንቆ መልስ የሚሰጥበት በመጥፋቱ ጊዜ አልፎ ጊዜ ሲተካ እያደገ እየፋፋ እዉነት እየመሰለ ሄደ  ሃቁ ግን ከዚህ በተቃራኒዉ ነበር። የደካማ አስተሳሰብ ትርክት እዚህ አድርሶናል። በቅርቡ እንኳን የኔ ልጆች የምትላቸዉ ስልጣኑን ተቆጣጥረዉ ባደረሱት ጫና የኢትዮጵያ  ህዝብ ልቡ ምን ያህል  ካንተ እንደሸሸ አንተዉ ምስክር ነህ።

ሌላዉ ኢትዮጵያዊ አገሬ ብሎ ሰርቶና ነግዶ ለመኖር ወደ ከለሉህ ክልል ሲሄድ በምን አይነት መንገድ እንደሚስተናገድ ጠንቅቀህ ታዉቀዋለህ።   ያለዉን ሊሰጥና ሊቀበል የተዘጋጀዉ የህብረተ ሰብ ክፍላችን እንደራቀህ ያንን ተከትሎ ምን ያህል እንደተጎዳህም በአሀዝ የተደገፈ ማስረጃ ማቅረብ ይቻላል  አንተም ታዉቀዋለህ። አንድ ሀገር ለማደግ  ሰላምና መረጋጋት ያስፈልገዋል ሰላምና መረጋጋት ከሌለ ሰዉ መዋእለ ንዋይም ሆነ የአእምሮ ሀብቱን ለመስጠት ወደ ክልሉ አይሄደም ክልሉም የሌለዉን ከሌላ ማግኘት ካልቻለ ሀብት መፍጠር ህልም ይሆናል በዉጤቱም ስራ አጥ ተበራክቶ አካባቢዉ የወንጀለኛና የቀማኛ ማእከል ይሆናል።

ቄሮ የተባለዉ መንጋ በሀሳብና በእዉቀት የተጎዳ፤ በክፉና በደካማ ሰዎች የሚጋለብ ጫት በቃመ ቁጥር በምናቡ የሚታየዉን ለመተግበር ያ ህንጻ የኔ ነዉ ይህ ድርጅት ለኔ ነዉ የሚገባዉ አይነት አካሄድ የትም እንደማያደርስ ሳትገነዘብ የቀረህ አይመስለኝም። ዛሬ ዚምባቡዌ ዉስጥ ቅኝ ግዛት ለማድረግ የሄዱት ነጮች መሬት እየተመለሰ ነዉ። አገሩን ከጠላት ተናጥቆ ያቆየዉን ግን ስም እየሰጡ በተከለለዉ ክልል ተጠቂ ማድረግ ግን በምንም መልኩ ተቀባይነት አይኖረዉም።

