የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ቡድን ከወልዋሎ ጋር ላለበት ጨዋታ መቀሌ ሲደርስ ደማቅ አቀባባበል አቀባበል ተደረገለት

የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ቡድን ከወልዋሎ ጋር ላለበት ጨዋታ መቀሌ ሲደርስ ደማቅ አቀባባበል አቀባበል ተደረገለት:: 

https://youtu.be/J8BZqY2t65c

የጎንደሩ ፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ከወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ ጋር ለመጫዎት ከአንድ አመት በኅላ ነው ወደ መቀሌ  ያመራው:: ላለፈው አንድ ዓመት የአማራና የትግራይ ክልል ክለቦች የሚገናኙባቸው የፕሪምየርሊግ ጨዋታዎች በገለልተኛ ሜዳዎች ሲደረጉ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን የሁለቱ ክልሎች ክለቦች እርስ በ እርስ ር የሚገናኙባቸውን ጨዋታዎች በሜዳቸው ለማስተናገድ ፍቃደኝነታቸውን በክልሉ ባለስልጣናት በኩል ጭምር ማሳወቃቸውን ዘ-ሐበሻ ሲዘግብ ነበር::

የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ክለብ ደጋፊዎች እና የመቀሌ ነዋሪዎች እንኳን ደህና መጣችሁ በሚሉ ባነሮችን ጭምር በመያዝ የፋሲል ከነማ ቡድንን የተቀበሉት ሲሆን  ነገ እሁድ ታኅሳስ 28 ቀን 2011 09:00 የሚደረገው ጨዋታ በሰላም ተጀምሮ እንዲያልቅ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  Barcelona edges out Manchester United as highest earning team from the 2010-11 Champions League

1 Comment

  1. Peace be with my people there never been hate between people’s but corrupted,selfish ,narrow minded poleticians there blinded supporters and paid agents .

Comments are closed.

Share