August 17, 2024
1 min read

በእነ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሃት ቡድን እነ ጌታቸው ረዳ በህወሓት ስም እንዳይንቀሳቀሱ አግጃለሁ አለ

455817712 1041209760957744 4621399522160588346 n
ቅዳሜ ነሐሴ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ውጥረትና መካረር የበዛበት የህወሃት ፖለቲካዊ ተቃርኖ ልዩነቶች አሁንም ጎልተው መታየታቸውን ቀጥለዋል፡፡
ይህን ተከትሎም የህወሃትን 14ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በውዝግብ ውስጥ ሆኖ እያከናወነ ያለው የነ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል ቡድን አዲስ ውሳኔ ማስተላለፉ ተሰምቷል፡፡
የህወሃት ሊቀመንበር ቡድን ዛሬ ባወጣው መግለጫም በ14ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ያልተሳተፉ የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ከዛሬ ነሃሴ 11 2016 ዓ.ም ጀምሮ በየትኛውም መድረክ በህወሓት ስም እንዳይቀሳቀሱ ማገዱን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ይህም የታገደው ቡድን ማለት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራና 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን የያዘ ሲሆን በህወሃት ስም የሚደረግ የዚህ ቡድን እንቅስቃሴ እንደማይታወቅ በሊቀመንበሩ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል በኩል የወጣው መግለጫ ያመላክታል፡፡
ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰአት ድረስም በአቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን በኩል ምላሽ አልተሰጠም፡፡

አዲስ ማለዳ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop