June 10, 2024
4 mins read

ከተሰወሩ 3 ወራት ተቆጥሯል!! (እየሩሳሌም ዓለሙ -አሻም)

448095691 857731069735329 4606614059049850902 n
448095691 857731069735329 4606614059049850902 n
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፌዴሬሽንና የክልል ምክር ቤት ተመራጩ ሀብታሙ በላይነህ ከተሰወሩ ከ3 ወራት በላይ እንዳስቆጠሩ እህታቸው ለአሻም ተናገሩ፡፡
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በመወከል የአማራ ክልልና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባሉ ሀብታሙ በላይነህ በአዲስ አበባ ከተማ የካቲት 22 ቀን 2016 ዓ.ም ለስብሰባ በሚል ከመኖሪያ ቤታቸዉ ወደ አራት ኪሎ ባቀኑበት ወደቤታቸው ሳይመለሱ ቢሰወሩም ዛሬም ያሉበትን ማወቅ እንዳልተቻለ እህታቸው ደብሪቱ በላይነህ ለአሻም ነግረዋታል፡፡
የምክር ቤት አባሉ በ2013 ዓ.ም በተካሄደዉ 6ተኛው ዙር ምርጫ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን)ን በመወከል በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም ከቋሪት ምርጫ ክልል አሸንፈዉ የክልሉና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች አባል በመሆን እስከተሰወሩበት ቀን ድረስ በስራ ላይ ነበሩ፡፡
እህታቸዉ ደብሪቱ በላይነህ ለአሻም እንደነገሯት ከሆነ ባለፉት ሶስት ወራት ከሚኖሩበት ወረዳ እስከ አዲስ አበባና ፌደራል ፖሊስ መፈለጋቸውን፣ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ጭምር አመልክተዋል፡፡ ነገር ግን ይህ ነው የሚባል ፍንጭ ሳይገኝ 3 ወራት አልፈዋል ይላሉ፡፡
‹‹ ሀብታሙ በላይነህ አንድ ግለሰብ አይደለም፤ በስሩ መርጦ ለምክር ቤት የወከለዉ ህዝብ አለ ›› የሚሉት ደብሪቱ ይገኝበታል ሲሉ የገመቷቸው ተቋማት ሁሉ ደጅ መጥናታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ይሁንና እንደራሴው የት እንደገቡ ማወቅ አልተቻለም፡፡ መንግስት ያሉበትን በማሳወቅ እንዲተባበረን ሲሉ ተማጽነዋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖለሲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንዳር ማርቆስ ታደሠ መረጃው እንደሌላቸው ጠቅሰው ማንኛውም የቤተሰብ አባል ‹‹ ሰው ተሰውሮብኛል በሚል ጥቆማ ከመጣ ክትትል እንደሚያደርጉ ›› በመጥቀስ በውል ሀብታሙ በላይነህ የት እንደሚገኙ መረጃው እንደሌላቸው ለአሻም ነግረዋታል፡፡ ወደ ፊት በክትትል ከደረሱበት ለቤተሰብም ሆነ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርጉ ግን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጄይላን አብዲ በበኩላቸው ይህን የሚመለከተው የአዲስ አበባ ፖሊስ ነው ከማለት ውጪ ዝርዝር መረጃ አልሰጡም፡፡
በተመሳሳይ ይሄዉ ጉዳይ የተነሳለት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ግንቦት 20 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣዉ መግለጫዉ አስገድዶ መሰወርና አስሮ ማቆየት በሚል ንዑስ ርእስ ስር ተጠናቅሮ በሪፖርቱ ይፋ ማድረጉን የኮሚሽኑ የሰብአዊ መብቶች ክትትልና ምርመራ ሥራ ክፍል ከፍተኛ ዳይሬክተር ሚዛኔ አባተ(ዶ/ር) ለአሻም በማስታወስ ነግረዋታል፡፡
በእለቱ ባወጡት ሪፖርትም በአዲስ አበባ ከተማ የተፈጸሙ እገታዎችና ስወራዎችን እንደሚጠቃልል በመግለጽ፤ እነዚህ ችግሮች እልባት እስከሚያገገኙም ክትትላቸዉ እንደሚቀጥል አመላክተዋል፡፡

1 Comment

  1. ሶስት ሺህም ሆነ መቶ ዓመት የነጻነት ዘመን አላት የምትባለው ኢትዮጵያ ለህዝቦቿ የማትበጅ የግፈኞች መናህሪያ ሃገር ናት። የክርስቲያን ሃገር ገለ መሌ የሚባለው ሁሉ የማታለያ ሃሳብ እንጂ ከህዝቡ ተግባርና ለዘመናት ከምናየው ግፍና መከራ ጋር ሲገናዘብ ለጨረቃና ለቆመ ዛፍ የሚሰግድ ህዝቦች የተሻለ ስብዕና አላቸው። ንጉሱን በሃይል የፈነቀለው የወታደር መንጋ በምድሪቱ ላይ የሰራው የ 17 ዓመት የደም ጎርፍን የተካው ጠባብ ብሄርተኛው ወያኔ ለ 27 ዓመት ሃገሪቷን ለሺያጭ፤ ህዝቦቿን ለባርነት፤ ስደትና መከራ ዳርጎ አሁን እንሆ ከዚያው ከወያኔ ጆኒያ ያፈተለከው የኦሮሞ ስብስብ ይህ ነው የማይባል መከራን በአማራው ህዝብ ላይ በማዝነብ ላይ ይገኛል። ሰው መግደል፤ ማፈን፤ መዝረፍ፤ ሰውን በፍርድ ማጉላላት፤ ከሥራ ማባረርና ሌሎችም ህቡዕና ይፋ ግፎች ዛሬም በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ይፈጸማል። ህዝብን እንዲያገለግሉ የቆሙ ተቋሞች እንደ ፓሊስ ያሉት ሰውን በእንበለ ፍርድ የሚያንገላቱ፤ ማንም ተራ ወታደር አንድን ኢትዮጵያዊ/ት በድላ፤ በጥፊ የሚደበድብበት ከከፋም የሚገድልበት የአስረሽ ምቺው የብልጽግና ፓለቲካ ኦሮሞውን አስጨፍሮ ሌላውን የሚያስለቅስ ለመሆኑ የየቀኑ የግፍ ወሬዎች ያመላክታሉ። ለምሳሌ በቅርቡ ወደ ሃገሯ የተመለሰች እህታችን ከቦሌ ስትወጣ እቃ እረስታ ተመልሳ ለመግባት ስትጠይቅ ወጠጤው ፓሊስ በጥፊ ሲመታት ህዝብ ማየቱ እነዚህ ጊዜ የሰጣቸው ጥርቅሞች ማንንም እንደማይፈሩ ያሳያል። ግፍን ግፍ እየወለደው ዛሬ ላይ ሰው ሆድ ተቀዶ ጽንስ የሚወረወርበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። በየትኛውም የእምነትም ሆነ የእምነት የለሽ የሰው ልጅ የስብዕና መስፈሪያ እንዲህ ያለ በደል የፈጸመ ሰው ቆሞ መሄድ አልነበረበትም። ግን ፍትህ የት አለና! ያለምንም በደሉ ተዘቅዝቆ የተሰቀለው የሰው ደም ዛሬም ይጣራል? ለግፈኞችም የማብቂያ ጊዜ ግን አለ፤ ይመጣል!
    እልፎችን እንበለ ፍርድ ሰውሮና በር ቆልፎ ስለ ሰላም ማውራት ማፌዝ ነው። ሰው በወንጀሉ መጠየቅ የግድ ነው። የእኛ ሃገር ክስ ግን 99% የፈጠራ ክስ ነው። ሰው በማሰር፤ በመግደል፤ በማሳደድ ስልጣን ላይ መቆየት ቢቻል ኑሮ ወያኔ ደርግን ባልተካው ወያኔን ብልጽግና ባልሸወደው። ፓለቲካ የመገለባበጥ ስፓርት ነው። ለሃገር ለህዝብ ለወገን የሚባለው ሁሉ የፓለቲካው የውስልትና ፕሮፓጋንዳ ነው። ለእውን ለህዝብና ለሃገር የቆሙ ወገኖች ከንጉሱ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እንደተሳደድና እንደተገፈተሩ ብሎም እንደተገደሉ ነው።
    በወያኔና በብልጽግናው መንግስት የአማራ መከራ ጣራ ላይ መድረሱ ምንጩ ፍርሃትና በራስ አለመተማመን ነው። ከአማራ ህዝብ ለእኛ የሱዳን ህዝብ ይቀርበናል አይደል ያለው ወስላታውና ደም አፍሳሹ ደብረ ጽዪን! ግን እድሜ ልኩን በህዝብ ጥላቻ ልቡ ለተነደፈ ሰው ምንም መድሃኒት የለም። ሞት ብቻ ነው ገላጋዪ። እኔ ትግራዋይ፤ እኔ አማራ፤ እዚያ ጋ ጉራጌ እዚህ ጋ ኦሮሞ መባባሉ ሁሉ የድንጋይ ዘመን አስተሳሰብ እንጂ የ 21ኛውን ክፍለ ዘመን አስተሳሰብ አይመጥንም። የሰው ልጅ መለኪያው ሰው መሆኑ ብቻ ነው። ምድርም ለሁሉ የተሰጠች ናት። የጠባብ ብሄርተኞች በሽታ ተላላፊ ደዌ ነው። አፍን ቢያፍኑ፤ አይን ቢጨፍኑ፤ አፍንጫን ቢይዙ ህመሙ የልብ ነውና ማምለጥ አይቻልም። ወንድምና እህቱን ገድሎና አስገድሎ ከሚፎክሩና ከሚያፋክሩ ጅሎች ጋር መከራከር በጨለማ ውስጥ ሆኖ አያለሁ እንደማለት ነው። ህሊናቸው የሞተ፤ በህዝባቸው ደም የሚነግድና የሚያተርፉ፤ የሰው ልጅ ሰቆቃ የማይሰማቸው የቁም በድኖች ናቸውና። የእውን ታሪክን ወደ ኋላ እያሽቀነጠሩ በከፈሏቸው ሰዎች አዲስ ታሪክ እያጻፉና እየጻፉ ሰውን ማማታት ከረጅሙ የፕሮፓጋንዳ እቅዳቸው አንድ ነው። ነገ በእኔ ይደርሳል የማይሉ ድርቡሾች ምድሪቱን ወረዋታል። ባልተፈጸመ ታሪክ ሰውን እየጠሉና እያስጠሉ ስንቅ ሸምተውበታል። ግን ይህም ያልፋል። እንኳን ይህ ቢወቅጡት እንቦጭ የሆነው የሃበሻ ፓለቲካ ይቅርና 70 ዓመት ሙሉ የተለፋበት የራሺያው ፓለቲካም እንደ እንቧይ ካብ ፍርክርኩ ወጥቶ ይኸው እንሆ ዛሬ ላይ አብረው የኖሩ ህዝቦች ዪክሬንና ራሺያ በመፋተግ ላይ ይገኛሉ። የፓለቲካ ንፋስ አቅጣጫ የለሽ ነው። የዛሬ ሽርኮች የነገ ተገዳዳሪዎችና ተፋላሚዎች ይሆናሉና!
    የዲያስፓራም ሆነ የሃገር ቤት የፓለቲካ ፓርቲዎች ሆነ ወይም በሌላ ስም ራሳቸውን እየጠሩ በየጊዜው እንደ አሸን ብቅ ብለው የሚሰወሩት ሁሉ መስማማት ያቃታቸው፤ አንድ አንድን ማድመጥ የተሳነው አፍ እንጂ ጆሮ የሌላቸው የጊዜ ማማቻዎች እንጂ ፍሬ ነገር የላቸውም። አንድ 4 ኪሎ እንገባለን ሲለን፤ ሌላው የሽግግር መንግስት ይቋቋም ይለናል። ቅማልን የት ትሄጃለሽ ቢሏት መተማ፤ ትደርሻለሽ ልብማ… አይ ጊዜ እንኳን ደስ አላችሁ ከ100 ሺህ በላይ የአማራ ተማሪዎች ለ 8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መቀመጥ አይችሉም። ብዙዎችም የ 6ኛ ፈተናን አይፈተኑም። ህዝብን ነጻ ማውጣት እያደነቆሩ ከሆነ ተሳክቶላችሁሃል። ግን ዛሬ ላይ እንደ ብርቅ የምታዪትና የምትሞቱለት ጉዳይ ነገ ሰከን ብላችሁ ስታዪት ፍርሽ ቢሆን ራስ ይዞ እየየ ማለት ጊዜን ወደ ኋላ መልሶ ለማስተካከል እድል አይሰጥም። ብልጽግና ስማ – በፓለቲካና በግፍ የታሰሩትን ሁሉ ፍታ! እናንተ የብሄር ታጣቂዎች መገዳደል ይብቃ፤ በጠራ ሁኔታ ጥያቄአችሁን አቅርባችሁ ነገር በሰላም ቋጩ። ጦርነት ለማንም አይበጅም። የሻገተ የፓለቲካ ውሸት የእንጀራ ኮቾሮ ሆኖ ህዝባችን ከረሃብ አያድንም። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Abiy Ahmeds self dialogue committee 1
Previous Story

ፍኖተ እንጦሮጦስ -የብልጽግናው ፖለቲካ ድርድር፣

191079
Next Story

ፋኖ አንድ ሌሊት አያሳድረንም” የአማራ ብልፅግናየኢሳያስ ግዙፍ ጦር ወደ ወልቃይት

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop