የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ከዩቲዩብ (Youtube) ተባረረ

July 23, 2013

(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በዩቱዩብ የተለያየ ፕሮፓጋንዳዎቹን የሚያስተላልፍበት የዩቲብ ቻናል ተዘጋ። ዩቲዩብ ኢትዮጵያ ቴሌቭዥንን ማባረሩን የገለጸበት መልዕክት “YouTube account ethiopiantv has been terminated because we received multiple third-party notifications of copyright infringement from claimants including: David Tesema” ይላል።
ከዚህ ቀደም በቴሌቭዥን ጣቢያው የአፍሪካ ዋንጫን ሰርቆ በማስተላለፍ የሃገሪቱን ስም አንገት ያስደፋው የኢትዮጵያ ቲሌቭዥን አሁንም ከዩቲዩብ የተባረረው በተደጋጋሚ በኮፒ ራይት ሲመከርና ማስጠንቀቂያ ሲሰጠው አልሰማ በማለቱና ከድርጊቱም ባለመቆጠቡ እንደሆነ የዩቲብ አሰራር ያመለክታል።
ኢቲቪ ለዘፋኞች 5 ሳንቲም ክፍያ ሳይከፍል ሥራዎቻቸውን በሕብረትርዒት ላይ እንደሚያቀርብ፤ የውጭ ሃገር ፊልሞችንም ምንም ክፍያ ሳይፈጽም በታላቅ ፊልም ላይ እንደሚያሳይ የሚታወቅ ሲሆን ይህን ስርቆቱን በመቀጠል ዩቲዩብ ላይ ገንዘብ ለማካበትና ፕሮፓጋንዳውን ለማስተላለፍ መጠቀሙ እንዲባረር ምክንያት ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የዩቲዩብ ቻናል ከፕሮፓጋንዳዎች በተጨማሪ ለአርቲስቶች ክፍያ የማይፈጸምባቸው ድራማዎች፣ ዘፈኖች፣ አስገራሚ ታሪኮችና ሌሎችም ይቀርቡበት ነበር።
ይህን የሰሙ አስተያየት ሰጪዎች”ሕዝብን መስረቅ የለመደ መንግስት በኢንተርኔት እሰርቃለሁ ሲል እጅ ከፍንጅ ተያዘ” ሲሉ ተሳልቀዋል።
ዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ ወደ ኢቲቪ የዩቲዩብ ቻናል በመሄድ እንዳረጋገጠቸው አካውንቱ ሲከፈት YouTube account ethiopiantv has been terminated because we received multiple third-party notifications of copyright infringement from claimants including: David Tesema” ይላል። ይህን ለማረጋገጥም፦
http://www.youtube.com/user/ethiopiantv

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop