February 19, 2019
1 min read

ቴዎድሮስ ካሳሁንየአዲስ አበባ ሚሊኒዬም አዳራሽ ያቀረበው የሙዚቃ ትርዒት በዲቪዲ ተዘጋጅቶ የፊታችን ቅዳሜ ለሕዝብ እንደሚደርስ ታወቀ

94151

ዝነኛው ድምፃዊ፣ የዜማና ግጥም ደራሲው ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጥቅምት 14 ቀን 2011 ዓ/ም 25 ሺህ ሕዝብ በታደመመበትና በታሪካዊው የአዲስ አበባ ሚሊኒዬም አዳራሽ ያቀረበው የሙዚቃ ትርዒት በዲቪዲ ተዘጋጅቶ የፊታችን ቅዳሜ ለሕዝብ እንደሚደርስ ታወቀ::

ይህ ሲዲ ለገና በዓል ሊቀርብ የነበረ ቢሆንም በአርቲስት ጎሳዬ ተስፋዬ ጥያቄ መሰረት መራዘሙን ዘ-ሐበሻ ቀደም ሲል መዘገቡ ይታወሳል::

https://youtu.be/_Na9XUN2kfA

ቴዲ ከ16 ዓመታት የሙያ አጋሮቹ አቡጊዳ ባንድ ጋር ያቀረበው የሙዚቃ ኮንሰርት ከድምፅና ሙዚቃ ቅንብሩ እስከ መድረክ ቁጥጥሩ የተሳካና በኮንሰርቱ የታደሙትን ያረካና የተዋጣለት ቅንጅት የነበረው ታረካዊ ትርዒት እንደነበር ሲነገር የቆየ ሲሆን ይህን ታሪካዊ ዝግጅት በቦታው ተገኝተው ላልተመለከቱ፣ በዕለቱም ታድመው ለታሪክ ማስታወሻነት በከፍተኛ የድምፅና የምስል ጥራት የተቀረፀውንና የተቀነባበረውን ቪዲዮ ለሚፈልጉ ሁሉ፤ በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀው ታሪካዊ ዲቪዲ ከፊታችን ቅዳሜ የካቲት 16 ቀን ጀምሮ በገበያ ላይ እንደሚውል አሳታሚዎቹ ከላኩት መረጃ ተረድተናል::

 

Previous Story

ሕዝብ እንዲሰማህ ሰፊ አፍ ይኑርህ!

94160
Next Story

በሸዋ ሮቢት ከተማ ጎማ እየተቃጠለ ለሰአታት መንገድ ተዘግቶ ዋለ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop