“ፋኖ የበለጠ ይደራጃል ወደ ኋላ አይልም!”/ “የትግራይን ህዝብን ይቅርታ ጠይቂያለሁ” “ፋኖ በናፍቆት እየተጠበቀ ነው” ገዱ አንዳርጋቸው (ዶ/ር)
7 Comments
Leave a Reply
Latest from Blog
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም
ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ
የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ
ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ አንድ አባውራ ምንነቱ ያልታወቀ እህል ከገበያ ገዝቶ ለሚስቱ አምጥቶ ሰጣት አሉ፡፡ ከሰጣትም በኋላ ሚስቱ ያንን እህል ፈጭታ ቂጣ ላርግህ ብትለው፣ እንጀራ ላርግህ ብትለው፣ ገንፎ ላርግህ ብትለው … ምን አለፋህ
ወሰንየለሽ ኦሮሙማዊ ዕብደት!!
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን
የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር
ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር) ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ
ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?
የቀጠለው ውጊያና የፋኖ ድሎች / የግብፅ ፣ሶማሊያ ፣ኤርትራና ሱዳን ውሳኔ / “የህወሓት መከፋፈል ገደለን “|EN
የቀጠለው ውጊያና የፋኖ ድሎች / የግብፅ ፣ሶማሊያ ፣ኤርትራና ሱዳን ውሳኔ / “የህወሓት መከፋፈል ገደለን “|EN
ከሃይለገብርኤል አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ
የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’
ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም January 10, 2025 በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና
በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡
ሀገሪቱ እኮ የለችም…. የጄነራሎቹ ጉድ…. የአብይ አህመድ ነገር…
ሀገሪቱ እኮ የለችም…. የጄነራሎቹ ጉድ…. የአብይ አህመድ ነገር…
ዓለም ሁሉ ያስደነቀው ሚልዮኖች የተመለከቱት አስደናቂው ቪድዮ| Ethiopian Orthodox Mezmur
YAmaran hezb maleteh newu? Gedu,Juwars,Bekele Gerba,Yayeh sewu Shimles, Bekalu Alamrewu,Berhanuley Nega,Belete Mola yemisetuachihun eyebelachihu btedebqu yishalachihual.
ከሰሞኑ አቶ ገድና ጃዋር በየፊናቸው ቱልቱላ ይነፋሉ። የሚያስገርም ነው። ለነገሩ በሁለቱ መካከል ያለው ልዪነት በRiver Rat (Water rat) እና በBeaver እንስሳት መካከል እንዳለው ነው። ሁለቱም መሰሪዎች ናቸው። የሚያወሩትና የሚለፉት በጥቂቱ ይለያይ እንጂ ገድና ጃዋር ስልጣን ናፋቂዎች ናቸው። የሁለቱ አይጥ መሰል እንስሳትም ተግባር መሰርሰርና ውስጥ ለውስጥ መጓዝ ነው። ጃዋር የፓለቲካ ሳይንስን ተምሬአለሁ በማለት ባልተማረ ህብረተሰብ መካከል ቆሞ የአኖሌን ሃውልት ተደግፎ ፎቶ የሚነሳ ደንቆሮ ነው። አኖሌ ሰዎች እንዲጨራረሱ ሆን ተብሎ በብሄር ፓለቲካ በጠነበሩ የኦሮሞ የዝንት ዓለም አልቃሾችና በወያኔ ሴራ የቆመ የፈጠራ ሃውልት ነው። ዓለም እየጨለመበት እያለ እነዚህ የፓለቲካ ውታፎች ከያሉበት ስርቻ ብቅ ብቅ በማለት ዛሬ ድምጻቸው እንዲሰማ የሆነበትን ሁኔታ ስፈትሽ ጥቂት ነገሮች ትውስ አሉኝ። 1. የብልጽግናው መንግስት የንግስና ማብቂያ ዓመት በመሆኑ – እኔን ስሙ ለማለት 2. በዚህም በዚያም የውጭ ሃይሎች ክፍያና ግፊት በመታከሉ 3. በሃገርና በውጭ ያሉት የት ገባችሁ ለሚሏቸው አለን ለማለት የራስን የመኖሪያ ብልሃት ካሳመሩ በህዋላ የሩቅ ተዋጊ ለመሆን የሚያሰሙት የጣር ድምጽ ነው። ሌላው ሁሉ አሻሮ ሃሳብ ነው።
እውቋ ጋዜጠኛ ቤተልሄም ታፈሰ እንዳስቀመጠችው ጀዋር ፈሪና ነገር አደባላቂ ሰው ነው። ተከበብኩ ድረሱልኝ በማለት ያስጨረሳቸው ንጽሃን ዜጎች ደም ለፍትህ እየጮኸ “አልጸጸትም” የሚል የአፍ ጀብደኛ በተግባር ግን የሌለበት በየጊዜው የፓለቲካ አቋሙንና ቀለሙን የሚቀያይር ሰው ጀዋር ማለት እሱ ነው። ከእስር ቤት ከወጣ በህዋላ እይታውን ሁለገብ አድርጎ፤ የሰላም መንገድን ተከትሎ፤ ባለፈው በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የሰራውን በደል አራግፎ ሰው ይሆናል ስንል ራሱን ናይሮቢ ላይ አስጠግቶ እንሆ አሁን ደግሞ በጀርመንና በሌሎች ከተሞች በመገኘት ለደነዘዘ ህዝብ ይዘላብዳል። ለመሆኑ በማን ፓስፓርት ነው ጀርመን የገባው? የአሜሪካ ፓስፓርቱን መልሷል ተብለን አልነበረም። ግን አሜሪካኖች የሚታመኑ አይደሉም። የወያኔ መሪዎችን ለማይሰምር የሰላም ድርድር በራሳቸው ወታደራዊ አውሮፕላን በየስፍራው እንደ ታክሲ ሲያመላሉሷቸው የነበሩት ለኢትዮጵያ አስበው አልነበረም። ሌሊት ሌሊት በሱዳን በኩል ከግብጽ የተላከ የጦር መሳሪያ በአውሮፕላን ትግራይ ውስጥ ሲራገፍ ደጋፊዎች ነበሩ። ያው የኢትዪጵያ አየር ሃይል በለስ ቀንቶት አንድን መቶ ከጣለ በህዋላ ነገሩ ቆመ እንጂ! አሁንም ወያኔ በድንበር በየብስ መሳሪያ በማጋዝ ላይ ይገኛል። አሜሪካኖች በወያኔ ዘመን ወያኔዎች ያደረጉላቸውን ውለታ ለመመለስ በጦርነቱ ጊዜም ሆነ አሁን ያልፈነቀሉት ድንጋይ አልነበረም! ለጀዋርም በስውር ፓስፓርቱ ተመልሶለት ይሆናል። የጥቁር ህዝቦች እንዲበለጽጉና በሰላም እንዲኖሩ ነጩና ዓረቡ አለም አይፈልግም። ግራም ነፈሰ ቀኝ የኢትዮጵያ ፓለቲከኞች እድል ፈንታ ሁለት ነው። ሞትና ግዞት! የድሃ አድግ ልጆችን ለመከራ ማግዶ በውጭ ሃገር በሰርቁትና ከውጭ ሃይሎች በተቀበሉት ገንዘብ መኖር። ግን ያ መኖር ሳይሆን በቁም መሞት ነው። ለገባው የሃበሻ ፓለቲካ እቦጭ ነው። የውሃ ወቀጣ። አንድ ግን ሌላ አማራጭ የማይገኝለት መንገድ የሰላሙ መንገድ ብቻ ነው። መገዳደሉን አይተነዋል። የብሄር ነጻነት ታጋዮችንም አይተናቸዋል። የእድሜ ልክ ጨካኝ መሪዎች ሲሆኑ፤ ለራሳቸው እንጂ ለህዝብ የማይገዳቸው የማፍያ ስብስብ እንደሆኑ። ጦርነት የእብዶች የእውቀት መለኪያ ማስመሪያ ነው። 12 ኢንች ብቻ! አርቆ ማየት የተሳነው!
የብሄር ፓለቲከኞች በጥቅሉ ድውያን ናቸው። ከላይ በቪዲዪው የበለጠ ይደራጃል፤ ወደ ኋላ አይልም። እየተናፈቀ እየተጠበቀ ነው የሚባለው የፋኖ ክምችት ነጻ አወጣሃለሁ የሚለውን ህዝብ መከራ ውስጥ የዘፈቀ፤ የጠራ የፓለቲካ ጥያቄ የሌለው፤ እርስ በእርሱ የሚሸራገድ የቀማኞች ስብስብ ነው። ይህ ማለት በአማራ ህዝብ ላይ ግፍ በወያኔም በብልጽግናውም አልተሰራም ማለት አይደለም። የአማራ ህዝብ ተለይቶ ተጠቅቷል። እየተጠቃም ነው። ግን በአማራ ክልል ነፍጥ አንስቶ ት/ቤትና መንገድ ዘግቶ የአማራን ህዝብ ወደኋላ መልሶ አማራን ነጻ እያወጣን ነው ማለት መጃጃል ነው። ጊዜ ቆሞ አይጠብቅም። በዘር የተሳከረው የሃበሻ ፓለቲካ ሳይደርሱብኝ የሚበቃኝ ልያዝ እያለ ይኸው መንገድም፤ ት/ቤቱም፤ የመገናኛ አውታሩም የሚሰራው በሌሎች ክልሎች ሆኗል። ስለዚህ ፋኖና ብልጽግና በጋራ የአማራን ህዝብ አግተው እንደያዙት ቁልጭ ብሎ ይታያል።
በመጨረሻም የትግራይ ህዝብ የይቅርታ ጋጋታ አይደለም የሚፈልገው የሚበላው ዳቦና ሰላምን እንጂ። የትግራይ ህዝብ መከራ ወያኔ ራሱ ነው። ወያኔ እያለ የትግራይ ህዝብ ሰላም አይኖረውም። ለማን ተብሎ ነው በወርቅ ፍለጋው ሳቢያ መሬቱ እየታረሰ፤ ያለምንም Land Remediation and Rehabilitation እቅድ አፈሩ፤ እንስሳትና እጽዋት እየተመረዙ ያሉት? የትግራይ ህዝብ ከምሲን ይደርሰዋል? መንገድ፤ ት/ቤት፤ የህክምና ተቋም እነዚህ ቆፋሪዎች ሰርተውለታል? ግን የወያኔ መሪዎች ዛሬ በአውሮፓ/በሰሜን አሜሪካ በየሥርቻው ተሸጉጠው በዘረፉት የሃገር ሃብት ሲፍነሸነሹ ማየት መፈጠርን ያስጠላል። የትግራይ ህዝብ የገድ አንዳርጋቸውንም ሆነ የማንንም ይቅርታ አይፈልግም። በሰላም ሰርቶ ጥሮ ገሮ እንዲኖር ግን ወያኔ መጥፋት አለበት። የትግራይ ህዝብ ጠላት አማራም፤ ሻቢያም፤ ብልጽግናም አይደለም። ወያኔ ሃርነት (ባርነት) ትግራይ እንጂ! በቃኝ!
ጎበዝ ችሎታ ያለው ሰው የጁዋር መሃመድን መጽሃፍ (ተረት) ኮፒ አድርጎ በኢንተርኔት ቢለቀው መልካም ነው፡፡
እንደ ኢትዮጵያ የመሰለች ብዙ ታሪክና ባህልም ያላት አገር በፖለቲካ ስም የሚነግድ ሰው እየተነሳ ሲዘላብድ፣ በተለይም አማራውን እወክላለሁ በማለት የባጡን የቆጡን ሲዘላብድ መስማት በጣም ያበሳጫል። ደርጉ አንዳርጋቸው ከደመቀ ጋር በመሆን በወጣትነት ጊዜው በህወሃት ተመልምሎና የእነሱ ካድሬ በመሆን ወያኔ 27 ዓመት ያህል ስልጣን ላይ በነበረበት ዘመን እንደ ጓደኞቹ ወያኔን ያገለገለ ነው። ወያኔ ስልጣን ላይ በነበረበት ዘመን በአማራውም ሆነ በተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ወንጀል ሲፈጽም አብሮ የተባበረና ለዛሬይቱ ኢትዮጵያ በእንደዚህ ዐይነት ሁኔታ ውስጥ እንድትገኝ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ካደረጉት ውስጥ ከፍተኛውን ቦታ የሚይዝ ነው። በአጠቃላይ ሲታይ ገዱ አንዳርጋቸውና ጓደኞቹ የአማራውን ክልል በሚያስተዳድሩበት ዘመን ሰፊውን የአማራ ህዝብ የሚጠቅም፣ እንደሰው እንዲኖርና ራሱንም እንዲችል የሚያደርገው አንዳችም የልማት ስራ አልሰሩም። በአንፃሩ ራሳቸው የሆቴልቤት ስራ እንዲስፋፋ በማድረግና እዚያ ገብተው በመዝናናት እንወክለዋለሁ የሚሉት የአማራ ህዝብ የተቦጫጨቀ ልብስ ለብሶ ሲሄድ ይታያል። እንደ ኦርቶዶክ ሃይማኖት የመሳሰሉት ተቋማት በአንዳንድ መነኩሴዎች ጥረት ራቅ ያሉና በቀላሉ ሊደረስባቸው የማይችሉና ጥንታዊ ገዳማትና ቤተክርስቲያናት ባሉበት አካባቢ ሰፊው አማኝ ህዝብ በቀላሉ በመጓጓዣ መጥቶ በሃይማኖት ስርዓት ላይ ይካፈል ዘንድ መንገድ ይሰራልን ብለው ሲያመለክቱ አይቻልም በማለት በአካባቢው የልማት ስራ እንዳይካሄድ ያደረጉ ናቸው። ከዚህም በላይ ባህር ዳር ከተማ ውስጥ ሰፋ ያለ የገበያ ቦታና ከአቧራ በስተቀር ምንም መቀመጫና መጠለያ የሌለው ቦታ ገበሬዎችም ሆኑ ነጋዴዎች በዚያ በጠራራ ፀሀይ ከስምንት ሰዓት በላይ ሲቃጠሉ የገበያ አዳራሽ መስራት አለብን በማለት አንዳችም ዕርምጃ ለመውሰድ ያልቻሉ ናቸው። ሃሳቡም በፍጹም የመጣላቸው አይደለም። እኔ ራሴ እንዳየሁት ከገጠር እየመጡት የተለያዩ ሰብሎችንና ሽንኩርት፣ እንዲሁም ፍራፍሬዎችን የሚሸጡ መጠለያ የሌላቸው ብቻ ሳይሆኑ መጸዳጃም በአካባቢው የለም። እንደምንም ብለው ከስምንት ሰዓት በላይ በጠራራ ፀሀይ ከተቃጠሉ በኋላ እንደገና በእግራቸው ብዙ ኪሎሜትር ተጉዘው ወደ ቢታቸው ይመለሳሉ። በመሰረቱ በአካባቢው ለገበያ አዳራሽ መስሪያ የሚሆን ለጡብ መቀቀያ አፈር ባለበትና ዲንጋይም በተትረፈረበት ቦታ ሰፋ ያለና በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሊያስተናግድ የሚችል የገበያ አዳራሽ መስራቱ ይህንን ያህልም የሚከብድና ብዙ ወጪም የሚጠይቅ አይደለም። ከተሰራም በኋላ ከገበያ አዳራሹ በሚገኝ ገቢ ዋጋውን እንደገና መሸፈን ይቻል ነበር። ሌላም ባህር ዳርን ውስጥ ውስጡን እየተዘዋወረ ለጎበኘ ሰው የሚገነዘበው ነገር ከተማዋ በሚገባ በዕቅድ ጥበባዊ በሆነ መንገድ የተገነባ ከተማ አይደለም።
ለማንኛውም ይህንን ወንጀል የሰራና ምንም ዐይነት የፖለቲካ፣ የፖለቲካል ኢኮኖሚና የሶስዮሎጂ ዕውቀት የሌለው ሰው በፖለቲካ ስም እየወጣ ድምጹን ሲያሰማ መስማት በጣም ያሳዝናል። ገዱ አንዳርጋቸው ከቤልጂግ ወደ አሜሪካ ካቀና በኋላ ከይልቃል ጋር ጌቶቹን ለመለማመጥ ነው ወደ ስቴት ዴፓርትሜንት ያቀናው። እንደሚታወቀው ወያኔን ስልጣን ላይ ያወጣውና አገራችንንም በእንደዚህ ዐይነት ሁኔታ ውስጥ እንድትወድቅ ያደረገው የአሜሪካን ኢምፔሪያሊዝም ነው። ገዱ አንዳርጋቸውና ኢንጂነር ይልቃል እያለ ስሙን የሚጠራ ሰው አሜሪካን በኢትዮጵያና በተቀረው የሶስተኛው ዓለም አገሮች የሰራውን ወንጀል የተገነዘቡ ቢሆን ኖሮ አሜሪካንን ለመለማመጥ ወደ ስቴት ዴፓርትሜንት ባላቀኑ ነበር።በነገራችን አቢይ አህመድም ስልጣን ላይ የወጣው በአሜሪካኖች ታግዞና ወያኔ ያለገባደደውን እርኩስ ስራ እንዲያጠናቅቅ ተብሎ ነው። ይህም ማለት ኢትዮጵያን በሁሉም አቅጣጫ ማዳከም፣ ህዝቡን አቅመ-ቢስ ማድረግና የአገራችንንም የጥሬ ሀብት ማስበዝበዝ ነው። ሀቁ ይህ ሆኖ ካለና አንድ ሰው ፖለቲካ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ሳይገባው እየተነሳ የሚዘላብድ ከሆነ በምን መለኪያ ነው አማራውን ወይም ፋኖን እወክላለሁ በማለት ገዱ አንዳርጋቸውና ጓደኞቹ የሚዘላብዱት። ጋዜጠኛ ነን የምትሉም እንደዚህ ዐይነቱን ወንጀለኛ ሰው እየጋበዛችሁ ውዥብንር እንዲነዛ ማድረጋችሁ ከተጠያቂነት ልታመልጡ የሚያደርጋችሁ አይደለም። ከእንግዲህ ወዲያም ገዱ አንዳርጋቸውና ጓደኞቹ ውዥንብር መዝናታቸውን ማቆም አለባቸው። እንዘኢሁን ሰዎች የሚያስተናግድ በጋዤጠኝነት ስም የሚነግድ ሚዲያም ሆነ ግለሰብ ከተጠያቂነት በፍጹም ሊያመልጡ አይችሉም።
ወደ ጃዋር ልምጣ። ይህ ግለሰብ በከፍተኛ የውንጀል ስራ መጠየቅ ያለበትና እስርቤትም መወርወር ያለበት ነው። ጃዋር በሲአይኤና በአረቦች በመመልመል ወጣቱንና ምንም ዕውቀት የሌለውን በኦሮሞ ስም የሚነግደውን ወጣት እየሰበሰበ የሚዘላብድና ውዥንብር የሚነዛ ነው። ጃዋር ምንም ዐይነት ዕውቀት የሌለ ሰው ነው። እንደ ገዱ አንዳርጋቸው ለአንድ አገር ግንባታ በሚያስፈልጉ ዕውቀቶች ላይ ጊዜ በመውሰድና በማጥናት ጭንቅላቱን የገነባ ሰው አይደለም። ጊዜው አሁን ነው በማለትና በራሱ ኤጎ በመጠመድ ሰፊውንና ምንም ዕውቀት የሌውን ወጣት የሚያወናብድ ተራ የፖለቲካ ነጋዴ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥም ስድሳ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር የሚያወጣ ቪላ ቤት ያስገነባና ምንም ሳይሰራ ወይም በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ሳይሳተፍ የማጅራት መቺ ፖለቲካ በማካሄድ በአጭር ጌዜ ውስጥ የናጠጠ ሀብታም ለመሆን የበቃ ሰው ነው። ተስፋዬ እንዳለው ጃዋር የአሜሪካ ዜግነት ያለው ሰው ሲሆን በመሰረቱ በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቶ የመሳተፍ መብት ሊኖረው አይገባም። በህዝብም ዘንድ ተቀባይነት አለኝ እያለ የሚያወራው በምን ስራው ተቀባይነት እንዳገኘ በፍጹም ሊነግርን አይችልም። ይህ ግለሰብ እንደ ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ምንም ዐይነት ተሳትፎ እንዳይኖረው ማድረግ የማንኛውም የአገር ወዳድ ተግባር መሆን አለበት።
ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)
ወንድሜ ፈቃድ – እንኳን ገድና ጃዋር ቀርቶ አሁን ላይ ፈጣሪ ራሱ ካለበት በሰው መሃል ተገኝቶ ስሙኝ ቢል ሰሚ የለም። ዓለሙ ሁሉ ተዘላብዷል። የጃዋር፤ የገድና የመስሎቻቸው የፓለቲካ ጫጫታም ጸጥ እርጭ ይላል። እንኳን የሃበሻው አስረሽ ምቺው ፓለቲካ ይቅርና 70 አመት የተለፋበትና እልፎች የተሰውለት የራሺያው አብዪትም ድምጥማጡ ጠፍቷል። የእነዚህ ስመ ፓለቲከኞች ወሬው መናፈሱ የወሬውን ይዘትና ብቃት አያሳይም። የንግድ ምልክት መሆኑን እንጂ! የወሬ ንግድ በስማ በለው! በዚህ ሁሉ መሃል አንድ አሌክሳንድር ፑሽኪን የጻፈው ግጥም ትዝ አለኝ።
የልጅነት ዘመን ጫወታዎች ሁሉ የሉም ህልም ሆነዋል
እንደ ማለዳ ጉም ብን ብለው ጠፍተዋል
ሆኖም ምኞት አለ የሚያቃጥል ገና
በከባድ ስልጣን ሥር ላለን በጭቆና (አያልነህ ሙላቱ እንደተረጎመው)
የሃገራችን የፓለቲካ እሰጣ ገባን የበለጠ መራራ የሚያደርገው ለብሄራቸውና ለጊዜው የፓለቲካ ገዢ መደብ ካደሩ በህዋላ ውጭ ሲወጡ ምላስ ማውጣታቸው ነው። ገዳዪም፤ አሳሪውም፤ ገራፊውም ቱልቱላ ይነፉብናል! ያኔም አሁንም የምናየው ይህኑ ነው። ያለፈውን ከአሁኑ የሚለየው የብሄርተኞች ስካር መበርከቱ ነው። እንደ እነ በቀለ ገርባ ያለው የፓለቲካ ሙት ተምረናል እያሉ የቆምነው ለብሄራችን ብቻ ነው ኦሮምኛ ካልተናገሩ አትግዙ አትለውጡ ያሉን ዛሬ ላይ አሜሪካ መተው ተወትፈዋል። ይህ ትራጄዲም ኮመዲም ነው። የሁለቱ ተውኔቶች ድብልቅ መጠሪያው ምን እንደሆነ አላውቅም። የምናየው ግን ይህኑ እውነት ነው። ስናሳዝን!
እውቁ ደራሲ በዓሉ ግርማ በአንድ ድርሰቱ ላይ እንዲህ ብሎን ነበር።
የአንድ እናት ልጆች በአስተሳሰብ ተጣልተው
በአመለካከት ተለያይተው፤ የሚያስታርቅ ጠፍቶ
የእብድ ገላጋይ በዝቶ።
የየዘመናቱ እብዶችና ጠበንጃ አንጋቾች ስንቶችን በሉ። ግን ፍትህ የት አለች? ሰላምስ መገኛዋ የት ነው? አንጋጠን ብናይ፤ በምድር ላይ ብንርመሰመስ መልስ የለም። የሚቀማው ይቀማል። የሚሞተው ያለግዜውም በጊዜውም ይሰናበታል። አንድ ሃዘን ደርሶ ሲመለስ ሌላዋ ከአራስ ጥየቃ ትመለሳለች። ይህን ሁሉ አይቶ ይሆን አንድ ጸሃፊ ” Life is a one shot affair” ያለው። በአንድ ጊዜ በሁሉም ስፍራ መገኘትም መኖርም አይችልም። ከሞቱ በህዋላ ተባይም ሆነ ሌላ ነገር ሆኖ ተመልሶ መኖር የለም። አበቃ… አፈርን አፈር በላው! ግን እሳት ለመቆስቆስና ህዝብ ለማጫረስ በሩቅም በቅርበትም እድሜ ለኢንተርኔት ተችሏል። ግን እኮ ደራሲ አለማየሁ ገላጋይ እንደሚለው ” የፍጻሜአችን መጀመሪያ ላይ እንሆን”? ወይስ አቤ ጉበኛ በአንድ ለእናቱ መጽሃፍ ላይ ከዘመናት በፊት እንደነገረን ” አንድ ጊዜ ኢትዮጵያዊ ሆነን ተፈጥረናልና ተስፋ አንቁረጥ” ? አላውቅም። ነገር ሁሉ ግን ያሰለቻል፡ ያለፋል፡ ያኮረፍዳል፡ ያስረጃል፤ ፍትህ ሳያዪ የሞቱት ደም ይጣራል። ሁሉም ነገር ወደ ምንምነት (Nothingness) እያዘገመ ይመስላል። የሰነበተ ያያል።
ይህ በቃሉ አላምረው የተባለ አይባልም እንጅ (ሆዳም) ስብሃት ነጋ እግር ስር ቁጭ ብሎ ስብሃት የጎደለውን እየሞላ አማራውን ሲሳደብ ክርሞ ዛሬ ከመሰሉ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር ሁኖ ገበያው ወደ ሞቀበት ጠጋ ሲል ማየት ያሳዝናል፡፡ ጎበዝ የመጣው ሁሉ ካላገጠብን እራሳችንን መዉቀስ ይገባል ቢያንስ እንዚህ ሰዎች እራሳቸውን እንዲያውቁ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡ ጁዋር መሃመድ ከዚህ ገዱ አንዳርጋቸው፤ከዚያ በቀለ ገርባ ከዚህ አንዳርጋቸው ጽጌ ከወዲያ ነአምን ዘለቀ ከአጠገቡ ትላንት ምንም እንዳላደረጉ ሁሉ ሲከተሉት በነበረው ስሌት ዳግም ሊያሞኙን ሲሞክሩ ማየት አግባብ አይሆንም፡፡ ጁዋር መሃመድ ማሰቢያው ተደምሶ ” በኢትዮጵያና በኬንያ መሃል ያለው ግ ንኙነት እንዳይበላሽ” አስቤ የመጽሃፌ(የተረቴ) ምረቃ አውሮፓ እንዲሆን ወስኛለሁ ብሎ በድፍረት ለእኛው ሲናገር ምን ያህል እንደተናቅን ያሳያል ጎበዝ ማሰብ የሚችሉ ወገኖች ያሉበት አገር እኮ ነው ተው ልንላቸው ይገባል፡፡ ጦርነት ባህላችን ነው መብረቃዊ ጥቃት ከፍተን ባሉበት አስቀርተናቸዋል ያሉ ትግሬዎች ተገልብጠው በትግሬ ላይ ጄኖሳይድ ተፈጽሞበታል እያሉ ሲያላዝኑ ያንን ተከትሎ ህዝቡ ከወንጀለኞች ጎን ቁሞ ሲያላዝን መመልከት ይገርማል፡፡ ጎበዝ በኢትዮጵያ ወታደር ላይ የተፈጸመው ሸፍጥ ዘወትር ሊያንገበግበን ይገባል ትግሬዎች ከኣእምሮዋችን ሊያጠፉት ይፈልጋሉ ይህ ቀን እንደ የካቲት 12 የሰማእታት ቀን ዘወትር ሊከበር ይገባል ፡፡
ፈጣሪ ይባርክህ።እዉነታዉን አስፍረሃል።ነገር ግን እነዚህን ግለሰቦች እኮ መኮነንም ብቻ ሳይሆን ከተጫነባቸዉ የዉጭ ጫና እና የግል ስግብግብነት ደፍረዉ ወጥተዉ ኢትዬጵያን እና ህዝቧን እንዲያስቀድሙ ፈጣሪ ከባንዳነት ልቦና እንዲወጡ መፀለይም ያሻል።