ሰበር ዜና -የአንድነት ፓርቲ እና መኢአድ ቅድመ ውህደት ፊርማ እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2006 እንዲደረግ ተጠየቀ

በያሬድ አማረ

ፍኖተ ነፃነት

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በውህደት ጉዳይ ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጋር ሲደረግ የነበረው ውይይት በመጠናቀቁና ሁለቱ ፓርቲዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ስምምነት ላይ በመድረሳቸው ምክንያት የቅድመ ውህደት ፊርማ ስነ-ስርዓት ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ መወሰኑን የሚገልፅ ደብዳቤ ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መላኩን የመኢአድ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነው ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡
እንደ ኃላፊው ገለፃ የቅድመ ውህደት ፊርማ ስነ-ስርዓቱን የሚያስፈፅሙ ከመኢአድ የተወከሉ የኮሚቴ አባላትንም ጭምር ያሳወቁ መሆኑንና በቀጣዩ ሳምንት የሚደረገው የቅድመ ውህደት ፊርማ ስነ-ስርዓትን በማካሔድ በአጭር ግዜ ውስጥ ሁለቱ ፓርቲዎች ወደ አንድ ውህድ ፓርቲነት እንደሚጠቃለሉና በቀጣይ ትግሉን በአንድነት ለመምራት የሚያስችል ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፖሊስ አላሰርኩትም › ያለውን አስራት አብርሃምን ፍርድ ቤት አቀረበ

2 Comments

  1. I wish it but I don`t think that they will unite while Abesha can eat together but can`t work togetrher.

  2. Birtu, that was a little bit cheap. I’m not sure if you realize that you’re reinforcing a negative stereotype of others on your self. I understand if you have skepticism about the merger, but please keep your self degrading opinion to your self.

    One can give countless examples where Ethiopians have achieved many things by joining their efforts together. At the moment what we need is positive outlook and everyone to do what can be done, but we don’t need attitudes that dampen our spirit.

    Ethiopia’s freedom from TPLF/EPRDF oppression through united actions of her heroic sons and daughters is imminent!!!

Comments are closed.

Share