አባይ አባይ። ዳዊት ዳባ

Friday, March 27, 2015

ኬንያ ስደት ካንብ ውስጥ ልጆች ኳስ ተቧድነው ይጫወታሉ። አሊ ለብሩክ አቀበለው። ብሩክ ወደጎል መታት።  ኡመት በቀላሉ ያዛት። ኡመት ለጋ አሁን ኳሷ ጅግሳ ጋር ናት:: ጥሩ አድርጎ ለገብሬ አቀበለው። ገብሬ ደስ በሚል አብዶ ሰርቶ ተከላካዩን ደንፎን አለፈ። አሁን ገብሬና ግብ ጠባቂው ጆሬጌ ብቻ ነው ያሉት። ገብሬ ገብሬ ብቻውን ነው፤ አደገኛ ሁኔታ ነው። ገብሬ መታ ። አይይ ለትንሽ፤ ለትንሽ።  ኳሷ የግቡን እንጨት መታ ወደውጪ ወጣች።

ከተመልካቾቹ መሀል ከድጃ የኔ ነው። የኔ ነው እያለች ወደኳሷ እሮጠች። ሌሎች ተመልካቾችም ተከትለዋት እሮጡ። ከድጃ ከኳሷ ወስጥ የሆነ ነገር ደስ እያላት መዛ አወጣችና ኳሷን ወረወረችላቸው። ከዛም የኔ ነው በቀጣይ ኳሱ ውስጥ የሚገባው ጭቅጭቅ በሌሎቹ ተረኞች መሀል ጠብ ሆነ። ከድጃ የስልኳ ቻርጀሯ አልቆ ስንት ቀኗ  ፍሴ ቡክ ከገባች።ያኔውኑ  ስልኳ ላይ ገጥማ ቻርጅ ማድረግ ጀመረች። ጓደኞቿ ትግስት፤ ፋጡማና ሌንሳም የነሱንም ስልክ ቻርጅ ለማድረግ የሚበቃ የተጠረቃመ ሀይል እንዳለው ስለሚያውቁ አብረዋት ተደሰቱ።

ግድቡን በሚመለከት ሰብሰብ ባለ መንገድ መነሻ ስምምነት ተብሎ በየሜዲያው ላይ የያነው እውነተኛው ስምምነት ነው ወይ?። ወይስ   እንደአየር ጥቃቱ የውሸቱ ነው። ይህን እንድል ያስቻለኝ ጠንካራ ተቃውሞ እየሰማው ስላልሆነ ነው። ስምምነቱ እኔም ልረዳው በምችል ቀላል በሆነ እንግሊዘኛ የተፃፈ ነው።  በእርግጥም የእውሸቱ ቢሆን ይሆናል። አንብቤው የእውሸቱ በሆነ ስል ነው የፀለይኩት። ምክንያቱም  አባይን ውሀ ግብፅ ውስጥ በረዶ አድርገው ቤት ቢሰሩበት፤ ቢመርዙት ፤ ብቻ ያሻቸውን ቢያደርጉት ስምምነት በተባለው ዶሴ ውስጥ በሙሉ እኛ ይህን ማድረጋቸው በዚህ መልክ ጎድቶናል ብለን ልንከስም ሆነ ልንከራከር የምንችልበት መንገድ ባስበው ባስበው አልታየኝ አለ። ስምምነቱ እኛንም ግብፅንም ሱዳንንም በጋራ የምንገዛበትና ተጠያቂ የሚያደርግ ቢመስልም አንድና አንድ በሆነ ሁኔቴ ኢትዬጵያ ማድረግ፤ አለማድረግ፤ መውሰድ ያለባትን ጥንቃቄ በሚመለከት የተጣለባት ግዳጅ ሆኖ ነው ያገኘሁት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጠብ-መንጃ አናነሳም! (ተመስገን ደሳለኝ)

ግድቡን ለኤሌክትሪክ ማመንጫነት ብቻ ለመጠቀም እንደሆነ እንደተፈራው በስምምነቱ ተካቷል። ከበፊቱም የተገነባው ጠረፍና ለእርሻ የሚሆን መሬት የሌለበት ቦታ ላይ ስለሆነ ለመሰኖ አገልግሎት ለማዋል እስቸጋሪ እንደሚያደርገው አካባቢውን በሚያውቁ ዜጎች  ሲገልጽ ነበር። በእርግጥ ወያኔዎችም ግድቡን ከኤሌክትሪክ ማመንጫነት ውጪ ለሌላ አገልግሎት የማይውል መሆኑን ቀድሞም አልደበቁም። ማንንስ ፈርተው ይደብቃሉ። ይህም ሆኖ ይገደብ እንጂ ወያኔዎች ለዘላለም አይኖሩም። ወደፊት  ወሀውን በቦይ ወደሗላ በመመለስ ለመስኖም ሆነ ለሌላ አገልግሎትም ለመጠቀም እንችላለን ተብሎም ተስፋ ተሰጥቶም አንብቤያለው። አሁን  እድሜ ለወያኔ ግድቡ እንጂ ውሀው የኛ ባልሆነበት ሁሉም ነገር በስምምነቱ እልባት አግኝቷል።

ውሀውን መከልከላችን ሳያንስ ተንከባክበንና አጣርተን ግብፆችን ማጠጣት ተስማምተን የፈረምንበት መሆኑ  እንዳለ “የኤሌክትሪክ ሀይል “ ተብሎ የሚደሰኮርበት እራሱ በቅጡ አልተመረመረም ባይ ነኝ። ወያኔዎቹን ትተናቸው ሁላችንም በይበልጥም  ሙህራኖቻችን ያላዩት ስለዚህም ያለነሱት ወና ችግር ያለ ይመስለኛል። ስብሰለሰልበት ከጀመረ ቆይቷል። ግድቡን በሚመለከት ሲነሳ የነበረው ስጋት በድህነት ከአለም አገሮች ጠርዥ ላይ ያለች አገር ለአንድ ግድብ ብቻ ይህን ያህል የአገር ሀብት አሟጣ ማፍሰስ በብዙ ጎኑ ይጎዳናል። ከተገደበና ሀይል ማመንጨት ከጀመረም በሗላም ይህ ግድብ  ከፍተኛ ወጪ ያለው ነው። ግድቡ መጨቆኛ፤ በዜጎች ዘንድም ለአባይ ካለ ጥልቅ መቆርቆር ፈቅዶ መጨቆኛም ሆኗል  የመሳሰሉ ስጋቶች ነበሩ።

የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨትን በሚመለከት በአለሞያም ባንሆን፤ የጠለቀ እውቀቱም ባይኖረንም ከመረጃ የራቅን ካልሆንና ሜዲያዎችን የምንከታታል ከሆነ በርካሽ ማመንጨትንና  መጠቀምን  በሚመለከት በሚቀጥሉት አስርና ሀያ አመት አለም ምን አይነት ገፅታ እንደሚኖረው መገመት አይከብድም። ተግባር ላይ ውለው ልናያቸው የሚችሉትን የተሻሉ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ አማረጮች ብዙ ናቸው። ኤሌክትሪክ በምን ደረጃ በቀላሉ ሊዳረስ እንደሚችል። ምን አይነት ዋጋ ሊኖረው እንደሚችል መገመትም እንዲሁ ከባድ አይደለም።  በቀላሉ በቀጣይ እንደሞባይል ስልክ የፀሀይ ብርሀንን የሚሰበስበው ፓናል  የአለም ህዘብ ሁሉ ይኖረዋል። አይደለም ህንፃዎች ላይ በየጎጆ ቤቱ ላይ የምናየው ዲሽ የሚሆን ይመስለኛል። አሁን ባለው ገበያ እንኳ በምኖርበት አገር ሰዎች ከ$300 እስከ $1000 ዶላር ባልበለጠ ወጋ  ጣርያቸው ላይ ፓናሉን በመግጠም የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን እየሸፈኑ ነው። እኔ እራሴ $29 በፀሀይ ብርሀን የሚሰራ መብራት ለቤተሰቦቼ አገር ቤት ልኬላው። አንዴ ጨክኜ ፓናሉን ባስገጥም ደግሞ ከገቢያቸው አልመጣጠን ብሎ ከሚማረሩበት ወራዊ የመብራት ክፍያ ይገላገላሉ። በፀሀይ ብረሀን የሚሰራው መብራቱ የ$19 ገበያ ላይ ነበር። የኤሌክትሪክ ሀይል ከንፋስ ከቆሻሻ፤ ከኒኩለር ለዛውም ከመጨረሻው ዝቃዥ መጣያ እየጠፋ ሲቸገሩበት ከነበረው ሳይቀር መጠኑ እጅግ ትልቅ የሆነ ማመንጫነት ተችሏል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ህውሃት እያዘናጋን አንዳይሆን! ለህወሃት መዘናጋት በትውልድ ላይ መፍረድ ነው፤ - ገብረ አማኑእል፤

ከፀሀይ ብርሀን የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሀይል ይህ በትልቅ እንዱስትሪ ደረጃ የሚሰራም አይደለም። “ ጁአካሊ” በኪሲዋሊ። “በጥቃቅንና አነስተኛ  ሰዎቻችን በሚሉት  በየጎጆ ቤቱ ላይ ሊገጠም የሚችል ነው። ዛሬ ዲሽ የሚገጥሙ ሰዋች ፓናል የሚገጥሙ ይሆናሉ። ኦባማ በቀን ውስጥ ስንት ቤቶች ነበሩ ከፀሃይ ብረሀን ከሚገኝ ኤሌክትሪክ ለማመንጨትና ፍጆታቸውን ለመሸፈን ይቀየሳሉ ያለው?። አሁን አሁን የመንገድ መብራቶች፤ አፓርትመንቶች፤ የንግድ ቦታዎች ፤ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን ከፀሀይ ብርሀን እያገኙ መሆኑን ዞር ዞር ሲሉ ትኩረት ሰጥቶ ማየትን ብቻ ነው የሚፈልገው።

በቅርብ አሜሪካኖች የአፍሪካ መሪዎችን በሙሉ በትእዛዝ ጠርተው  በዋናነት ቃል የገቡላቸው በሉት ያስሟሟቸው ሀይል በማመንጨት አፍሪካ ላይ መዋለንዋይ ሊያፈሱ ነው። ለአፍሪካችን ተጨንቀው ያበረከቱት ቾሮታ።መሪዎቹ በአስቸኳይ የተጠሩበት ዋናው ጉዳይ ይህው ነው። አሜሪካኖች በቀላሉና በርካሽ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨት እንደሚቻል አውቀውበታል። ጠቅላላ አፍሪካ ገና ጭለማ ውስጥ ነው ያለው። ከዚህ በላይ ገንዘብ የሚዛቅበት አውድማ መቼም የለም።  መቼም አምስትና አስር ቢሊዬን ብር እያወጡ ግድብ ገድበው አፍሪካን ብረሀን በብረሀን ሊደርጉ ነው ቆርጠው የተነሱት ብለን የምናስብ አንኖርም።

ግድቡ አለቀ እንበል። ለኛ ስንት ዘመን ስንመኘውና ስንዘፍንለት የነበረ  ከአባያችን የተገኘ ስለሆነ በግዳጅም ጭምር ገበሬው ሳይቀር መብላት ትቶ መብራት ይኑረው። ለኬንያ፤ ሱዳንና ጅቡቲ ለሌሎችም አገሮች እንዴት በአለም ገበያ አወዳድረን በቅናሽ እንዲገዙን እንደምናደርግ የሚታይ ይሆናል። አፍሪካዊው አንዴ ሶስት መቶ ዶላር ከፍሎ ለዛውም ላንድ አንፖል ቢበዛ ለፍሪጅ በቀላሉ ኤሌክትሪክ ማግኘት እየቻለ በየወሩ ለመብራት ለምን ይከፍላል። የትኛው አፍሪካዊ መንግስት ለዛውም መንግስት ሳይገባበት ዜጋው እራሱን ችሎ ሊያደርገው ሲችል በየወሩ የውጪ ምንዛሪውን አሟጦ ለኛ እየከፈለ ነው የሚያበለፅገን። በጭራሽ የማይሆን የሞኝ ሀሳብ ነው። ምን አለ በሉኝ ሁሉ ባለ መብራት የሚሆነው ደግሞ እኛ ላባችንና አንጡራችንን ጠብ አድርገን አባይን ገንብተን በምንጨርስበት ጊዜ ጋር እኩል ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አልተገናኝቶም! - በገለታው ዘለቀ

ለማንኛው በመጪው አስርና ሀያ አመት በሗላ ኤሌክትሪክ ሳይሆን እራሱ “ውሀው” ነው መዳረሱ አለምን እያስጨነቀ ያለው። በቀጣይ ያአለምን ፀጥታ የሚፈታተነው ነዳጅ ዘይት ሳይሆን ውሀ መሆኑ ብዙ ተብሎበታል። ውሀ የማያልቅ የማይመስለን ተሳስተናል። አላቂ  ሀብት ነው። ይሄ  ስምምነት ደግሞ አይደለም ከግድቡ ከገባር ወንዞችም በጣሳ ቀድተን ስንጠጣ ግብፅና ሱዳን አዩን አላዩን እያልን እንዲሆን የሚያደርግ ነው።  አንዴ ጉዶች ነግሰውብናል። ሊያውም የሚያደባብን። ወገን ለራሳችን እንወቅበት። ምን ማድረግ እንደምንችል ባላውቅም። ዝም ግን አንበል።

 

Share