February 15, 2019
2 mins read

በነአብዲ ኢሌ የክስ መዝገብ ላይ የምስክሮች ማንነት ለተከሳሶች እንዳይገለጽ ተፈቀደ

94086

ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ቀርበው የቀረበብኝ ክስ ድራማና ውሸት ነው ያሉት አብዲ ኢሌ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረብይ:: በዛሬው የችሎት ውሎ ፍርድ ቤቱ ዐቃቤ ህግ በሶማሌ ክልል የቀድሞ ርእሰ መስተዳድር  አብዲ መሀመድ የክስ መዝገብ ላይ የምስክሮች ማንነት ለተከሳሶች እንዳይገለጽ ያቀረበውን አቤቱታ ተቀበለ።

https://www.youtube.com/watch?v=bsEiZlueJBA

ክስ ከተመሰረተባቸው 47 ግለሰቦች ውስጥ ፍርድ ቤት ቀርበው ክሳቸው የተነበበላቸው አቶ አብዲ መሀመድ ዑመር፣ ራህማ መሀመድ ሀይቤ፣ አብዱራዛቅ ሰሀኔ ኢልሚና ፈርሃን ጣሂር በርከሌ ናቸው። ሌሎቹ በቱርክ ሃገር እንደጠፉና የሚፈለግጉም እንዳሉ ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም ዘግቦ ነበር::

በዛሬው ችሎት ጉሌድ ኦበል ዳውድ እና ወርሰሜ ሼህ አብዲ የፍርድ ቤቱን የስራ ቋንቋ ባለማወቃቸው ምክንያት እስካሁን ድረስ ዐቃቤ ህግ ያቀረበባቸውን ክስ እንዲረዱት አለመደረጉ የተገለጸ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ዛሬ በዋለው ችሎት የሶማሊኛ ቋንቋ አስተርጓሚ በቋሚነት እንደሚመደብ አዟል::

ከዚህ ቀደም በነበረው ችሎት ዐቃቤ ህግ በጉዳዩ ላይ ያስረዱልኛል ያላቸውን የሰው ምስክሮች ከተከሳሾች መዝገብ ጋር በማያያዝ በምስክሮች ላይ ሞራላዊ፣ አካላዊ እና የደህንነት ስጋት እንዳይደርስባቸው ጥበቃ ለማድረግ እና ህጉም የሚፈቅድ መሆኑን በማስረዳት የተከሳሾች ማንነትና አድራሻ እንዳይገለፅ በጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱ አቤቱታውን መቀበልይ ተሰምቷል:: የግራ ቀኙን ክርክር የተመለከተው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ተለዋጭ ቀጦር ለየካቲት 20 ቀን 2011 ዓ.ም  ሰጥቷል::

94083
Previous Story

የሕዝብና ቤት ቆጠራ የሚያከናውኑ ሰዎች ቆጠራ ከመጀመራቸው በፊት ሊምሉ ነው

29
Next Story

የትግራይ ልዩ ሃይል መካከል 29 የልዩ ሃይል አባላት ለመጥፋት በዝግጅት ላይ እያሉ ተይዘው በወታደራዊ እስር ቤት ገቡ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop