May 25, 2020
1 min read

አባይ ፈላ ጉዱ – በላቸው ገላሁን

አባይ ጉዱ ፈላ አባይ ፈላ ጉዱ
ሲወርድ ሲዋረድ የሰራው ጉድጓዱ
ያ የቦረቦረው ያረሰው ሁዳዱ
ታጠረ መሄጃው ማለፊያ መንገዱ
እጁን ተሸበበ እግሮቹን ታሰረ
ጉዞውን አቆመ ረጋ! ተከተረ፤

ዝንት እድሜ ዘመኑን እንዲያ እንዳልተጓዘ
አፈር ግሳንግሱን እንዳላጓጓዘ
ጊዜ ከዳውና ጉዱ ተዝረጥርጦ
ሁሌ እንደለመደው ላይጓዝ አምልጦ
አገሩን ቀዬው ሰፈሩን ሊያበራ
ከንቱነቱ ሊቀር መሆኑ ኪሳራ
በስሚንቶ ምርጊት በደንጊያ ድርድሮሽ
እንዳይሮጥ እንዳይሄድ ወደ ግብጥ እንዳይሸሽ
ወገቡን ተያዘ እግሮቹን ታሰረ
ጉዞው ጨነገፈ ረጋ! ተገተረ፤

ጥንቱን ድሮስ ቢሆን ነው ጠፍቶ እንጅ ጎበዝ
እርካቡን የሚረግጥ ልጓሙን የሚይዝ
ተረግዞ ተወልዶ እትብቱ ካለበት
ውሎ ላይሰነብት እግሩ ወዶ ሽሽት
እንዲያ መጣደፉ ቁልቁል መሽኮልኮሉ
ጎርምሶ ሸፍቶ ካገር መኮብለሉ፤

እንግዲህ አባይ ሆይ ይቆረጥ ተስፋህ
አጉዘህ ተጉዘህ ቅብጥ* ማደርህ
መሄጃ መንገድህ ማለፊያህ ይዘጋ
እጅ እግርህም ይረፍ መንፈስህም ይርጋ።

*ጥንታዊ የግብፅ ስም ነው፡፡

ምስጋና ይሁን ለዐባይ ሳተኖች!!

በላቸው ገላሁን ሚያዝያ ፯ ፳፻፬

ፒትስበርግ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚቴ  በጀርመን መግለጫ

Next Story

የሹም ዶሮ ነን አትንኩን ባይነት ተቀባይነት የለውም! – አበጋዝ ወንድሙ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop