ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ እና ዶ/ር በያን ሱባ -በገበየሁ ባልቻ

በገበየሁ ባልቻ

ባለፈዉ ጊዜ ሁለቱ ልሁቃን ዶፍቶሮች በፈረንጂ እዉቀታቸዉ የተመሰከረላቸዉ ምሁራን (በኢትዮሚዲያ) የተመላለሱትን በመመልከት የበኩሌን በጉዳዩ ዙሪያ ሀሳብ ልሰጥ አስቤ የአባይ ጉዳይ በረድ ይበል በማለት በጋዉን ስጠብቅ ባጀሁ።

ዶ/ር ፍቅሬ ዶ/ር በያን የሚመሩት ድርጅት ኢትዮጵያዊ ይዘት ያለዉ መስሎ ስለታያቸዉ መሰለኝ ዘመን ተሻግረዉ ማህደር ፈልፍለዉ ልዩ ጥናት አካሂደዉ በዘመኑ ያለነዉን ሁሉ የሚያስደምም የምርምር ድርሳን አቀረቡ። በጥናቱ መሰረት ኦሮሞ እና አማራ የአንድ ቤተሰብ ልጆች ከመሆናቸዉም በላይ በየጊዜዉ የኦሮሞ ተወላጆችንን አንገት የሚያስደፋዉን አሉባልታ ወደጎን በመተዉ በማንኛዉም የኢትዮጵያ አስተዳደር ኦሮሞ ያልተሳተፈበት ወይም ደግሞ ኦሮሞ ያልገዛበት ዘመን እንደሌለ በርቀት ተጉዘዉ መረጃ አስደግፈዉ ገለጹልን ። በዚሁ መልእክታቸዉ  ለዶ/ር በያን እንዲህ ያለ የምርምር ሰነድ ካሻችሁ ከጎናችሁ ነኝ ሌሎች ኢትዮጵያዉያንም በኢትዮጵያ ምድር ለሚደርሰዉ ማንኛዉም በደል ዘር፤ ወገን፤ ጎሳ፤ሀይማኖት ሳንለይ አብረን እንታገላለን በማለት ቃላቸዉን ሰጡ። ነገር ግን ማንኛዉም እንቅስቃሴ፤ሀሳብ፤መመሪያ አሉባልታ ላይ ያተኮረ ወይም ደግሞ ፈረንጂን እና የኢትዮጵያ ጠላቶችን የሚያስደስት ሳይሆን ኢትዮጵያዊ ይዘት ያለዉ የእኛዉ መሆን አለበት በሚል አገላለጽ አድናቆታቸዉን፤ ምስጋናቸዉን፤ ምክራቸዉንና ትብብራቸዉን ለ/ዶር በያን እና ይመሩታል ለተባለዉ ድርጅታቸዉ አበሰሩ እኛም በእጅጉ ደስ አለን።

ዶ/ር በያን ለዚህ ሀገራዊ ጥያቄ መልሳቸዉ ሲጠበቅ ብዙም ሳይቆይ ከመቅጽበት ብቅ አለ። በእዉነቱ የዶ/ር በያን መልስ በእጅጉ ይጠበቅ ነበርና ስማቸዉንና ምስላቸዉን ስንመለከት ልባችን ቀለጠ በስንት መከራ ከፈረንጅኛ ወደ አማርኛ ገልብጠን ስንረዳዉ በተቻለ መጠን ልዉዉጡን እኩል በማድረግ  የዶ/ር በያን መልስ ስምን ሆነ ብሎ በመለወጥ እና ስምን አሳስቶ በመጻፍ ላይ የተነጣጠረ ዉንጀላ እና ክስ ሁኖ ቀረበ (ሼክስፒር ፈይሳ እንዴት ያዩት ይሆን ይህን ነገር?)። በዉነቱ ዶ/ር ፍቅሬ ያን ያህል የተጉዋዙ እና ታሪክን ያብላሉ በፈረንጂ እርሶ የተባሉ ምሁር ይህ ጠፍቷቸዉ አልመሰለኝም። ስምን በተመለከተ ራሺያኖች ኢትዮጵያን ኢፊዮፒያ፣ ጃፓንን  ያፖኒያ…….ሲሉ የኛ የጥንቶቹም ለንደንን  ሎንዶን፤ግብጽ ምስር፤አዉስትሪያ ነምሳ…….ጣሊያኖች ኢትዮጵያን  አቢሲኒያ እንግሊዝን ኢንግልቴሪያ…….እያለ ይቀጥላል። ሌሎቻችሁም በስደት በያላችሁበት እንዲሁ እናንተ ከምታዉቁት አጠራር ዉጭ የአገሬዉ ሰዉ የሚጠራበትን  አጠራር ሳትስሙ የቀራችሁ አልመሰለኝም። እዚህ ላይ አሁን የምንሰማዉ ቋንቋ ዶ/ር በያን እንደሚፈልጉት ወደፊት አሁን ባለበት ሁኔታ ሊቀጥል አይችልም። ቁዋንቁዋ በንግድ፤በትምህርት፤በሀይል፤ከዉስጥና ከዉጭ ባለዉ ግፊት፤በስልጣኔ፤በወረራ አጠራሩ እና አጠቃቀሙ ይለዋወጣል፤ይዳቀላል፤ ካልጠቀመም ይጠፋል ለምሳሌ መኪናን የሚተካ ቴክኖሎጅ ተፈልስፎ መኪና ከጠፋ ያንን ጽንሰ ሀሳብ የሚተካዉ መኪና ከጊዜ ብዛት መጥፋቱ ግድ ይላል።

ተጨማሪ ያንብቡ:   ህይወት እደዋዛ - ቤተልሄም ጌታቸው

በዚህ መልኩ የምስራቅ ፍልስፍና አራማጆች፤ ብሄረተኞች፤ ነገድን ለመቀስቀሻነት ለመጠቀም ሲሉ ቋንቋን  ከዳቦ በላይ አቅርበዉታል። እዚህ ላይ በእርግጠኛነት ለመናገር የ/ዶር በያን ልጆችም (ካላቸዉ)  ኦሮምኛዉን ከእንግሊዝኛ በላይ ያዉቁታል ማለት ይከብደኛል ለዛዉም ኦሮምኛዉን ካወቁት። በዚህ በዘመናችን እንኳን ፔሪስትሮይካ የሩሲያኖች ቁዋንቁዋ ወደ እንግሊዝኛዉ ተጠቃልሏል። በጀት፤ካልሲ፤እስክሪፕቶ፤አስቢዳሌ እንደዉ ሌላም ሌላም።ይህ ሁሉ ቅይጠት እና አጠቃቀም የመጣዉ የቁዋንቁዉን ባለቤት ለማስቀየም ሳይሆን ቋንቋ የተናጋሪዉ እንጂ የማንም ባለመሆኑ ነዉ። ወደ ምእራብ ኢትዮጵያ ብዙ የአማራዉ ብሄረሰብ አባሎች ዛሬ ጆሯቸዉን ቢቆርጧቸዉ አማርኛን አይሰሙም በሌላ አካባቢ የተወለዱ ኦሮሞዎችም በአንጻሩ እነዲሁ ከትዉልድ ቋንቋቸዉ በላይ የመጠቀሚያ ቋንቋቸዉን አጥብቀዉ ይዘዋል።

ቁዋንቋ ሀሳብን የመግለጫ ልሳን እንጂ ምንም ማለትም አይደለም። ለምሳሌ የአዉሮፓ ማህበረሰብ አባሎች ቁዋንቋቸዉ እንግሊዝኛ እንዲሆን ወስነዋል። ማንኛችንም እንደምናዉቀዉ እንግሊዝ የአዉሮፓ ማህበረሰብ አገር ወዷትም አይደለም ኢኮኖሚዋም ቢሆን ከሌሎች የበለጠ ስለሆነም አይደለም እንግሊዝ የአዉሮፓ ሀገሮችንም ወርራ ቋንቋቸዉንም እንግሊዝኛ እንዲሆን አስገድዳም አይደለም ነገር ግን በተለያዩ መስፍረቶች እንግሊዝኛ ለማህበረሰቡ ከሌሎች ቁዋንቁዎች በላይ አገልግሎት ይሰጣል በሚል ግምት እንጂ። የህዋት አስተዳደር አማርኛ እና አማራ ላይ ካለዉ ጭፍን ጥላቻ የተነሳ አማርኛን ከስሩ መንግሎ ለመጣል ያላደረገዉ ጥረት አልነበረም ሆኖም ተጠቃሚዉ የሚጠቅመዉን በማወቁ እነሱኑ ጨምሮ አማርኛ አማርኛ እንደሆነ ቆይቷል። አቶ መለስ ወደ ሁዋላ ላይ የአማርኛቸዉ አጠቃቀም ከዋሸራ የተመረቁ አስመስሏቸዉ ነበር ብቻ ለመልካም ስራ ስላልተጠቀሙበት የቋንቋዉ ባለቤት ጠራቸዉ።እዚህ ላይ ከመሰረቴ ሳልወጣ ታላቁ ሎሞኖሶቭ የሩሲያን የቁዋንቁዋ ህግጋት ሲያወጣ የኢትዮጵያን የቋንቋ ህጎች (አማርኛን) ተጠቅሟል ይላሉ ሩሲያኖች በመጻፋቸዉ እንግዲህ ምን ልንሆን? ሩሲያኖች ተዋረዱ ማለት ነዉ? አይ የኛ ፍልስፍና።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አማካሪ የሌለው መንግስት አገር እያፈረሰ ነው - ገለታው ዘለቀ

ብቻ በማይረባዉ ስትነጫጩ ኑሩ ስላለን በማይረባዉ ስንክሳር ሁሉ ስንባላ እንኖራለን። ህዋትም መርዙን እኛ ዉስጥ እየረጨ መኸሩን ይሰበስባል ፈረንጅም፤አረብም እንዲሁ።  በአጠቃላይ ዶ/ር በያን ዶ/ር ፍቅሬ በዝርዝር የጠቀሱትን መልካም ነገር በመዝለል  ለምን በሱባ እና ጅክሳ ላይ አይናቸዉ እንዳረፈ ከሳቸዉ በስተቀር ማንም ሊያዉቅ አይችልም። አኝህ አንድ ድርጅት እንዲመሩ ስልጣን እና ሃለፊነት የተሰጣቸዉ ሰዉ በዚህ መልሳቸዉ ማንነታቸዉን አመላክተዉናል።

በአዉሮፓም ሆነ አሜሪካ ተፎካካሪ መሪዎች ወደ ስልጣን ሊመጡ ሲሉ ጠያቂዎች እልህ አስጨራሺ፤ የሚያበሳጭ፤ እዉቀትን፤ ድፍረትን፤ አርበኝነትን፤ ማስተዋልን እና መሪነትን የሚለካ ጥያቄ ይጠይቋቸዋል። የዚህ አይነት የከረረ ጥያቄ መሪዉ በዉጥረት ጊዜ የአመራር ችሎታዉን፤ ትእግስቱን፤እዉቀቱን፤ማመዛዘኑን ለመለካት እድል የሚሰጥ አጋጣሚ ነበር። እስቲ እንግዲህ እግዜር የሳያችሁ ዶ/ር በያን እና ዶ/ር ፍቅሬ በአንድ መድረክ ላይ ተገኛኝተዉ ቢሆን ኑሮ ሊደርስ የሚችለዉን በአይነ ህሊና እንገምት ወይም ደግሞ ዶ/ር በያን ትልቅ ጦርና አገር እንዲመሩ እድል ቢሰጣቸዉ  ሊደርስ የሚችለዉን መገመት አስቸጋሪ አይሆንም።

እድል ሆነና እኛ አካባቢ ግን በድርጅትም ሆነ በሀገር አቀፍ ምርጫ መሪዎቻችን በእኛ ተመርጠዉ አያዉቁም እንዲሁ በተንኮል፤ በጭካኔ እና በቡድን ስልጣን ላይ ቁጭ ብለዉ በዉርደት ወይም ይድፋዉ እየተባለ በእርግማን ይወርዳሉ። አቶ መለስ እና ዶ/ር ጳዉሎስን ማለቴ አይደለም የነሱ ከእዚህ በላይ ነዉ።

እንግዲህ ዶ/ር በያንን ልብ እና ትእግስት ይስጥልን እያልን ዶ/ር ፍቅሬን ደግሞ በጎደለን የእዉቀት ክፍተት እንዲሞሉልን እንጠይቃለን የጀመሩትንም የፍቅር ተልእኮ በጀመሩት መንገድ እንዲቀጥሉም አደራ እንላለን ከቂም፤ ከጥላቻ፤ ከመከፋፈል፤ ከተንኮል ምን ይተርፋል?። በዘመናችን ከሻቢያ ብዙ መማር አንችልም ነበር?  ሲንጋፖር ሊሆን የታሰበዉ አገር ዛሬ ፓስታ እና በርበሬ በፖስታ ከአዉሮፓ እና አሜሪካ እየተላከለት አሁን ኑሮ ነዉ ይሄ?። በዉነቱ የህዋት መንግስት አቅፎ ደግፎ ባይዛቸዉ ዛሬ ኤርትራ ዘጠኝ ቦታ አይከፋፈልም ነበር? ለማንኛዉም መቻቻል እና አርቆ ማሰብን ይስጠን። ማነዉ አማራን እና ኦሮሞን ወይም ደግሞ ደቡብን እና ትግሬን ወይም ሱማሌን እና ወላይታን አፋርን የሚለየዉ? ኢትዮጵያዊ ሁሉ በስነልቦናዉም ሆነ መልኩ ጠባዩ ተመሳሳይነት ያለዉ ነዉ ይህም ተፈልጎ ሳይሆን አብሮ በመኖር የፈጠርነዉ ትስስር ነዉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጭካኔ ጥጉ የቱን ያህል ይረዝማል? - እውነቱ ፈረደ

ለማንኛዉም በቸር ይግጠመን gebeyhubalcha@yahoo.com ካጠፋሁ በዚህ አናግሩኝ

ገበየሁ ባልቻ

 

13 Comments

  1. Gebeyehu Balicha kkkkkkkkkkkkkkkkkkkk, do you think you are smart.
    Why do not you come up with your real name Ato Difabachew Erigete Mintesinot kkkk.
    I wounder why nefitegnas always choose to use fake name.

    Anyways you wasted my time Mr Gebeyehu Balicha ( Ato Difabachew Erigete Mintesinot ).

    • Gebeyehu Balicha ani oromodha jete kkkkkk oromo taatuus Jalee akka teetii eega dhagayuu dhifne bubbullerra hindhiphatini waanuma sitti kennan funannadhu.Amboti dhalatuun dhira namagootu,dhirra yoo dhalatan malee!!!!!!!!!!

    • aba dula,
      i have come across a few Woyanes, who try to rationalize the irrational or engage in face saving endeavor, but you, MUST BE A THIRD LEVEL TPLF in that an idiotic one! for you are displaying the very weakness Mr.Balcha is exposing, which is at best ignorance at worst ethnic politics

  2. Aba dula kkkkkkk
    Why don’t you use your real name … Aboy gebremedhin .gujeli tigree

  3. ABADULA, why did you frastrate to write your right name like HAGOSE GOITOM.your Idea is stupied nonsense. I am oromo .I born Ambo. i like Dr, Fikre I dea rather Dr. Beyan. This is the real . I am Ethiopian oromo. Long live Ethiopia.

  4. Ato Gebeyehu, you are telling us to abandon Afaan Oromoo and use Amharic language. The Ethiopianists have always wanted the Oromo people to abandon Afaan Oromoo and speak and write in Amharic. The Europeans used to tell African to use English, French and Portuguese to write their literature. Ngugi Wa Thiong’o reponded like this: “There is something very wrong in saying to a human being, let me cut off your legs, and I will give you artificial ones, which will be perfect. I’ am saying let us walk on our own two feet.” Ato Gebeyehu, leave us alone. You are telling the Oromo people that artificial legs are better than the natural ones. No one believes you. You are trying to deny us Afaan Oromoo, the production of knowledge.

    • Thank you, for your swift response that is not my intention and I am no one to tell what language you should use, the aim of the article is not intended in this way unless it is derailed by feeble mind. Truly speaking either you or lencho/juwar/dima and the rest can not be more oromo than Laureat Tsegayea/Keflea Dadi/Balcha aba nebso/Mesfin Selshi and the rest, I dont want to say more than this and I am one of the citizens ready to die for the cause of oromo but not in line with the above people i mentioned. many thanks

  5. FAKE NAME WILL NOT TAKE U ANY WHERE MAN!

    Let say this abandon Afaan Oromo is a day dream for habesha’s and their likes .
    we gone far man with our Qubee never to turn back
    so never try to write about oromo or ormos affairs no one will pay attention to your trash.

    • Faajjii…et al, You are the one who is fake. You already lost your identity. We,the Oromo people are just like other Ethiopians. We are generous, friendly, and peace loving people. We don’t support your stupid idea, i.e. hateful approach to other tribes. We are oppressed by different regimes just like our brothers and sisters. We will fight for freedom, justice and equality together with the rest of Ethiopians. Don’t forget our heroes like Abdissa Aga, Abebe Bikila and many Ethiopian Oromos who bled and sweat for their country. You are an opportunist who wants to get into the throne in the name of the Oromo tribe and torture us just like your master woyane.

  6. Kkkkkkkk!!!! Gabayiyyee! What fikre wrote and you supported seems good. But you are talking what you thought it is right for you. I hope you must be good at writting fiction. But fiction and history are different. Ask the Oromos what Oromo history is. Our Dr. fikre is telling us milk is black. Hey men! Please liston to the heart beating of Qube generation. You know ‘what is inevitable to happen will happen!’ thanks to WQ we have known every thing.

Comments are closed.

Share