አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ‹‹ያገኘነው መሪ እግዚአብሄር የሰጠን ሰው ነው፣ በጣም ጥሩ ሰው አግኝተናል፡፡›› አሉ

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ታዋቂ ታጋይ የሆኑትና በፓርላማ ለአምስት አመታት ጠንካራ ጥያቄዎችን በማንሳት የሚታወቁት የ88 አመቱ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስለወቅታዊው የአገራችን ሁኔታ ተናገሩ፡፡ 

https://youtu.be/J8BZqY2t65c

አቶ ቡልቻ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የተገኘው ለውጥ የመጣው ከኢትዮጵያ ሁኔታ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ያገኘነው መሪ እግዚአብሄር የሰጠን ሰው ነው፡፡ በጣም ጥሩ ሰው አግኝተናል፡፡›› ያሉት አቶ ቡልቻ ስለዶ/ር አብይ ሲገልፁ ‹‹ኢህአዴግ ሳያውቅ ይህንን ሰው ሰጠን፡፡ እኔ ምርጫው ሲደረግ አልነበርኩም፡፡ ተወዳዳሪዎቹ ዶክተር አብይን መረጡ፡፡ እኔ የተሻለ ሰው የሚገኝ አይመስለኝም ነበር፡፡ እና ጸሎት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡›› ብለዋል፡፡ አሁን በአንዳንድ ቦታዎች በኦነግና በመንግስት መሀከል ግጭት እንዳለ መስማታቸው እንደሚያሳስባቸው ያስረዱት አቶ ቡልቻ ይህንን ጉዳይ በመሸማገል መፍታት እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ 

ከኦነግ መሪው ዳውድ ኢብሳ ጋር በአስመራ ተገናኝተው እንደነበር የተናገሩት አቶ ቡልቻ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ሲገልፁ ደግሞ ‹‹የኦነግ መሪን ዳውድ ኢብሳን አውቀዋለሁ፡፡ ከአስመራ እንደመጣ አግኝቼዋለሁ፡፡ ታረቃችሁ አይደል? ብዬ ጠየቅኩት፡፡ አዎን በደንብ ታርቀን፣ የምንሰራውንና የምናደርገውን ሁሉ ተስማምተን ነው የመጣነው ብሎ መልሶልኛል፡፡ እኔም በምላሹ ተደስቼ ነበር፡፡  አንድ ላይ መሆናችን አስደስቶኝ ነበር፡፡ ግን የእርሱ ሰዎች በወለጋ በኩል ከመንግሥት ፖሊሶች ጋር ለምን እንደሚጣሉ አይገባኝም፡፡›› ብለዋል፡፡ 

ኦነግ በወለጋ በተመሰረተበት ወቅት ተጋብዘው እንደነበር፣ ገንዘብም ተጠይቀው እንደሰጡ፣ ነገር ግን የኦሮሞ ነፃነት የሚለው ጉዳይ እንዳልጣማቸው በወቅቱ ለነበሩት አመራሮች መግለፃቸውንም አብራርተዋል፡፡ ኦሮሞ ከኢትዮጵያ ተለይቶ ሌላ አገር መሆን አለበት የሚለውን የኦነግን አቋም ተቃውመው ድርጅቱ ውስጥ ሳይገቡ መቅረታቸውንም አውስተዋል፡፡ ያለፈውን  27 ዓመታት  እንዴት ይገልጹታል? የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ቡልቻ ሲመልሱ ‹‹ በእነርሱ ዘመን ድንቁ ርና ነው የሚበዛው፡፡ ሰው አያውቅም እንጂ እነርሱ አሁንም ጉልበት አላቸው፡፡ የሰሩት በድንቁርና ነው፡፡ ሰው ሲያስሩ፣ ሲገድሉ፣ ገንዘብ ሲሰርቁ ዓይን የላቸውም፡፡ ጊዜው ያልፍና እንቀጣለን አይሉም፡፡ እኔ ፓርላማ ውስጥ አቶ መለስን ብዙ ጥያቄ ጠይቄያቸዋለሁ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዶ/ር አብይ ተፎካካሪ ፓርቲዎች 3 ወይም 4 እንዲሆኑ ጥሪ አቀረቡ

 እርሳቸው ስልጣን መጠቀምን እንጂ ሌላ ምንም የሚያስቡት ነገር የለም፡፡›› በማለት አስረድተዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይን አስተዳደር ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች እንዲናገሩ በተጠየቁበት ወቅት ደግሞ ‹‹መቼ ተጠናና፡፡ ደካማና ጠንካራ ጎንነው ብሎ ለማለት አይቻልም፡፡ ሰውዬው ጥሩ ነው ከማለት በስተቀር፡፡ ግን ሰውዬው እንዲሁ ሰው ይወደዋል፡፡ እርሱ ሲናገርም ሃሳቡ ግልጽ፣ጥሩም ነው፡፡ ገና ነው አሁን ምንም ማለት አይቻልም፡፡ ገና የድሮ ሥርዓት ወድቆ የአሁኑ አልተተካም፡፡›› ሲሉ መልሰዋል፡፡

1 Comment

  1. በሃገራችን አያሌ ወስላታ ፓለቲከኞች ብሄራቸውን ተግነው ስልፈኞች ሆነዋል እየሆኑም ነው። በመሰረቱ የጠባብ ብሄርተኞች በሽታ በዘር/በጎሳና በቋንቋ የተመሰረት እይታቸው የሻገተ መሆኑን አለመረዳታቸው ነው። አሁን እንሆ የኦሮሞን ህዝብ ከመከራ እናድናለን ኦሮሚያ የምትባል ሃገር እንገነባለን እያለ የሚለፈው ኦነግ ሃገር ከገባ በህዋላ በወለጋ ህዝባችንን እያተራመሰ መንግሥት እሆናለሁ ብሎ ማለሙ የድርጅቱን ጭፍንነት ያመላክታል። ነጻ የምታወጣውን ህዝብ አታርድም፤ ለመከራ አትዳርግም፤ ቤት ንብረቱን አታቃጥልም፤ ከቀየው አታፈናቅልም። ፓለቲካው ግን ገና ከጅምሩ የተንሻፈፈ በመሆኑ ለማንም አይበጅም። ወልጋዳ ሃሳብ ሩቅ መንገድ አይሄድም ከአሰበበትም በጊዜው አይደርስም!
    በኢትዮጵያ ምድር ዘርን ጎሳን ሃይማኖትን ቋንቋን ተገን ሳያረጉ ለዳር ድንበሯ ክብር የተሰው፤ ዛሬም የወስላቶችን አፍ ለመዝጋት የሚታገሉ የቁርጥ ቀን ልጆች ነበሯት/አሏት። ከእነዚህም መካከል አቶ ቡልቻ ደመቅሳ አድ ናቸው። በኢትዮጵያዊነታቸው የማይደራደሩ በተገኘው መድረክ ሁሉ ወያኔንና መሰሎቹን ሲሟገቱ ከኖሩ ፓለቲከኞች አንድ ናቸው። ባንጻሩ የፓለቲካ ንፋስ አቅጣጫ ሲቀይር አብረው የተቀየሩ ድሮ ያከበርናቸው ዛሬ በዘራቸው ዙሪያ የተሰለፉ እንደ አቶ በቀለ ገርባ አይነት ፓለቲከኛም አለ። በሌላ በኩል ወያኔን በየመድረኩ ሲፋለም የኖረው አንደበተ ሩቱዕና እይታ ሰፊው አቶ ልደቱ አያሌውን የጊዜው ፓለቲከኞች ጭቃ እየቀቡ የሌለ መልክ ሲሰጧቸው ማየትና መስማት ልብ ያደማል። አቶ ልደቱ ከ 60 አመታት በህዋላ ሃገራችን ካፈሯቸው ደፋርና የማያወላውል ፓለቲከኛ ቀዳሚው ናቸው። ዛሬ ሰው የሚፈረድበት በሶሻል ሚዲያ ክስ በመሆኑ ከሳሹም ፈራጅም የጅምላ ፓለቲካ በመሆኑ እሰጣ ገባ ሰሚ የለውም። ያዘው ጥለፈው የሆታ ፓለቲካ!
    ሃቀኛና ሃገር ወዳድ ፓለቲከኞች ያሉት በሃገሪቱ ልዮ ልዮ ክፍሎች እንጂ በክልል ወሰን ብቻ አይደለም። ይሁን እንጂ እንደ ሃገራችን ባለዛር ያዝ ለቀቅ የሚያረጋቸውም ሞልተዋል። ተደምረዋል ስንል የሚቀንስ ሃሳብ የሚያመነጩ፤ ተቀንሰዋል ሲባል በመደመር ሃሳብ ብቅ የሚሉ መሃል ሰፋሪዎች ናቸው። ከእነዚህም መካከል ዶ/ር ደብረጽዮን ቀዳሚ ስፍራ ይሰጣቸዋል። ዶ/ር ደብረጽዮን ባለፈው የወያኔ የገና ጫወታ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ እንደማትገነባ ጠንቅቀው ያውቃሉ። በመሆኑም የፌደራል መንግስቱን ሃሳብ ማገዝና መሞረድ ሲገባቸው በክልል ፓለቲካ ብቻ ተመርኩዘው ሃተፍ ተፍ ማለቱ አፍራሽ ተግባር እንጂ ገንቢ አይደለም። እሳቸው ብቻ አይደሉም በክልል ፓለቲካ የተተበተቡት። በአማራ ክልል (ከለለ ማለት አጠረ/የእኔ ነው አለ ማለት ነው) ቃሉን ስጠላው! በአደባባይ መባል የማይገባቸው ጸያፍ ነገሮች ሲደሰኮሩ መስማት ለጆሮ ይቀፋል። ሰላም ያለፈን በመርሳት፤ ራስን በመለወጥ የሚመጣ እንጂ ና ግጠመኝ ላሳይህ በማለት አይደለም። የክልል ፓለቲካን ወደ ጎን በመተው፤ የዜግነት ፓለቲካን መሪ በማድረግ በሆነ ባልሆነው መፋተጋችን ትተን ለአንዲትና ለተጠቃለለች ሃገር እንቁም።

Comments are closed.

Share