November 30, 2018
4 mins read

በደቡብ ክልል 42 ሚሊዮን 284 ሺ 908 ብር ጎደለ

የደቡብ ክልል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ ተስፋዬ ታፈሰ በክልሉ 42 ሚሊዮን 284 ሺ 908 ብር ጉድለት መታየቱን ተናገሩ
አቶ ተስፋዬ ከመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት ከተካሄደባቸው መሥሪያ ቤቶች የገንዘብ አስተዳደር ሥርዓት ሕጉን የተከተሉ መሆኑን ለማረጋገጥ በተደረገው ኦዲት ስምንት መሥሪያ ቤቶች የገንዘብ አያያዛቸው ላይ ጉድለት መኖሩ መታወቁን ጠቁመው ‹‹በእነዚህ መሥሪያ ቤቶች 275 ሺ 49 ብር የጥሬ ገንዘብ ጉድለት ተገኝቷል፡፡ የክልሉ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት 155 ሺ 316 ብር፤ የክልሉ የውሃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት 67 ሺ 87 ብር በማጉደል ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡›› ብለዋል፡፡

ጨምረውም ‹‹በክልሉ የፋይናንስ አስተዳደር ሕግ መሰረት በተቋማት ያለው የገንዘብ መጠን በየወቅቱ ይቆጠራል፡፡ በቆጠራ ሪፖርትና በሂሳብ መግለጫዎች ላይ የሚሰፍረው አሃዝ እኩል መሆን አለበት፡፡ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ በሂሳብ መግለጫ ሪፖርት የተደረገውና በቆጠራ በተገኘው ገንዘብ መካከል በ59 መሥሪያ ቤቶች 42 ሚሊዮን 284 ሺ 908 ብር በማነስ ታይቷል፡፡›› ብለዋል፡፡ በ133 መሥሪያ ቤቶች ላይ በወቅቱ መወራረድ ሲገባው ያልተወራረደ 629 ሚሊዮን 982 ሺ ብር እንዳገኙ ያስረዱት ዋና ኦዲተሩ ሥራ ያልተሠራበትም ካለ ተለይቶ ወደ መንግሥት ካዝና መመለስ የነበረበትና ሥራ ተሠርቶም ከሆነ መረጃዎች ቀርበው መወራረድ የነበረባቸው ቢሆንም ምንም ሰነድ እንዳልተገኘ ጠቁመዋል፡፡ ‹‹ኦዲት በምናደርግበት ጊዜ በ137 መሥሪያ ቤቶች 128 ሚሊዮን ብር ማስረጃ ሳይቀርብ፣ የተሟላ ማስረጃ ሳይኖርና ህጋዊ ባልሆነ ማስረጃ ተወራርዶ እንዲሁም ተመዝግቦ ተገኝቷል፡፡›› ያሉት አቶ ተስፋዬ ይህ በመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች መሰረት ያልተፈፀመ በመሆኑ ሕጋዊ ያልሆነ ሥራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ወደ 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር፣ ፖሊስ ኮሚሽን 9 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር፣ የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽሕፈት ቤት 8 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር እንዲሁም የሲዳማ ዞን ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ማስረጃ ሳይቀርብ፣ የተሟላ ማስረጃ ሳይኖርና ህጋዊ ባልሆነ ማስረጃ የወጪ ሂሳብ አወራርደው ከተገኙት መሥሪያ ቤቶች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ኦዲተሩ ተናግረው በመጨረሻም ‹‹በሕጉ መሰረት ያልተሟላ ማስረጃ ሳይኖር ሂሳብ አወራርዶ መገኘት ያስጠይቃል፡፡ እኛም በላክነው ሪፖርት ይህን የፈፀሙ አካላት በሕግ መጠየቅ እንዳለባቸው አሳውቀናል፡፡›› ብለዋል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=cKOwRaexXZ4&t=4s

1 Comment

  1. The press conference with embassy official diplomats and their goons in Washington DC is a theatre.The fake so called Ethiopian diaspora thrust fund with no thrustee , with no thrust deed and no set beneficiary calls itself diaspora thrust fund while holding events in the Woyane controlled diplomats embassy.

    Girma Birru’s mansion now the other ambassador’s residence in DC is costing us more , his bodyguards at his holiday parties cost us also the GERD bond cost us all for nothing but for buying bullets for EPRDF woyane and their goons.
    Why isn’t the Ambassador calling another teleconference like he did when he first got appointed ambassador’s to USA.
    Why don’t the council and ambassador call a big teleconference and see if diaspora acknowledges these self appointed ambassador’s and advisors council’s talk?I advise diasporas to demand justice ,the embassy should investigate Abay Tsehaye and Mohammed Amoudi’s joint international bank accounts first .

    http://ethioforum.org/press-conference-ethiopian-diaspora-trust-fund-advisory-council/

Comments are closed.

92828
Previous Story

በምዕራብ ወለጋ የተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተካሄዱ

92834
Next Story

ኦምሃጅር ከተማ ቀን እየወጣላት ነው

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop