ስለ ቂሊጦ ዝም አልልም! ከ ሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት »

ስለ ቂሊጦ ዝም አልልም!
==============
በቂሊጦ እስር ቤት በርካታ ወንድሞቻችን በጸረ ሽብር አዋጁ ተገን በኦነግ ስም ታስረው መከራቸውን እያዩ ነው፡፡ አሁን በቅርቡ የምግብ ማቆም አድማ አድርገው የነበሩት እነዚህ ወንድሞቻችን የርሃብ አድማ ሲያደርጉ የመጣላቸው ሀኪም አይደለም፡፡ ልዩ ሀይል የሆነ ወታደር ነው እንጂ… ልብ በሉልኝ፤ በርሃብ ለደከመ ሰውነት ገራፊ ወታደር!!!

ይሄ አይነቱን ጭካኔ ሰይጣን እንኳን አድርገው ቢባል “አረ ፈጣሪ ምን ይለኛል” ብሎ መፍራቱ አይቀርም፡፡ ፈጣሪን መፍራት የተሳናቸው ሰዎቻችን ግን በድፍረት እንዲህ ጨከኑ…

በብረት ክርችም ካሰሩ በኋላ በርሃብ የደከሙ ሰዎችን መደብደብ ጀግና ያስብል ይሆን…! ወይስ “ጀግንነቱን ቀድመን ተብለናል እስቲ ደግሞ በእርኩሰት ሳጥናኤልን አንብለጠው” ብለው እየተወዳደሩ ነው…! ግራ ገብቷቸው ግራ አጋቡንኮ…

እንደሰማነው ገድል ከሆነ… (መሆኑን ግን አንጃ…) ህውሃት ያኔ ጫካ እያለች የሚታኮሷትን ወታደሮች የያዘቻቸው እንደሆነ እንክብካቤዋ በጦርነት ሳይሆን በፍቅር የማረከች ነበር የምትመስለው ብለው ድርሳን ፀሀፊቿ እና ኢቲቪዋ ነገሮናል፡፡

ታድያ ያኔ ሲታኮሷት የነበሩ ሰዎችን ስትንከባከብ የነበረች ድርጅት ዛሬ ከትምህርት ቤት እና ከሰላማዊ መስሪያ ቤት የሰበሰበቻቸው ሰዎች ላይ እንዲህ መሆኗ … አብዳ ነው ተናዳ….!?

“እስቲ ጠይቁልኝ ይቺን ሰው በሰው…

አያያዟ ሁሉ እንደማሆን ነው… ”

(እስቲ ተቀበል…)

እውነቱን ለመናገር ይሄ መካሪ ማጣት ነው፡፡ በዚህ ርግጫ መሰል ርምጃ፤ በእስር ላይ ያሉትን ፀጥ ማሰኘት ይቻል ይሆናል፡፡ በውጪ ያሉትን ግን ያበረታል፡፡ የበረቱት ሲታሰሩ ደግሞ ሌሎች ይበረታሉ፡፡ እነርሱም ሲታሰሩ ሌሎች ይበረታሉ… ያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ… ከተረሳ የህዳሴው ዋዜማ የሚለውን ቪዲዮ ድጋሚ መመልከቱ ሳይበጅ አይቀርም…!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዋስትናችን እርቅ ብቻ ነው!

ለማንኛውም በቂሊጦ የሚገኙ ወንድሞቻችን እየደረሰባቸው ላለው ስቃ የህዝ ለህ እያሉ ነው…! እኔ ስለ እነርሱ ዝም አልልም…. ኪቦርድ ያለህ በኪቦርድህ ድምጽ ለህ በድምፅህ አግዘኝ…. ስለ ወንድሞቼ እጮሃለሁ…!

ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ….!!!

https://www.facebook.com/MillionsOfVoicesForFreedomUdj

Share