ጁዋር መሀመድ የአሜሪካ ዜግነት ወስዶ ከየመን በብዙ ኪሎሜትር ርቀት በምትገኘዉ አሜሪካ ዜጋ ሁኖ አሜሪካ የምትሰጠዉን ጥቅምና ነጻነት እያጣጣመ ማሰብ የተሳናቸዉንና ቄሮ ብሎ የሾማቸዉን  ዜጎች በወንጀል ያመጣዉን ብር እየሰጠ ሰላማዊዉን ህዝብ እንዲያስጨንቁ፤እንዲዘርፉ፤እንዲገድሉ ህገ ወጥ ተግባር እንዲፈጽሙ ማድረጉ በየትኛዉም ሀገር ህግ ተቀባይነት ባይኖረዉም በኦፒዲዮ ኢትዮጵያ ግን ገድሉ እንደ ጀግንነት ተቆጥሮለት አጃቢ ተመድቦለት በግፉ ከብሮና ተፈርቶ ይኖራል።  እነ ሌንጮ፤ ዲማ ነገዎ፤ ዳዉድ ኢብሳና የነሱ ቡድን ለወያኔ በዉርደት ልጆችህን አስረክበዉ ከፈረጠጡ በሗላ  ዛሬም እናዉቅልሀለን ሲሉህ መፍቀድ አልነበረብህም። ባለፈዉ ወደ ገደል የወረወሩት ዜጋ በወንጀል ተጣርቶ ብይን እስኪሰጥበት ወዳንተ ቀርበዉ እንዲሸሸጉ ባታደርጋቸዉ መልካም ነበር። ረስተኸዉ ካልሆነ በስተቀር 25፣000 የሚገመተዉን የዳዉድና ሌንጮ ጦር  ታሪክህ እንዲበላሺ በሴት የትግሬ ወታደር ያስማረኩብህ እነዚሁ ጉዶች ነበሩ። ለመሆኑ የት ታዉቃቸዋለህ 30/40/50 አመት በዉጭ ሀገር በጡረታ ከኖሩ በሗላ ነዉ ዛሬም እናዉቅልሃለን ብለዉ የተቀላቀሉህ? በእርግጥ የመጣዉንስ ለዉጥ ያመጡት እነሱ ነበሩ?  እርግጥ ነዉ ላንተ ነዉ የቆምነዉ አንተን እየጠቀምን ነዉ የሚሉህ በስልጣን ላይ ያሉ ያልወከልካቸዉ ተወካዮችህ ተጠቅመዋል ወፍራም ደሞዝ አግኝተዋል ልጆቻቸዉን ከሀገር ዉጭ ልከዋል አገር ቤትም ዘመናዊ መስፍኖች ሁነዉ ተንቀባረዉ እየኖሩ ነዉ ያንተ ኑሮ ግን አለመቀየሩን ባይናችን ተመልክተናል።

ወደ ነገራችን ስንመለስ የእነዚህ ህጻናት መታገት እነደ ነገድ  ሊያሳፍርህ ሊያሳስብህም ይገባል ስምህንም ምን ያህል ሊያጠለሸዉ እንደሚችል መገንዘብም ይኖርብሀል። ዛሬ ህዝቡ ልጆቹን ያገተዉ ኦነግ ሸኔ ነዉ አይልም ወይም ደግሞ ኦፒዲኦ ነዉ አይልም በጥቅሉ ኦሮምያ የተባለዉ ክልል ሂደዉ እንደታገቱበት ነዉ የሚያዉቀዉ። እርግጥ ነዉ የኦነግ ወታደራዊ ክንፉ ባንክ ሲዘርፍ የፖለቲካ አመራሮቹ አብይ አህመድ ጎን ቁጭ ብለዉ ቤትና መተዳደሪያ ተሰጥቷቸዉ የሀጢያታቸዉን ፍሬ እየበሉ ነዉ በመኖራችን ብዙ አይተናል የነሱንም ነገ እናያለን ብለን እንገምታለን የማይቀርም ነዉ።

እንግዲህ የነዚህ ልጆች ስቃይና እንግልት የኦሮሞ ነገድ እንጂ የኦነግ ሸኔ ስራ ብቻ ሊሆን አይችልም ምክንያቱም ኦነግ ሸኔን እንደ ባህር የሸሸገዉ የአካባቢዉ ኦሮሞ በመሆኑ። ዉድ የኦሮሞ ነገድ ሆይ  በተመሳሳይ ሁኔታ ልጆችህ ለትምህርት አምነህ በላክኸዉ ክልል ዉስጥ ቢታገቱብህ እንደ ወላጂ ምን ይሰማሀል? በእርግጥ ኦነግ ሸኔ ከደምቢዶሎ ህዝብ የተሰወረ ነዉን? የደምቢዶሎ ህዝብስ ልጆቹን ወደ ሌላ ክልል አልላከምን? በተመሳሳይ እነዚህ ልጆች ላይ የተደረገዉ በደል ወደ ሌላ ክልል በላክሀችዉ ልጆችህ ላይ ቢደርስ በጸጋ ትቀበለዋለህን  ብለን ብንጠይቅ መልስህ ምን ይሆናል? በእርግጥ ልጆቹ በማስፈራሪያነት በመደራደሪያነት እንደ ተያዙ እንገምታልን ሆኖም እንዲህ ያለዉ አሰራር ባርባሪክ በሚባለዉ ዘመን የነበረ የሞራል ደረጃ እንጂ ዛሬ ላይ እንዲህ አይነት የትግል ስልት ሲሰራበት አይሰተዋልም ስለሆነም  ኦሮሞን በክፋቱ ሊያስቡት ለሚፈልጉ በር የሚክፈት በመሆኑ እነዚህን ልጆች የባህል መንገድህን ተጠቀምህ ነጻ አዉጣቸዉ ብለን እንማጸናለን።በነሱ በኩል የሚገኝ የፖለቲካ ኪሳራ እንጂ የፖለቲካ ትርፍ እንደማይኖርም ላጋቾቹ ማስገንዘብ እንወዳለን። ዛሬ የተማረኩ ወታደሮች    መብታቸዉ ተጠብቆ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሳይቀር እንዲጎበኙ እየተደረገ ባለንበት ዘመን ለትምህርት የሄዱ ህጻናትን አፍኖ ማሰቃየት ከምን አንጻር እንደሚታይ በጤናማ አእምሮ ማሰላሰል ይከብዳል።  ትላንት አንድ ሚሊዮን ኦሮሞ ከሱማሌ ክልል ሲባረር በጉዳዩ ተጸጽተን ሰልፍ ወጥተናል ዛሬም አላግባብ በታገቱት ህጻናት ላይ ለሚደርሰዉ ግፍና ሰቆቃ ጩኸታችን ይቀጥላል።

ህጻናትና ሴት ልጆችን ማገት እንኳን የነጻነት ታጋይ ነኝ ለሚል ድረጂት ቀርቶ ለተራ ሺፍታ፤ ቀማኛና ወንጀለኛ የሚመጥን ተግባር ባለመሆኑ ልጆቹ ተፈተዉ ወደ ቤተሰባቸዉ በክብር የሚሸኙበት ሁኔታ እንዲዘጋጅ በሰብአዊነት ስም እንጠይቃለን። ከነንጉሱ ጥላሁን ፍትህ ከምንጠይቅ ከባለቤቱ መጠየቅም አግባብነት ያለዉ አካሄድ ይመስላል።

ለማንኛዉም ጉዳዩን ለማጠቃለል ከየነገዱ የሀገር ሺማግሌዎች፤ ኑሮ  ያስተማራቸዉ አባቶች፤ ክፉዉን ከደጉ የለዩ፤  ባደረጉት አስተዋጽኦ ህብረተሰቡ  ክብር የሰጣቸዉ የኦሮሞ አባቶች በድፍረት ይህንን ነገር አዉግዘዉ ልጆቹ ተፈትተዉ ወደመጡበት እንዲመለሱ እንዲያደርጉ በዚህም ታላቅነታቸዉን እንዲያሳዩን እንጠይቃለን። የደቡብ ሺማግሌዎች ለነብሳቸዉ ሳይሳሱ ትልቅ እልቂት አስቁመዉ አይተናል ከኦሮሞ ሺማግለዎችም ተመሳሳይ ተግባር እንጠብቃለን። የነዚህ ልጆች መኖርና አለመኖር በሂሳብ አንጻር ብዙም ጉዳት ላያመጣ ይችላል ለኦሮሞ ነገድ ግን ጊዜ የማይፍቀዉ ክፉ ጠባሳ ስለሚተዉ ማንኛዉም የኦሮሞ ነገድ ይህ ተግባር ከእርሱ ጋር የተያያዘ በመሆኑ ልጆቹ ተመልሰዉ ወደመጡበት እንዲሄዱ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ እንማጸናለን። መንግስት ተብዬዉ እንዴት እንደተዋቀረና እነማን እነደሚያሸከረክሩት ስለምናዉቅ በዛ በኩል ያለዉ ነገር ተስፋ አስቆራጭ በመሆኑ መላዉ የኦሮሞ ነገድ ጉዳዩን ጉዳዬ ብሎ እነዚህ መታሰር የማይገባቸዉን ህጻናትን አስፈትቶ ከይቅርታ ጋር እንዲሸኛቸዉ ከወላጂ ጭንቀት አንጻር ጉዳዩን እንዲመለከቱት እንጠይቃለን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ሰመረ አለሙ

8 Comments

  1. Forget your crocodile tears, man! The Oromo Nation has nothing to do with this political theatre!
    Ask Abiy and his cronies, old TPLF lackeys, who actually kidnapped the students (if not out of free will) to blackmail the Oromo people. You are repeating this sinister propaganda here. Stuff it!

    • The arch enemies of Oromo People are its own ‘Intellectuals’ ,’ academicians…etc in one word its own ‘Elite ‘.
      They are incorrigible and need to be deconstructed and molded afresh . Don’t ask me how ? Very puzzling…
      በነገራችን ስለ ኦሮሞ ፖለቲከኞች ኣንድ ተቺ ሲጽፍ፣ ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎችን ከመመዝገቡ በፊት ኣባላቶቹ ከኣይምሮ በሽተኝነት ነጻ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ሴርቲፊኬት ሳያቀርቡ ሊያስተናግዳቸው ኣይገባም ያለው ትዝ ይለኛል።
      ኣፍረን፣ኣፍረን፣ ተሸማቀን ሚጢጢ ኣደረጉን ! ሰው ለራሱ ክብር ከሌለው ከከብት በምን ይሻላል??
      Abiy’s Prosperity Party is on the right track dismantling the archaic ethnic polity towards a more civil, democratic one commensurate with the current political exigencies of 21 Century .
      Thank you Semere, you raised the right issue at the right time !

      • PP is a fascist party! You, as an ardent supporter, proves this. You boldly tell us that you and your PP are ready to eradicate the Oromo people!! No one expects other than that when idiots and merciless gangsters attain state power! ይቅርታ፣ ለጡንቻ ራስ ጡንቻ ብቻ ነበር መልሱ!

  2. Hi zehabesha,
    The following comment is a response that I sent to the writer of this article at the given email address and his response. Please post it for a thought in a way readers might pick it.

    —————————————————————————–
    Mr. ሰመረ አለሙ,

    Please follow me and critically analyze my response. I do think you are miles away from the existing reality concerning Oromo Nation and its father land Oromia.

    ስለ ኦሮሞ ሕዝብ የሰማሄውን መልካም ነገርና አሁንም ያለውን የኦሮሞ ሕዝብ መልካም ሥራ ማየት፣ ማረጋገጥና መቀበል እንጠብቅብሃለን፡፡ የጠቀስከው መልካም ያልሆነ ተግባርም ተከናወነ የተባለው በኦሮሞ ምድር ላይ መሆኑም ግልጽ ነው፡፡ ግን ማን ፈጻመው?

    ኦሮሞ ምድሩን ለድንበር ዘለል ሠፋሪዎች ዕድል ሰጥቶ ያኖረና እያኖረ ያለ ታላቅ ህዝብ ነው፡፡ እነዚህ ድንበር ዘለል ሠፋሪዎች ያልኳቸው አሁን በኢትዮጵያ ሥልጣን ያሉ አብይ አህመድና ንጉሱ ጥላሁን የመሳሰሉትን እና በየዘመናቱ ከሀበሻ ቀኝ ገዥ መንግስት ሥርዓት ዋና ተዋናይነት የሚያገለግሉትን ያጠቃልላል፡፡ እነዚህ በመሰረቱ አማራ (ቅይጥ) ደም ካለውና አማርኛ ተናጋሪ ነኝ ብሎ ከሚያምን ህዝብ የመጡ ናቸው፡፡ እውኔታነቱ ላይ ብዥታ ካለ ልወቀው ምክንያቱም ሰፋ አድርጌ ማስረዳት እችላለሁና፡፡ ሀቅን ላለመካድ መዘጋጀት ግን ያስፈልጋል፡፡

    እውነት መናገር የምትሻ ሰው ከሆንክ ትግሬንም ባልወቀስክ ነበር፡፡ ህወሀትን ከሚጠሉት የመጀመርያው ነኝ ብል ማጋነን አይደለም፡፡ ቁስሉም እነሆ የሚታይ ነውና፡፡ እንደዛም ሆኖ ህወሀት (እንዲሁም ኦነግ) ትግል የጀመረው አማራ (ቅይጥ) የተባለውን ሕዝብ ስም አየጠሩ በትግራዋይ (ና በኦሮሞ) ሕዝብ ላይ በደል ባደረሱ መንግስታት መነሻነት መሆኑን ግን መካድ አይቻልም፡፡ አሁንም በኦሮሚያ ተወልዶ በአደገው (ግን ምንም ኦሮሞ ደም ያሌለው) መጤና ሠፋሪ አብይ አማካኝነት እየተጠነሰሰ ያለው ሴራ ህወሀትን (ትግሬን) ና ኦሮሞ (ኦነግ)ን ያለውዴታም ቢሆን ሊያጣምር እንደሚችል መዘንጋት አያስፈልግም እላለሁ፡፡

    እንደሚገባኝ ከሆነ አንተ ምክር ብለህ ለኦሮሞ ህዝብ ማቅርብ የሞከርከውን ተራ ፓለቲከኛ አንብቦ የሚጨርሰው አይመስለኝም፡፡ እኔም እስከ መጨረሻው ያነብኩት ተገቢ መልስ መስጠትና ማስተማርን ስለማስቀድም ብቻ ነው፡፡ የኦሮሞ ሕዝብ የሚጠቅመውንና የሚጎዳውን ለይቶ ያውቃል፡፡ የተማሩት ልጆቹንም ይሰማል፡፡ ያንተ (alien) ምክር የሚያተርፈው ጥላቻውን ማደስ ብቻ ይመስለኛል፡፡ በተለይ ደግሞ ከኦሮሞ ጥቅም ጋር የሚጻረር እያቀረብክ በሆነበት ሁኔታ፡፡ ምክንያቱም ያንተ መካሪ ሆኖ መቅረብ ተቀባይነት ያለው አመክኖ ያለው አይመስለኝም፡፡ ኦሮሞ ከቅይጥ ደም መጣጮቹ የተሻለ ከአረብና ትግራዋይ ጋር የሚቀራረብበት ብዙ ጥቅምና ጉዳይ አለው፡፡ የተማሩት የኦሮሞ ልጆች ብቻ ሳይሆኑ ያልተማረው ኦሮሞም ይህን ያውቃል፡፡ ለምስክርነት (to prove) ከፈለጋችሁ ለብቻችሁ ከመጮህ ይልቅ ረጋ በሉና ጠይቁ (ask the typical society)፣ አድምጡና ተንትኑ፡፡

    Out of your foolishness, you try to mediate Qeerroo, OLF, Jawar (sons of Oromo) and Oromo nation. How come? Isn’t it a puzzle? Or are you living in the era of Menelik, the conqueror line of Judah, and hence you think that then system might work even today? Never!

    In a nutshell, evil deeds came to Oromia following the footsteps of habesha settlers in Oromia. They are responsible for what so ever evil is in the contemporary Oromia. Hope we will soon do away with them.

