አጤ ምኒልክና ኢጣሊያኖች – ከታሪክ ማህደር

የታሪክ ጥናት ለሕሙም አእምሮ ፍቱን መድኃኒት ነው።

በእደ ማርያም እጅጉ ረታ

ኢትዮጵያ ጥንታውያን ከሚባሉት ሀገሮች አንዷ ስትሆን፣ ከአምስት ሺህ ዓመት ያላነሰ ታሪክ አላት። በእነዚህ ዘመናት፣ ቀደምት አባቶቻችን ሠርተው፣ ትተውልን ካለፉት ሥራዎች መካከል የአክሱም ሐውልት፣የላሊበላ ቤተ መቅደስ ሕንፃዎች፣ የጎንደር ቤተ መንግስቶች ለምስክርነት የሚጠቀሱ ናቸው። ባለፉት በእነዚህ ዘመናት ሀገራችን የእርስ በርስ ጦርነትና ከውጭ በመጡ ወራሪዎች፣ ብዙ ቅርሶች ወድመዋል፣ የሰዎች ሕይወት ጠፍቷል። ከእዚህ ሁሉ ፈተና በኋላ፣ በዐሥራ ስምንተኛውና ዐሥራ ዘጠነኛው ምዕት ዓመት፣ ሀገራችን ዘመነ መሳፍንት በመባል የሚታወቀው ጊዜ ውስጥ ገባች። ያ ወቅት ደግሞ አውሮጳውያን አፍሪቃን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመከፋፋል ወስነው ዘመቻቸውን የጀመሩበት ወቅት ነበር።

ትረካውን ለማድመጥ –https://www.ethiopianorthodox.org/amharic/tereka/Emperor%20menelik_final_26-Dec-2020.mp3

የአማርኛ ጽሑፉን ለማንበብ-

 

Beide Mariam
ተጨማሪ ያንብቡ:  ከታሪክ ማህደር: ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share