በጎንደር ኮማንድ ፖስት ተቋቋመ | መከላከያ ገባ 

በምዕራብ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች የተከሰተውን ግጭት ለማርገብ የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ጥያቄ ማቅረቡ ታወቀ፡፡ በዚህ መሰረት የመከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም ለማስከበር ከዛሬ ጀምሮ ተሰማርቷል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=Fu1uIyUHtps&t=186s

በፀጥታ ኃይሉ አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ በአካባቢው የተከለከለከሉ ተግባራትም ዛሬ ይፋ ተደርገዋል፡፡ በዚህም መሠረት ከጎንደር-መተማ መስመር ከመንገድ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ አይቻልም፤ በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ ክልከላ ተደርጓል፡፡ በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሣሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ እንደማይችልም ታውቋል፡፡ ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል እርምጃ እንደሚወሰድበትና ‹‹ሰላም ለማስከበር›› በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፈቃድ ውጭ መሣሪያ ይዞ እንዳይንቀሳቀስ እገዳ ተላልፏል፡፡ የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ኃይሉ ጋር እንዲሠሩ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡ ከቀናት በፊት ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም አቶ ብርሀኑ ጁላ በጎንደር ያለውን ሁኔታ ለማረጋጋት መከላከያ ያልገባው የክልሉ መንግስት ጥያቄ ስላላቀረበ ነው ማለታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  (ሰበር ዜና) አንድ ሰው ከተገደለ በኋላ ሹፌሮች ባደረጉት አድማ ከአዲስ አበባ ጅቡቲ የሚወስደው መንገድ ከተዘጋ 3 ቀን ሆነው

4 Comments

  1. ክልሉ መጠየቅ አለበት እየተባለ በየቦታው የከፋ ችግር እንዲፈጠር ማድረግ ለሴረኞቹ ሞራል መስጠት በመሆኑ አስቀድሞ የመከላከል ስራ ቀን ለሊት መሰራት ይኖርበታል፡፡ መንግስትና አስተዳደር የሌለበት አገር መሆን የለበትም፡፡ የውጪ ጠላት ሲያንበረክክ የነበረ ህዝብ በወስጥ ባንዳ ሲጠቃ ማየት የህሊና ፀፀት አለው፡፡

    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!

  2. ክልሉ መጠየቅ አለበት እየተባለ በየቦታው የከፋ ችግር እንዲፈጠር ማድረግ ለሴረኞቹ ሞራል መስጠት በመሆኑ አስቀድሞ የመከላከል ስራ ቀን ለሊት መሰራ ይኖርበታል፡፡ መንግስትና አስተዳደር የሌለበት አገር መሆን የለበትም፡፡ የውጪ ጠላት ሲያንበረክክ የነበረ ህዝብ በወስጥ ባንዳ ሲጠቃ ማየት የህሊና ፀፀት አለው፡፡

    What did they do for more than 90,000 victims & displaced people? Who will be on side of them? These is a shame for all of us.

    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!

  3. ክልሉ መጠየቅ አለበት እየተባለ በየቦታው የከፋ ችግር እንዲፈጠር ማድረግ ለሴረኞቹ ሞራል መስጠት በመሆኑ አስቀድሞ የመከላከል ስራ ቀን ለሊት መሰራ ይኖርበታል፡፡ መንግስትና አስተዳደር የሌለበት አገር መሆን የለበትም፡፡ የውጪ ጠላት ሲያንበረክክ የነበረ ህዝብ በወስጥ ባንዳ ሲጠቃ ማየት የህሊና ፀፀት አለው፡፡

    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!

Comments are closed.

Share