    ስለዚህ ኦሮሞ በታርኩም ሆነ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የቅይጥ ተዋንያን ሥርዓት ተጠቂ እንጅ በማንም ላይ ያደረሰው በደል የለም፡፡ በታርክ አጋጣሚ የእነዚህ ለማኞች (ቅይጥ ተዋንያን) ሥርዓት ኦሮሚያን ሰብሮ ገብቶ እነርሱም ከእኛ ጋር መኖር ከጀመሩበት 150 ዓመታ አካባቢ ወዲህ ግን ኦሮሞ እንደ ሕዝብና እንደ ግለሰብ ፍዳውን እያየ ነው፡፡ እኔም ሕያው ምስክር ነኝ፡፡

    Go and ask habesha regime in Oromia who is gambling with your daughters!

    Sincerely,

    ——————————————————————————
    ኢልማ
    ትምህርት ልትሰጠኝ እስከ መጨረሻዉ ማንበብህ ጥሩ ሁኖ ሀይልና ስድብ የተቀላቀለበት ነገር መላክ አግባብ አልነበረም በአንድ አቅጣጫ ብቻ እንድታይ በሻቢያ/በወያኔ/በአረብ ተቀርጸህ ስላደግህ ካሁን በሗላ አንተን ምክንያታዊ ዉይይት ዉስጥ ተመለስ ማለት የማይቻል ነዉ።
    እንግዲህ ያነሳኸዉን ሃሳብ ነጥብ በነጠብ ከበቂ ማስረጃ ጋር ማቅረብ ቢቻልም አንተ ግን ከአንተ እምነት ዉጭ የመጣዉን ስለማትቀበለዉ ትቼዋለሁ። የማልተወዉ ግን አንተ እራስህን ኦሮሞ ነኝ ከማለተህ ዉጭ ኦሮሞነትህን በማያሻማ ሁኔታ የሚገለጽ አንድ መረጃ ብትልክልኝ ደስ ይለኛል። ለማንኛዉም ባለህበት ጤና ሁን ሳንፈልግ ኮሮና አብሮ ያኖረናል አንተ ለመቶ አመት ስታልም ጻእረ ሞት ደጃፍህ ደርሷል ለሚቀጥለዉ ምልልስ ወይ አንተ ወይ እኔ ላንኖር እንችላለን።
    ነጋቲ

  3. ” ቄሮ የተባለዉ መንጋ በሀሳብና በእዉቀት የተጎዳ፤ በክፉና በደካማ ሰዎች የሚጋለብ ጫት በቃመ ቁጥር በምናቡ የሚታየዉን ለመተግበር ያ ህንጻ የኔ ነዉ ይህ ድርጅት ለኔ ነዉ የሚገባዉ አይነት አካሄድ የትም እንደማያደርስ ሳትገነዘብ የቀረህ አይመስለኝም። ዛሬ ዚምባቡዌ ዉስጥ ቅኝ ግዛት ለማድረግ የሄዱት ነጮች መሬት እየተመለሰ ነዉ። አገሩን ከጠላት ተናጥቆ ያቆየዉን ግን ስም እየሰጡ በተከለለዉ ክልል ተጠቂ ማድረግ ግን በምንም መልኩ ተቀባይነት አይኖረዉም። ”

    ” ዛሬ ዚምባቡዌ ዉስጥ ቅኝ ግዛት ለማድረግ የሄዱት ነጮች መሬት እየተመለሰ ነዉ። ”

    ምን ይሉታል ይሄ ሁሉ………………..!!??

  4. ዘረ ያእቆብ ብለህ የጻፍከዉ ያ ማለት እንኳንስ ሀገርን ከጠላት ታናንቆ ያቆየዉን ዜጋ ቀርቶ ቅኝ ግዛት ለማድረግ የሄዱት መሬታቸዉ እየተመለሰ ነዉ ለማለት ተፈልጎ ነዉ። የተጠየቀዉ እነዚህ ልጆች ያለጥፋታቸዉ ታግተዋል ይሄን ተከትሎ የሚደርስባቸዉ የሳይኮሎጂ ጫና ለመገመት ከባድ ነዉ ንክኪያችሁን ተጠቅማችሁ አስፈቱዋቸዉ ነዉ ያልነዉ። በ21 ክፍለ ዘመን ይህን በማድረጋችሁ የምተደሰቱ ቀደም ባለዉ ጊዜ ምን ታደርጉ እንደነበረ ማሳያ ይመስለኛል አንዳችሁ እንኳን ድርጊቱን አታወግዙም እንዴ? ወደ ሌላ መሄድ አስፈላጊ አይደለም ማብረጃዉን ይስጣችሁ እራሳችሁንም አገርንም ይዛችሁ መዉረዳችሁ አይቀሬ ነዉ።በተረፈ ጊዜህን ለቁም ነገር እንጂ ወንጀለኛን ለመከላከል አታዉለዉ አንተንም ይመርዝሀል።

  5. Hier spricht die russische Seele, Putin’ም እንደ Puschkin ሌኒንግራዳዊ ነው፣ ለሰው ልጆች ራስን ማንፀባረቅያ መስተዋትን ማቅረብ ይችላሉና፣ እንሆ ሁሉም ማንነቱን ይይ፣ ዓይን ካለ ማለት ነው….!

    ” “የአፍሪካውያን ምድር መላ አውሮፓውያንን፣ አሜሪካውያንንና ኤዥያውያንን ባንድነት ይመግባል፤ ነገርግን ችግራቸው አንድና አንድ ነው፤ እርሱም “….. “፡፡
    የሩሲያውያኑ ፕሬዚደንት ቭላድሜር ፑቲን አፍሪካ በምዕራባውያኑ ላይ ያላትን ጥገኝት / ዕምነት መጣል አስመልክቶ የሰነዘሩት ድንቅ መልዕክት

    ሰሎሞን ዳውድ አራጌ
    ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ፤ እንግሊዝኛ ቋንቋና
    ስነፅሁፍ ትም/ት ክፍል መምህር

    ሪፖርተርስ ፕረስ ኤን. ጅ በተባለ ድረገፅ የወጣውን ይህን ወቅታዊና ለመላው ዓለም በተለይም ለዕኛ በዚህ እነርሱው አምጠው በወለዱት ጭንቅና መከራ መልሰን እነርሱኑ የሙጥኝ ብለን ያድኑን ዘንድ ከእነርሱ ውጭ ላሳር በምንልበት ወቅት ጆሮ ገብ መልዕክት ነው፤

    ♦ ♦ ♦ ♦
    አፍሪካ ራስ-መር ልትሆን ፈፅማ አትችልም፤ አፍሪካዉያኑ ዕምነታቸውን ከራሳቸው ይልቅ በአውሮፓውያኑ፣ አሜሪካውያኑና ቻይናውያን ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡

    ራሳቸው ፍፁም ዕምነት የላቸውም፣ አፍሪካውያን የቴክኖሎጅ ጠበብት /መሃንዲሶች በሰለጠኑባቸው ሙያዎች ላይ ልምድን ያካብቱ ዘንድ መድረኮች አይመቻቹላቸውም፤ በአንፃሩ ቻይናውያኑን መንገዶቻቸውን ይገነቡላቸው ዘንድ ይቀጥሯቸዋል፡፡

    አፍሪካ ውስጥ አንድ ነጭ ግለሰብ ወንጀል ሊፈፅም ይችላል፤ ይፈፅማልም፤ ነገርግን ምንም ዕርምጃ ሲወሰድበት አይታይም ምክኒያቱም አፍሪካውያን ባለስልጣናት /ሊቀመናብርት/ የወንበር ላይ ሊቆች እኛን (ነጮችን) ከዕውነታው ባፈነገጠ መልኩ የሚስሉን አንደ ከፊል ፈጣሪዎቻቸው አድረገው ነው፡፡ አውሮፓ ውስጥ ጥቁር ሰው ታፍኖ ሊወሰድ እንዲሁም ትንኮሳ ሊደርስበት ይችላል፤ ይባስ ብሎም ይገደላል፤ አንድም አፍሪካዊ መሪ ግን ግድ ሰጥቶት ጠይቆ አያውቅም፡፡ አፍካውያን ለራሳቸው የሚሰጡት ምስል በተለይም ከአውሮፓውያንና አሜሪካውያን ዘንድ አንዳች የውል ስምምነትን በሚያደርጉበት ግዜ እንደ አንድ ተስፋ ቢስና ደካማ ፍጡር ነው፡፡

    ራሳቸው የራሳቸው ባላንጣዎች ናቸው፡፡ ዕርስ በርስ አይዋደዱም፤ ይህም ለቅኝ ገዥ ጌቶቻቸው የሃብት ብዝባና ምዝበራ መቀጠል በር ከፋች ነው፡፡

    እኔ እስካማውቀው ድረስ አፍሪካ በፈጣሪ ዘንድ የተመረጠች ብሎም የተባረከች አሕጉር ነች፤ እናም ለአፍሪካውያን መላው አውሮፓውያን፣ አሜሪካውያንና ቻይናውያን የሚቋምጡባት፣ እነርሱን በሆን ሲሉ የሚጎመዡባት ሁናቴ ላይ መሆናቸው የሚገነዘቡበት ግዜው አሁን ነው፡፡ የአፍሪካውያንን የአየር ፀባይ ከሌላው ዘንድ አታወዳድረውም፤ የአፍሪካውያ ምድር መላ አውሮፓውያንን፣ አሜሪካውያንንና ኤዥያውያንን ባንድነት ይመግባል፤ ነገርግን ችግራቸው አንድና አንድ ነው፤ እርሱም “መሪዎቻቸው“፡፡ ጉዳዩ እንደሚያስጨንቀው አንድ ሰው የምንግዜም ምርጡ መሪያቸው ጋዳፊ ነበር፡፡

    ♦ ♦ ♦ ♦
    እንደ አንድ ዕጣ ፋንታዋ አንደሚያሳስበው፤ ለውጧን በእጅጉ እንደሚናፍቅ አፍቃሬ አፍሪካ ወይም አፍሪቃዊ ይሕ ጦማር ቧልት፣ ፌዝ ወይም መናኛ ወሬ አይደለም ነገርግን የማህበረሰባችን ከነጭ ውጭ ወደ ውጭ የሚል ያልተገባ ዕሳቤ የሚገራ ምክር ነው፤ (በቅርቡ አንኳን በባሕል ሕክምናችን ላይ የተሰነዘረው መዘባበት ገና ከአዕምሮአችን ስላልጠፋ እርሱን በሕሊናችን ሰንቀን እነርሱ አንዲት ብልቃጥ ወርውረው ለወረርሽኙ ክትባቱ ተገኘ ብለው ቢሰጡን ዕለቱን የምንሽር የሚመስለንን ቤቱ ይቁጠረን) እና ፈጣሪ ባስቀመጠን ሁኔታ /እንደፈጠረን/ እንዳንጠብቀው እንለወጥ ዘንድ፤ ሰልጥነንም የተሰጠንን ምልዑ አሕጉር ሃብቷን እንጠቀም ዘንድ ለእኛ የተላለፈ ብርቱ መልዕክት ነው፡፡

    ♦ ♦ ♦ ♦
    ምንጭ፡ Reporters press NG at http://reporterspressng.com

Leave a Reply

Your email address will not be published.

corona virus ethiopian registrar 1
Previous Story

አነጋጋሪው የኮሮና በሽታ መድሀኒትና እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎች ግድፈት – ሰርፀ ደስታ

Next Story

ግር ግር ለሌባ ያመቻል! – አገሬ አዲስ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop