“የኢትዮጵያን ትንሣኤ ሊያረጋግጥ ሃያል ባለስልጣን ነብዩ ኤልያስ ከብሔረ ህያዋን ጳጉሜ 1/2003 ዓ.ም ወደ ምድር መጥቶ በመካከላችን ይገኛል፣ ኦርቶዶክስ የሚባለው የሃይማኖት ስም ስህተት ነው ተዋህዶ ነው መባል ያለበት፣ ሰንበት ቅዳሜ ብቻ ነው፣ መለበስ ያለበት እግዚአብሔር ለኖህ ቃል ኪዳን የገባበትን ቀስተ ደመና ቀለማት ያካተተ ጥለት ያላቸው ነጭ አልባሳት ናቸው” የሚል አዲስ እምነት እያራመደች ያለችውና ነብዩ ኤልያስ ወደ ምድር እንደመጣ የምታምነው አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አዲስ ባቋቋመችው እምነት የተነሳ መታሰሯን ከአዲስ አበባ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገበ።
በተለያዩ የመድረክ ቴያትሮች፣ በቴሌቪዥንና በሬዲዮ ድራማዎች በተለይም “ገመና” በተሰኘው ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ የእናትነት ገፀ – ባህሪን ተላብሳ በመተወን የምትታወቀው አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን ታሰረች፡፡ አርቲስቷ ማክሰኞ ማታ ተይዛ አራት ኪሎ የሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ከታሰረች በኋላ ረቡዕ አመሻሽ ላይ ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ መዛወሯንና ከእርሷ ጋር ሌላ አንዲት ሴትና ሁለት ወንዶች መታሰራቸውን በስፍራው ተገኝተን አረጋግጠናል ያለው የአዲስ አድማስ ዘገባ አርቲስት ጀማነሽና አብረዋት የታሰሩት ግለሰቦች ሃሙስ እለት አፍንጮ በር መንገድ አዲስ አበባ ሬስቶራንት አካባቢ በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጀ ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው የታየ ሲሆን በድጋሚ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡም ዘግቧል።
ጋዜጣው ዘገባውን በመቀጠል “አርቲስቷንና አብረዋት የታሰሩትን ሰዎች ለመጠየቅ ወደ ስፍራው ከመጡ ግለሰቦች ለመረዳት እንደቻልነው፤ አርቲስቷና አብረዋት ያሉት ሰዎች የታሰሩት “ማህበረ ስላሴ ዘ ደቂቀ ኤልያስ” ከተባለው ማህበራቸውና ከሀይማኖት ጉዳይ ጋር በተያያዘ እንደሆነ ጠቁመው ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ከአርቲስቷ ጋር የታሰሩት አንድ የሃይማኖት አባት፤ ጉዳዩ በፍርድ ቤት የተያዘ በመሆኑ ከፍርድ ሂደቱ በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ፣ አሁን ምንም አይነት ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ነግረውናል፡፡ አርቲስት ጀማነሽን ሊጠይቋት የመጡ ሰዎችን ለማነጋገር ስትወጣ በተመለከትናት ጊዜ በፈገግታ የታጀበች ሲሆን ጠያቂዎቿ “እንዴት ነሽ ተመቸሽ?” ብለው ሲጠይቋት “እግዚአብሔር ያለበት ቦታ ሁሉ ምቹ ነው” ስትል ምላሽ ሰጥታለች፡፡ አርቲስቷ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ተዋህዶ” በሚል ሃይማኖት ውስጥ ተሣታፊ በመሆን አነጋጋሪ ሆና መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡” ብሏል።
“ወረዳ ዘጠኝ ፖሊስ ጣቢያ በተገኘን ጊዜ የሃይማኖቱ ተከታዮች የሚለብሱት የቀስተደመና ቀለማት ያሉት ነጠላ አጣፍታ፣ ፀጉሯንም የቀስተ ደመና ቀለም ዙሪያውን ባቀለመው ሻሽ አስራለች፡፡ ማህበረ ስላሴ ዘ ደቂቀ ኤልያስ “የኢትዮጵያን ትንሣኤ ሊያረጋግጥ ሃያል ባለስልጣን ነብዩ ኤልያስ ከብሔረ ህያዋን ጳጉሜ 1/2003 ዓ.ም ወደ ምድር መጥቶ በመካከላችን ይገኛል፣ ኦርቶዶክስ የሚባለው የሃይማኖት ስም ስህተት ነው ተዋህዶ ነው መባል ያለበት፣ ሰንበት ቅዳሜ ብቻ ነው፣ መለበስ ያለበት እግዚአብሔር ለኖህ ቃል ኪዳን የገባበትን ቀስተ ደመና ቀለማት ያካተተ ጥለት ያላቸው ነጭ አልባሳት ናቸው” የሚሉትን የተለያዩ ጉባኤዎችን እያዘጋጀ የሚያስተምር ማህበር መሆኑን ያነጋገርናቸው የማህበሩ አባላት ገልፀውልናል፡፡ በተለያዩ ገዳማትም የሀይማኖቱ አራማጆች እንደሚገኙና እንደሚያስተምሩ ያገኘናቸው የሃይማኖቱ ተከታዮች ነግረውናል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ከፖሊስ መረጃ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም፣ ከመምሪያው የተፃፈ ፈቃድ ያስፈልጋል በሚል የወረዳው ፖሊስ መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡” በማለት ዘገባውን አጠናቋል።
she has the right to belief what ever true for her.that is freedom !!!!
Not with the arrogant tyrants ruling the country.
I think this kind of revisionism in our belief system need to be done! I do not know for sure that we used Orthodox as a name when for us the Bet Amharas in south wollo are laid down (develop the frame work for Orit and Haddis belief system )the transition of the belief system from Orit to Haddis kidan! They need to consult the Kibra-Negast, Tarik Negast, Zena Mewal! in Tedbab Tsion(now Tedbab Maryam in Sayint werda south wollo. Also search for clues in Debre Kelanch-Leganibo werda in south wollo. i know from history that there was an old historical connection with outsiders especially with europe countries such as Greek, Italy Vatican,and middle east Egypt, Syria, Armenia..etc. I do not know how much exactly it affected us when The Bet Amhara Preists crafted the ways, rituals, dogmas and other related religious and spiritual motifs of Tewahido! Becareful with the weyane Tigrays-they stole many things since ancient times from us. And they are doing it too. we will take back what is ours!
She has the right to pursue and belief what ever religion ,but she has no right to belittle other people’s belief and religion. No way of knowing which one is right and which one is wrong as all religions are not based on rational reasoning .Rather demand for belief with out questioning the theological dogma. i donot know why one accuse the other for infalliability. Religion is a blind belief.
Jemanesh can practice any religion whatsoever,but she can’t downgrade or denounce the oldest form if Christianity.she has no enough theological merit to evaluate the wright or wrong values of Christanity.
I think she wasn’t pointing her fingers on others but she can compare her thoughts or belief’s to other religions for instances what orthodox, muslim and other religion does their ideology and doctrine. i guess that is not downgraded or insulting others but my anxious is if this case is a crime i may stop speaking about my belief’s , let me put it this way what is true for me may not be true for my brother/sisters so is it criminal ?
She is an evil woman who is starving her husband’s mother.