December 30, 2023
2 mins read

አዲሳባ ገንፍል!

addis ababa zehabesha
addis ababa zehabesha

እስከ መቼ ጥደው ያንፈቀፍቁሃል፣
ስንት ዘመን ቀቅለው ንፍርቅ ያረጉሃል፣
አዲሳባ ገንፍል እሳት በዝቶብሃል!

ተቤትህ አውጥተው መንገድ ጥለውሃል፣
የግዛትን ቀንበር በጫንቃህ ጭነዋል፣
ሲፈልጉ እንደ በግ ጎትተው ያስሩሃል፣
ሰውነትን ገፈው ግዑዝ አርገውሃል!
በራራ አዲሳባ ምንድን ይሰማሃል?

እንደ በሬ አፍነው አፍህን ዘግተዋል፣
ደንቆሮም ሊያደርጉህ ጆሮህን ደፍነዋል፣
አውረው ሊሸጡህ ዓይንህን ጋርደዋል፣
መብትህን ተገፈህ ስንት ዘመን ያልፋል?

ወገንህን ሕዝብህን በድሮን ፈጅተዋል፣
ለድሮኑ መግዣም ብር ያስገብሩሃል፣
እግርህን በእጆችህ ቁረጠው ይሉሃል፣
እንዲያው አዲሳባ ምንድን ይሻልሃል?

በቋንቋ ወረንጦ ሲነቅሱህ ኖረዋል፣
ጠርገው ሊያስወጡህም ቁማር ቆምረዋል፣
ፈተና የሚባል መጥረጊያ ሰርተዋል፣
አወይ አዲሳባ ምንድን ይበጅሃል?

ፈረስ ሲለጉሙት በኮቴው ያደማል፣
ዶሮ ለእርድ ሲጎተት በጥፍሩ ይጭራል፣
በሬ ለእርድ ሲጠለፍ በቀንዱ ይዋጋል፣
ያንተ ዝምታ ግን እግዚኦ! እግዚኦ! ያሰኛል!

ግለት ሲያሰቃየው ፈንድሻ ይንጣጣል፣
በከሰል ሲፈላ ቡና ቡልቅ ይላል፣
እሳት ሲበዛበት ሽሮ ተክ ተክ ይላል፣
አንተ ተቃጥለህም ድምጥን ዋጥ አርገሃል፡፡

በእሳት ሲፍለቀለቅ ውሀም ይፎክራል፣
ወደ ታች ነጥሮም እሳቱን ያጠፋል፣

ይበቃል! ይበቃል! አንድ በአንድ መቃጠል፣
ይበቃል! ይበቃል! በጅሎች መቀቀል፣
እሳቱን ለማጥፋት አዲሳባ ገንፍል!

በላይነህ አባተ ([email protected])
ታህሳስ ሁለት ሺ አስራ ስድስት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop